In todays’ Ethiopia the word Abay has become a source of worry for a few and brings despair and anger to the many. We have two Abays that are in the news and they are both causing us internal and external problems. Abay the river አባይ ወንዝ is as victim as the rest of Ethiopia. Poor Abay of Egypt and the great pyramids, the longest river in the world and a name that evokes greatness and pride among Ethiopians is reduced to becoming a prop for Woyane ponzi scheme. The Dam that will never be built … [Read more...] about Ethiopia and the two Abays
የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች
ክፍሉ ከኮሪደሩ ላይ ከተንጠለጠለ አምፖል በሚመጣ ብርሃን ፈገግ ብሏል፡፡ እኔም ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ ወደ ክፍሉ ስገባ ከክፍሉ አንደኛው ጫፍ ላይ አንድ ቀጠን ያለ ሰው ድምፁን በትንሹ ከፍ አድርጎ ቁርዓን ‹እየቀራ› ነበር፡፡ በክፍሉ ሌላኛው ጫፍ ላይ ደግሞ አንድ ፍራሽ፣ አንድ የውሃ ጀሪካን እና ትንሽ ልብሶች በፌስታል ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡ በሌላኛው የክፍሉ ጫፍ ደግሞ የሽንት ባልዲ - ሽታውን ለመቀነስ ሲባል በግማሽ ውሃ ተሞልቶ ተቀምጧል፡፡ ክፍሉ ውስጥ እንደገባሁ አንዱ ጫፍ ላይ ትንሽ ቆም ካልኩ በኋላ በክፍሉ ውስጥ ያገኝሁት ብቸኛው ሰው ፍራሹ ላይ እንድቀመጥ በእጁ ሲጠቁመኝ ቁጭ አልኩ፡፡ ፍራሽ ላይ እንደተቀመጥኩ በፍራሹ ጫፍ ላይ የጆን ግሪሻም ‘The Last Juror’ መፅሃፍ ተቀምጦ አየሁት፤ አንስቼ ስመለከተው ክፍሉ ውስጥ ያገኘሁት ሰው ቁርዓን መቅራቱን ጨርሶ እንግሊዝኛ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሙስሊም ፈተና በ224 ደቂቃዎች
የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ ሊያስገባ”?!
* ውሳኔው “ማዕቀብና የዕርዳታ ቅነሳ አያስከትልም” አና ጎሜዝ * የቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያዊ ልመና” አልሰራም የአውሮጳ ፓርላማ ሐሙስ ዕለት ባለ 19 ነጥብ ውሳኔ ህወሃት/ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ ላይ አስተላልፏል፡፡ ጉዳዩ ኢህአዴግ “ልክ ሊገባ ይሆን” የሚል አመለካከት ጭሯል፡፡ ረቂቁ ለውይይት እንዳይቀርብ የቻሉትን ያህል የጣሩት ቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያቸው” አልሠራም፡፡ ውሳኔው “ማዕቀብና የዕርዳታ ቅነሳ አያስከትልም” በማለት አና ጎሜዝ ተናገሩ፡፡ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ውሳኔው “ውስጡ በብረት የተወጠረ የቦክስ ጓንቲ ነው” ብለውታል፡፡ የአውሮጳ ፓርላማ ሐሙስ ዕለት የኢትዮጵያን ጉዳይ በተመለከተ የቀረበለትን ረቂቅ ውይይትና ክርክር ካካሄደ በኋላ በከፍተኛ አብላጫ ድምጽ ያለ አንዳች ማሻሻያና ለውጥ እንዳለ አጽድቆታል፡፡ ጉዳዩን ከሥሩ ሲከታተሉና ለኅብረቱ … [Read more...] about የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ ሊያስገባ”?!
ከናሚቢያ እስከ ኢትዮጵያ
ይድረስ ለኢትዮጵያዊያን የከበረ ሰላምታዬ ከናሚቢያ ዋና ከተማ (ዊንድሆክ) ይድረሳችሁ እያልኩ ስለምወዳት እና ስለምኖርባት ሀገር ስለ ናሚቢያ በጣም በትንሹ አሳጥሬ ላወጋችሁ ወደድሁ ። ናሚቢያ በደቡባዊ ምእራብ አፍሪካ የምትገኝ ሀገር ናት። በጀርመን ቀጥሎም በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ ቅኝ ትገዛ ነበር። በደቡብ አፍሪካ ኣፓርታይድ ቅኝ ግዛት በነበረችበት ጊዜ ይገዧት የነበሩት የአፓርታይድ ፍልስፍና አራማጆች ህዝቡን በቀለም በቋንቋ በብሔረሰብ እና በዘር ከፋፍለዉ እያንዳንዱ ብሔረሰብ በሀገሪቱ ላይ የራሱ የሆነ ክልል እንዲኖረው አድርገው ነበር። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ከናሚቢያ እስከ ኢትዮጵያ
አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያም ኔታኒያሁ አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እየሆነ መጥቷል በማለት ተናገሩ፡፡ ጉዳዩ ያስቆጣቸው የሙስሊም መሪዎች ንግግሩ በሃይማኖታችን ላይ ማዕቀብ ለመጣል የተቃጣ ነው ብለውታል፡፡ ባለፈው አርብ በእስራኤል ሸንጎ የሊኩድ ፓርቲ አባላት በተገኙበት ኔታኒያሁ ባደረጉት ንግግር በእስራኤል የሚገኙ የአረብ ከተሞች ለአገሪቷ ሕግ መገዛት አለባቸው ብለዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ ለአገሪቷና ለማኅበረሰቡ ግዴታቸውን መወጣት አለባቸው በማለት አስታውቀዋል፡፡ “በአብዛኛዎቹ የአረብ ከተሞች ሕግ አይከበርም፤ ይህም አዛን እና ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ተጠቃሽ ናቸው” በማለት ቢኒያም ኔታኒያሁ የተናገሩ ሲሆን ከዚህ አኳያ ከበርካታ መስጊዶች የሚሰማው አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት እያስከተለ” ስለሆነ መንግሥታቸው ሕግ ሊያወጣ መወሰኑን አስታውቀዋል፡፡ አዛን … [Read more...] about አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ
የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?
ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣው የዓለም የነዳጅ ዋጋ አሁን ደግሞ ሊብስበት ነው፡፡ በኢራን ላይ የተጣለው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ትናንት በመነሳቱ በዓለም ገበያ ለአንድ በርሜል ድፍድፍ ዘይት የሚከፈለው ዋጋ ከ31 ዶላር ወደ 28 ዶላር ገብቷል፡፡ ይህ በአንድ ቀን የታየ የዋጋ ልዩነት ለወደፊቱ እየባሰ ሊሄድ እንደሚችል የዓለም የኢኮኖሚ ጠበብት በመናገር ላይ ይገኛሉ፡፡ በኢኮኖሚክስ Principle መሰረት ዋጋ ሲቀንስ የፍላጎት መጠን ይጨምራል፡፡ የገንዘብ የመግዛት አቅምም ይጨምራል፡፡ ዋጋውን ተከትሎ በአቅርቦት ላይ የሚደረግ ቅናሽ ካልታየ በዚያው ዋጋ ብዙ ምርትና አገልግሎት መግዛት ይቻላል፡፡ አቅራቢው ምርቱን የሚጨምር ከሆነ ደግሞ (በኢራን ላይ የተጣለው ማዕቀብ በመነሳቱ የነዳጅ አቅርቦቱ መጨመሩን ልብ ይሏል) ገዥው የሚገዛው ምርትና አገልግሎት እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ስለዚህ እጥረት … [Read more...] about የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?
ከሰርቢያው ነውጥ አልባ ትግል ውጤታማነት ኢትዮጵያችን ምን ትማራለች?
ከክሮሺያ እና ከቦስኒያ ጋር በሁለት ጦርነቶች ተሸንፎ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ያደቀቀው የሚሎሶቪች መንግስት በህዝቡ ዘንድ ይሁንታን ባጣበት ሁኔታ ላይ እያለ እ.አ.አ በ1996 ዓ.ም በተካሄደው የክልል ከተሞች ምርጫ በስርቢያ አጠራር ዛየኖ ወይም ቱጌዘር የተሰኘው ፓርቲ በ40 የክልል ከተሞች ውስጥ ማሸነፍ ችሎ ነበር። ሚሎሶቪች ግን ለምርጫ ቦርዳቸው ውጤቱን እንዳያጸድቅ ቀጭን ትእዛዝ አስተላለፉ። በዚህም ሳቢያ ተማሪዎች ለ55 ቀናት እለት በእለት ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ተቃውሞ የመንግስት ተወካይ ከተማሪዎች ተወካይ ጋር ባደረጉት ስምምነት ለዛየኖ ወይም ቱጌዘር ለተባለው ፓርቲ በማን አለብኝነት ተነፍጎ የነበረውን 40 መቀመጫዎች መልሶ ማግኘት ቻለ። በተገኘው ድል መጠነኛ የስነልቦና ጥንካሬን ያገኙት እኚሁ ሰልፈኛ ተማሪዎች ለሚሎሶቪች ውድቀት ዋና ተዋናይ ለሆነው ኦትፖር ለተሰኘው ድርጅት … [Read more...] about ከሰርቢያው ነውጥ አልባ ትግል ውጤታማነት ኢትዮጵያችን ምን ትማራለች?
የማስተባበር ጥሪ
መንደርደሪያ ባሁኑ ጊዜ በሃገራችን ለፍትህ፤ ለነጻነትና ለዴሞክራሲ የሚደረገውን ትግል አስመልክቶ፤ ተደጋግሞ የሚነሳው ጥያቄ ተቃዋሚዎች ለምን ተባብረው አይታገሉም? የሚለው ነው። ጥያቄውን ያነሳው ማን ነው ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ ማን ያላነሳው አለ ብሎ መጠየቁ ተገቢ ይመስለኛል። እኔም አልደግመውም። የሃገሪቱን የተወሳሰበ ሁኔታ ስናጤን፤ በመተባበር ለመታገል በቅድሚያ በሁለት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ግልጽ የሆነ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን የሞትና የሽረት ጥያቄ አድረጎታል። እነዚህ ሁለት ሁኔታዎችም፤ የትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባር (ወያኔ) የባርነት አገዘዝ መወገድ አለበት የሚለው ባንድ ወገን፤ ከባርነት አገዛዙ መወገድ በሁዋላ የምትገነባው ኢተዮጵያ በሌላው ወገን ናቸው። ቀዳሚውን የትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባር (ወያኔ) የባርነት አገዛዝ መወገድ አለበት የሚለውን በተመለከተ፤ በተለያየ … [Read more...] about የማስተባበር ጥሪ
ጥምቀትና ጎንደር Vs የትዝብት ወግ
“ጥምቀትን በጎንደር መታደም መባረክ ነው” ይህ የብዙሃኑ የእምነቱ ተከታዮች የምስክርነት ቃል ነው፡፡ ጥምቀትና ጎንደር የገጠሙ እለት እንኳንስ ለጎብኝዎች ለነዋሪዎችም ታይተው አይጠገቡም፡፡ የጎንደር ጥምቀት በዓል ከመላ ኢትዮጵያ አከባበር የሚለይባቸው በሁለት ተያያዥ ምክንያቶች ይመስለኛል፡፡ ከቀድመው የመሳፍንት እና የአፄዉ ስርዓት ጋር በተያያዘ ከተማዋ ለረዥም ዓመታት መናገሻ ከተማ ሆና መቆየቷ፣ በጊዜው የነበረው ኃይማኖታዊ መንግስት በመሆኑ አብዛኛው ነዋሪ ጥብቅ የኦርቶዶክስ ክርስትና ኃይማኖት ተከታይ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ከሌላው አካባቢ (ከተማ) በተለየ መልኩ “የአርባ አራቱ ታቦታት” መገኛ መሆኗ የመጀመሪያው ምክንያት ሲሆን፤ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ከአፄ ፋሲል ቤተመንግሥት ምስረታ በኋላ ከቤተ መንግሥቱ በስተ ምዕራብ በኩል አራት … [Read more...] about ጥምቀትና ጎንደር Vs የትዝብት ወግ
ላለመክሸፍ?!
ሊቀ ሰላዩ ደብረጽዮን የህወሃት መክሸፍ ያሳሰባቸው ይመስላል። "ነጻው ጋዜጠኛ" ዳዊት ከበደ "አውራምባ times" በሚባለው ጉራማይሌ ጋዜጣ ላይ የሰሞኑን ቃለምልልሳቸውን ሲያትም ያወጣው ፎቶ በደብረጽዮን ጠረጴዛ ላይ የሚታየው Why Nations Fail የሚለውን የDaron Acemoglu እና የJames A. Robinson መጽሃፍ ነው። ላለመክሸፍ የባዕድ መጽሃፍ ከማንበብ ከምትሞቀው ወንበር ትንሽ ብድግ ብሎ "እረኛ ምን ይላል?" ማለት ከክሽፈት ያድን ይሆናል! ወይስ አላማው ለኦህዴድ መሪዎች ተሃድሶ ሊያስተምሩበት ይሆን? ወይስ ሃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው ግምገማ "አዳዲስ ቃላት አመንጭተህ አታውቅም" ተብለው ስለነበር "የሃይለማርያምን መሰደብ የሰማ" በማለት ለራሳቸው አዳዲስ ጸረ-ክሽፈታዊ ቃላትን ሊማሩበት ይሆን? የወንበሩዋ ተስፈኛ አይደሉ! መጽሃፉ ስለክሽፈት ብዙ ያስተምራል ግን … [Read more...] about ላለመክሸፍ?!










