• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ

January 21, 2016 08:35 am by Editor 1 Comment

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያም ኔታኒያሁ አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እየሆነ መጥቷል በማለት ተናገሩ፡፡ ጉዳዩ ያስቆጣቸው የሙስሊም መሪዎች ንግግሩ በሃይማኖታችን ላይ ማዕቀብ ለመጣል የተቃጣ ነው ብለውታል፡፡

ባለፈው አርብ በእስራኤል ሸንጎ የሊኩድ ፓርቲ አባላት በተገኙበት ኔታኒያሁ ባደረጉት ንግግር በእስራኤል የሚገኙ የአረብ ከተሞች ለአገሪቷ ሕግ መገዛት አለባቸው ብለዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ ለአገሪቷና ለማኅበረሰቡ ግዴታቸውን መወጣት አለባቸው በማለት አስታውቀዋል፡፡

“በአብዛኛዎቹ የአረብ ከተሞች ሕግ አይከበርም፤ ይህም አዛን እና ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ተጠቃሽ ናቸው” በማለት ቢኒያም ኔታኒያሁ የተናገሩ ሲሆን ከዚህ አኳያ ከበርካታ መስጊዶች የሚሰማው አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት እያስከተለ” ስለሆነ መንግሥታቸው ሕግ ሊያወጣ መወሰኑን አስታውቀዋል፡፡

አዛን (አድሃን) ለጸሎትና ለስግደት ሙስሊሙ እንዲሰበሰብ የሚደረግ ጥሪ ነው፡፡ ድምጸ መረዋ በሆኑ የሚሰማው ይህ ጥሪ በበርካታ ቦታዎች በድምጽ ማጉያ የሚደረግ ሲሆን በአንዳንድ ቦታዎች ያለ ድምጽ ማጉያም የሚከናወን ነው፡፡

“ይህንን (ጩኸት) መቀበል በጭራሽ አይቻልም” ያሉት ኔታኒያሁ በአረብም ሆነ በአውሮጳ አገራት እንዲህ ያለ ጩኸት በድምጽ ማጉያ እንዲሰማና ሰዎች እንዲረበሹ የሚፈቅድ ሃይማኖታዊ ፅሁፍ የለም ብለዋል፡፡ ስለዚህ ገደብ ሊደረግበት ይገባል፤ እንዲያውም ጩኸትን የሚከለክል ሕግ አለን እርሱን ተግባራዊ እናድርገው ብለዋል፡፡

በእስራኤል በሚገኙ የአረብ ከተሞች የሚታየው ከአንድ በላይ ሚስት የማግባት ሁኔታን በተመለከተም “ይህንን ክስተት በተመለከተ የሴቶች (መብት ተሟጋች) ድርጅቶች እንደ ሙታን ዝምታን” መምረጣቸውን የወቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ የተወሳሰበ መሆኑን ከመናገር ግን አልተቆጠቡም፡፡ ሲያጠቃልሉም “ሕግ የምንከተል አገር መሆን አለብን ወይም የለብንም” በማለት ቃላት በተግባር መተርጎም እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

በየሩሳሌምና በፍልስጤም ግዛቶች ጠቅላይ ሙፍቲ የሆኑት ሼክ መሐመድ ሁሴን ጉዳዩን በመስጊዶቻችን ላይ የተሰጠ “ማስጠንቀቂያ”፤ በሃይማኖቱ ላይ ማዕቀብ ለመጣል ያነጣጠረ ነው ብለውታል፡፡ በእስራኤል ሸንጎ አረባውያኑ እንደራሴዎች ጉዳዩ የዘረኝነት መንፈስ የተጠናወተው በማለት የጠቀሱት ሲሆን ኔታኒያሁ የአረብ ጥላቻ በመቀስቀስ ርካሽ የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት በመደጋገም የሚሞክሩት አደገኛ አካሄድ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

“ኔታኒያሁ እንደ አገር አስተዳዳሪ ጉዳዮችን መመልከት ይገባቸዋል እንጂ እንደ አምባገነን ወታደራዊ መሪ መሆን የለባቸውም” በማለት ሌላኛው እንደራሴ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ወቅሰዋል፡፡al-aqsa-mosque-southern-wall

የእስራኤል ሸንጎ አባላትና አይሁዳዊ ሰፋሪዎች በወታደሮችና በፖሊሶች በመታገዝ ባለፈው መስከረም ወር የአል-አቅሳን መስጊድ ከወረሩበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ከ2400 በላይ ፍልስጤማውያን ታስረዋል፤ 30 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ጨምሮ 158 ተገድለዋል፤ 10ሺህ የሚጠጉ ደግሞ ቆስለዋል፡፡ የየሩሳሌም ኢንቲፋዳ የሚባለውን ተቃውሞ ቀስቅሷል የሚባልለት ይህ ድርጊት ለእስራኤል በየሩሳሌም አካባቢ በሚገኙ የአረብ ሰፈሮች ላይ የከረሩ ሕግጋትን እንደትተገብር ነጻነት እንደሰጣት በሰፊው ይነገራል፡፡ (ለዜናው ጥንቅር የተለያዩ የዜና ምንጮችን ተጠቅመናል፤ የመግቢያ ፎቶ ሲያሳት ዴይሊ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Hunde says

    January 21, 2016 06:52 pm at 6:52 pm

    I fully agree with the PM. There is no reason to disturb the silent life of non-Muslims in the area. I travel to Finfinnee (Addis Ababa ) and one of the reasons I hate to be there is the uncontrollable and truly disturbing shouting from the. Mosques, specially in early morning.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule