• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች

February 11, 2020 07:53 pm by Editor Leave a Comment

የሙያው ባለቤቶችና ተመራማሪዎች ታጋቾችን ማስለቀቅ ራሱን የቻለ ታላቅ ጥበብና ስልት ይጠይቃል ይላሉ። የአጋቾችን ስነልቡና ለመስረቅ፣ ለማለስለስ፣ ወዘተ አደራዳሪዎች ፈጽሞ ሊታሰቡ የማይችሉ የሚባሉ ዘዴዎችን ሲጠቀሙ ይስተዋላሉ። የአጋቾቹን ፍቅረኛ ወይም እናት ወይም ሌላ ተወዳጅ የቤተሰብ አባል ወደ ዕገታው ቦታ በማምጣት በድምጽ ማጉያ የተማጽንዖ ቃል እንዲናገሩ ይደረጋሉ። የሃይማኖት መሪዎች፣ ሽማግሌዎች፣ ሌሎች ተጽዕኖና አመኔታ ሊጣልባቸው የሚችሉ ሰዎች በዚህ እንዲሳተፉ ይደረጋል። ይህንና ሌሎች መሰል ተግባራትን በመጠቀም የታገቱት ያለ አንዳች ችግር በነጻ እንዲወጡ ሙከራ ይደረጋል። በዚህም ምክንያት ረጅም ጊዜ የሚወስድ ዕገታ በሰላም የመጠናቀቅ ዕድሉ በጣም ከፍተኛ ነው ይባላል። 

ማፈን፣ ማገት፣ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው በቁጥጥር ሥር ማዋል፣ ወዘተ ያልተለመደ ተግባር አይደለም። በአብዛኛው የጤና ችግር ያለባቸው፣ አእምሯቸው የተቃወሰ፣ ከአእምሮ ሐኪም ቤት ያመለጡ ወይም መግባት ሲገባቸው ሳይገቡ የቀሩ፣ አሸባሪዎች፣ የጥቃት ሰለባዎች፣ ወንጀለኞች፣ እስረኞች፣ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው እና ሌሎችም በማገት ተግባራት እንደሚሰማሩ በየጊዜው የሚወጡ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። የአብዛኛዎቹ ዓላማም በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለማስከበር ያልቻሉትን እጅ በመጠምዘዝ ለማስፈጸም ሲሆን ጥቂት የማይባሉ ደግሞ ተፈጸመብን የሚሉትን ግፍ ለመበቀል የሚፈጽሙት ተግባር ሆኖ እናገኘዋለን። በየትኛውም መንገድ ቢሆን አእምሮው እጅግ የተቃወሰበት፣ የሚፈልገውን የማያውቅ፣ ካልሆነ በስተቀር አጋች ዓላማ አለው፤ በተለይ ደግሞ የፖለቲካ አጋቾች በምክንያት ነው የሚያግቱት፤ ይህንንም ዓለም እንዲሰማቸው የሚችሉትን ያህል “ይጮኻሉ”።

በዓለማችን በየቀኑ ከሁለት ሺህ በላይ ህጻናት የደረሱበት እንደማይታወቅ ይህም ከማገት ጀምሮ እስከ ሕገወጥ የሰው ዝውውር እስከ ግድያ እንደሚደርስ ዘገባዎች ያስረዳሉ። በሌላው በኩል ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ዕገታዎች ለዘመናት ሲፈጸሙ የኖሩ ሲሆን አንዳንዶቹ ከጥቂት ሰዓታት በላይ ያልወሰዱ ቢሆንም ሌሎች ብዙዎች ግን በርካታ ዓመታትን ያስቆጠሩ ሆነዋል።

ቴሪ ዌይት የተባለ የእንግሊዝ ቤ/ክ ተደራዳሪ በሊባኖስ የታገቱ አራት ሰዎችን በሽምግልና ለማስለቀቅ ወደ ሊባኖስ ካመራ በኋላ ሒዝቦላ ሰላይ ነው ብሎ በመጠርጠር አገተው። በመጨረሻም ለ1,763 (ከአራት ½ ዓመት) በኋላ ከታገቱት ጋር ተለቅቋል። “የኢራን የዕገታ ቀውስ” ተብሎ በሚጠራው ኢራን ያገተቻቸውን አሜሪካውያን ከ444 ቀናት በኋላ ለቅቃለች። ቼቺኒያ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ በነበረችበት ጊዜ በርካታ ሰዎች (ህጻናትም ጭምር) የሞቱበት የተለያዩ ዕገታዎች ተካሂደዋል፤ 800 ሰዎች የታገቱበትና ከመቶ በላይ ሞተው የተጠናቀቀው የሞስኮ ቴአትር ዕገታ እንዲሁም ከ350 በላይ ህጻናትን ህይወት የቀጠፈው የቤስላን ት/ቤት ዕገታ ጥቂቶቹ ተጠቃሾች ናቸው። በእነዚህና ሌሎች ዕገታና አፈናዎች ሁሉ አፋኞቹ ወይም አጋቾቹ ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ በግልጽ ይናገራሉ፤ ዓለም እንዲሰማላቸውም ያደርጋሉ። 

ለበርካታ ቀናት ባልታወቁ “ሽፍቶች” የታገቱት የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከታገቱ በርካታ ሳምንታት በኋላ ሚዲያውን አጨናነቀ። ባልታሰበ ፍጥነት እያደገም መጥቶ በአገርና ዓለም አቀፍ ደረጃ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አስደረገ። እጅግ በርካታ ሕዝብ በተለይ በአማራ ከተሞች ወጣ፤ አክቲቪስቶች የሚባሉቱም በሽሙጥ በለውጡ ኃይል በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትሩ አሸሞሩ፤ እርስዎን የሚጠብቀው ሪፓብሊካን ዘብ ታጋቾችን ማስፈታት እንዴት አቃተው በማለት ዕውቀትን የጾመ ልመና አቀረቡ፤ እናቶች ይጸልዩልኛል እያሉ እንዴት ሴቶች ልጆች ሲታገቱ ዝም ማለት አስቻለዎት በማለት ጠቅላዩን “ትህትና” በተላበሰ ሽሙጥ ወረፉ፤ ንጉሡ ጥላሁንም አልቀረላቸውም፤ ጸረ አማራ ተባሉ። በየማኅበራዊ ሚዲያውም ዘመቻው ቀጠለ።

ዓይን አፍጥጦ ወጥቶ የነበረ ነገርግን ሆን ተብሎ ትኩረት እንዳይሰጥበት የተደረገው ነገር ቢቢሲ አስቀድሞ ያወጣውና ከታጋች ወላጆች መካከል አንድኛው አባት የተናገሩት ነበር፤ “… ከእንግዲህ ከሷ ጋር መገናኘት እንደማልችል ነገረችኝ” ካሉ በኋላ “እና ታዲያ ምን አሏችሁ? ብዬ ስላት “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን”” አለችኝ ብለው ነበር ምስክርነታቸውን የሰጡት። ይህ ፍንትው ያለ እውነታ ለምን ትኩረት አልባ ሆነ?    

እንደሚታወቀው አጋች ዓላማ ስላለው ያገተበትን ዓላማ በመግለጽ የሚቀድመው አይኖርም። በዘመናችን እንዲያውም ያለውን ሚዲያ በመጠቀም አጋች ፍላጎቱን ዓለም እንዲሰማው ያደርጋል። በየጊዜውም ያገተውን እያስፈራራ የቪዲዮና የፎቶ መረጃ ይለቃል፤ ይህንን ካላደረጋችሁልኝ ይህንን አደርጋለሁ እያለ ይፎክራል። በደምቢዶሎው ግን ይህንን መሰሉ ድርጊት ሲፈጸም አልታየም። እንዲያውም ባልተለመደ ሁኔታ አጋቹ ዓይናፋር ይመስል መሰወርና አለመታወቅን ነው የመረጠው።

የሚፈልጉትን ባለማግኘታቸው አገራችንን ለማፍረስ እየጣሩ ያሉና ዓላማቸውንም ለማሳካት በትጋት የሚሠሩት ሩቅ ሳይሆን እዚሁ ቅርብ ያሉ ናቸው። ጽንፈኛ ብሔረተኞችና በይፋ የሚታወቁ ድርጅቶች በተለይ በአማራና በኦሮሞ ክልል የሚገኙ ከህወሓት ጋር የሚለያቸው እታገልለታለሁ የሚሉት ብሔር ስም መለየት ብቻ ስለሆነ ከህወሓት ጋር አይወግኑም፤ በአጀንዳ አይስማሙም ብሎ ማሰብ የፖለቲካ ጨቅላነት ነው።   

የታጋች አባት ያሉትን በድጋሚ እናጢን፤ “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን”!!

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial, Right Column Tagged With: jawar massacre, Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule