• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኛ የነዳጅ ዋጋ የሚቀንሰው መቼ ነው?

January 20, 2016 11:33 am by Editor 1 Comment

ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ የመጣው የዓለም የነዳጅ ዋጋ አሁን ደግሞ ሊብስበት ነው፡፡ በኢራን ላይ የተጣለው የኢኮኖሚ ማዕቀብ ትናንት በመነሳቱ በዓለም ገበያ ለአንድ በርሜል ድፍድፍ ዘይት የሚከፈለው ዋጋ ከ31 ዶላር ወደ 28 ዶላር ገብቷል፡፡ ይህ በአንድ ቀን የታየ የዋጋ ልዩነት ለወደፊቱ እየባሰ ሊሄድ እንደሚችል የዓለም የኢኮኖሚ ጠበብት በመናገር ላይ ይገኛሉ፡፡

በኢኮኖሚክስ Principle መሰረት ዋጋ ሲቀንስ የፍላጎት መጠን ይጨምራል፡፡ የገንዘብ የመግዛት አቅምም ይጨምራል፡፡ ዋጋውን ተከትሎ በአቅርቦት ላይ የሚደረግ ቅናሽ ካልታየ በዚያው ዋጋ ብዙ ምርትና አገልግሎት መግዛት ይቻላል፡፡ አቅራቢው ምርቱን የሚጨምር ከሆነ ደግሞ (በኢራን ላይ የተጣለው ማዕቀብ በመነሳቱ የነዳጅ አቅርቦቱ መጨመሩን ልብ ይሏል) ገዥው የሚገዛው ምርትና አገልግሎት እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ስለዚህ እጥረት የሚባል ነገር አይኖርም ማለት ነው፡፡ “ነዳጅ” እጅግ ወሳኝ ከሚባሉ ሸቀጦች መካከል አንዱ በመሆኑ የዋጋው መቀነስ በሌሎች ምርቶችም ላይ የዋጋ መቀነስን ማስከተሉ የማይቀር ነው (“እንዴት” ለሚለው መልሱን ለናንተ ትቼዋለሁ፤ ይህ ማንም ሰው ሊረዳው የሚችል rudimentary economics ነው እንጂ የኒውክለር ሳይንስ አይደለም)፡፡

በሀገራችን የሚተመነው የነዳጅ ዋጋ ግን “ፍላጎት” እና “አቅርቦት” የተሰኙትን ወሳኝ የኢኮኖሚክስ እርከኖችን የሚከተል አይደለም፡፡ የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ገደማ ነበር የዓለም የነዳጅ ዋጋ ጣሪያ የነካው፡፡ ባልሳሳት በዚያን ጊዜ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ዘይት ዋጋ 138 ዶላር የደረሰ ይመስለኛል (አንድ ወዳጄ 168 ዶላር ነበረ ብሎኛል)፡፡ በወቅቱ በሀገራችን ውስጥ የቤንዚን ዋጋ በሊትር ሰባት ብር በመግባቱ “ጉድ ነወ” ያላለ ሰው አልነበረም፡፡ ከዓመት በኋላ ግን የዓለም ኢኮኖሚ ግልብጥብጡ ወጥቶ የነዳጅ ዋጋ መንሸራተት ጀመረ፡፡ እነሆ በዚያን ጊዜ የጀመረ እስከ አሁን እየተንሸራተተ 28 ዶላር ገብቷል፡፡ በኛ ሀገር ውስጥ ግን የዓለም ዋጋን ተከትሎ የተደረገ ማስተካከያ አለን??… እስቲ መልሱልን እባካችሁ፡፡

የዛሬ ዘጠኝ ዓመት የነበረው የነዳጅ ዋጋ በዓለም ደረጃ በ400% ቀንሶ እኛ ሀገር የሚከፈለው ተመን ሰማይ ጠቀስ ነው፡፡ እስቲ ጉዳችንን እዩት፡፡

(ምንጭ: አፈንዲ ሙተቂ/Afendi Muteki ፌስቡክ ገጽ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Rule of Law says

    January 27, 2016 09:10 am at 9:10 am

    ካገሬ ከወጣሁ ከ30 ዓመታት በላይ ሆኖኛል ቢሆንም ይህች አገር በለቤ ውስጥ ሰላለች ይህን ጥያቄ የነዳጅ ዋጋ በወረደ ቁጥር በሃሳቤ አስተናግደዋለሁ። በአንድ ወቅት ላይ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ደረጃ በጨመረበት ጌዜ መኪናዬን ለመሙላት $70 የከፈልኩበት ጌዜ አስታውሳለሁ በአሁኑ ወቅት ደግሞ ወደ $28 ገደማ ስከፍል ሁሌ እየሳቅኩኝ እነዳልሁ። ስለኢትዮጵያ ሳስብ ግን ጭማሪ እንጂ መውረድ በሎ ነገር ያለ አይመስለኝም። ምን ዋጋ አለው! ይህ ለህዝብ ያልቆመ ዱርዬ መንግስት ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule