• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል!

March 2, 2020 11:24 am by Editor 1 Comment

ስለ ዓድዋ ጦርነት አንዳንድ እውነታዎች❗️

ቀን: የካቲት 23, 1888
ቦታ: አድዋ፤ ኢትዮጵያ
አሸናፊው ሀይል: ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በኩል የነበሩ የጦር አዛዦች
አጤ ምኒልክ
እቴጌ ጣይቱ
ተክለ ሀይማኖት
ራስ መኮንን
ራስ ሚካኤል
ራስ መንገሻ
ፊታውራሪ ገበየሁ
ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ
ፊታውራሪ ዳምጠው
ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ
ኒኮላ ሊዮንቴቭ

በጣልያን በኩል የነበሩ የጦር አዛዦች
ኦሬስቴ ባራቴሪ
ቪቶሪዮ ዳቦርሚዳ
ጁሴፔ አሪሞንዲ
ማቲዎ አልቤርቶኒ
ጁሴፔ ኤሊና

በኢትዮጵያ በኩል የተሰለፈ የጦር ብዛት
80,0000 መሳርያ የታጠቅ
20,000 ጦርና ጎራዴ የታጠቀ
8,600 ፈረሰኛ

በጣልያን በኩል የተሰለፈ የጦር ብዛት
24,804 ዘመናዊ መሳርያ የታጠቅ ወታደር
56 ረጅም ርቀት ተወርዋሪ መሳርያዎች

በኢትዮጵያ በኩል የተሰዉ ጦረኞች ቁጥር
3867 የሞቱ
ከ8000 በላይ የቆሰሉ

በጣልያን በኩል የተሰዉ ጦረኞች ቁጥር
6394 የሞቱ
1428 የቆሰሉ
ከ3000 በላይ የተማረኩ

© መልካም 74 Radio

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, Politics, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    March 2, 2020 04:09 pm at 4:09 pm

    የዛሬን አያርገውና የአድዋ ድል ለመላው ጥቁር ህዝብ የድል ጮራ እንደሆነ በየትምህርት ቤቱ እንማር ነበር። አስታውሳለሁ አንድ ጊዜ በአንድ ትምህርት ቤት ግርማ ፍስሃ የተባለ የጀርመን ኗሪ አባቱን ሊጠይቅ ብቅ ይላል። ጊዜው ክረምት ነበረ። እኛም ተማሪዎች የክረትም ትምህርት እንድንማር (ሃገርህን እወቅ) አይነት ነገር ደ/ች መንገሻ ይልማ ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ተኮልኩለናል። ሰብሰብ ብለን በኦሮምኛ እየዘፈንን ስንቀላለድ ደወል ተደወለና ገባን። በቀኑ ግርማ ፍስሃ ተጋባዥ አስተማሪ ነበር። ሰላም ልጆች በማለት ራሱ ካስተዋወቀ በህዋላ ለዛሬ የማስተምራችሁ “አርሙኝ” ከተሰኘ መጽሃፍ ውስጥ ” አልሞትም ብዬ አልዋሽም የተሰኘውን ታሪክ በማንበብ እጀምራለሁ በማለት የአቶ ተማቹንና የወ/ሮ ጽጌረዳን በጣሊያን ወረራ ጀግንነት ማንበብ ጀመረ። በማህሉ ሲቃ ያዘውና ማልቀስ ጀመረ። ክፍሉም ሁሉ አብሮት አለቀሰ። ያ ጊዜ እንደ አሁኑ በዘር ዙሪያ ሰው ያልተሰፈረበት ሁሉም በሰላምና በህብረት የሚኖርበት የመልክዓ ምድር የመማሪያ መጽሃፋችን አርዕስት “አብሮ መኖር በዓለም ዙሪይ” የሚል እንደነበር ትውስ ይለኛል።
    ወደ ዛሬው የዘር ፓለቲካ ስንመለስ ደግሞ ሌቦች ጀግና የሚባሉበት፤ ወንድም እና እህቱን ገድሎ ሰው የሚፎክርበት፤ ለዘሬ፤ ለጎሳዬ፤ ለክልሌ በማለት ሰው ሁሉ በየጎራው የሚፎልልባት፤ በብሄር ነጻነት ስም ባርነት ውስጥ የምንኖርበት በጥቅሉ የደንበር ገተር ጊዜ ላይ እንገኛለን። አድዋ ከሃገሪቱ አራት ማዕዘናት ሃበሾች ተጠራርተው ጠላትን ያሳፈሩበት የድል ጎራ ናት። የአድዋው ድል የጋራ ድል ነበር ነውም። ሼሁ ከመስጊድ፤ ቄሲ ከመንበሩ፤ ገበሬው ከእርሻው፤ ነጋዴውና ሌላውም ተጠራርተው የነጭ መንጋን ያሳፈሩበት የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ጮራ! ታሪክን ሰርተው በታሪክ ውስጥ ያለፉ ጀግኖች ደምና አጥንት ዛሬም በአድዋ ሸለቆና ተራራዎች ይጣራል፤ ይናገራል። የሚሰማ ግን የለም። የክልል ፓለቲካ ያሰከረው የእብድ ክምችት ያፈራች ሃገር። ሲያሳዝን! በአዲስ አበባ ለሰላም ገቡ የተባሉ ጠበንጃ አንጋችና አፋዊ ፓለቲከኞች በለመድት የፓለቲካ የሾኬ ጠለፋ ሰውን ያተራምሳሉ። መማር ማለት እንዲህ ነው። ነጻ እናወጣሃለን የሚባለውን ሰው እሳት ውስጥ እየገፉ መክተት። ዶ/ር አብይም እየቆ መንግሥቱንና አቶ መለስን ለመምሰል ጥቂት ጊዜ የቀረው ይመስላል። በቅርቡ ከብዙ ውጣ ውረድ በህዋላ አንድ የደረስኩበትን መረጃ አልባ የሆነ የራሴን አስተያየት ልስጥ። ሁልጊዜ ኢንጂኒየር ስመኘውን ማን ገደለው በማለት እጠይቅ ነበር። መልሱ ጠ/ሚሩ ናቸው። እንዴት ለሚል። ባፋቸው። ግድቡን በጊዜው ሄደው ከጎበኙ በህዋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እጠቅሳለሁ ” ግድቡ በአስር ዓመት ጊዜም አያልቅ” ይህ ይፋዊና ፌዚያዊ ንግግር ኢንጂኒየሩን ጎድቶታል። በዚህም የተነሳ ራሱን ለማጥፋት ተገዷል። የእኔ ድምዳሜ እሱ ነው። አብይ የማያውቀው የእውቀት ሚዛን የለም። መለፍለፍ ልምድ አድርጎታል። ቃልም ተግባርም በሚዛን ሲሆን መልካም ነው። እንዲሁ ራስን እንደ (chameleon ) ከከባቢ ጋር እየለዋወጡ ቢዘላብድት ዋጋ የለውም። የሚገርመኝ ነገር ባለስልጣኖች እየቆዪ የንጉስ አይነት መልክና ባህሪን ይላበሳሉ። መታመም ነው። ንጉስ ድሮ ቀረ። ይህን አስቀድመው ያዪት እውቁ የወረሂመኖው ሸህ ሁሴን ጅብሪል እንዲህ ብለው ነበር።
    ያምናን ቀን አማሁት ላፌ ለከት የለው፤
    የዘንድሮው መጣ እጅ እግር የሌለው፤
    ቀን ይወጣል ብየ ብጠብቅ ባስጠብቅ፤
    እንኳን ቀን ሊወጣ ጨለማ ነው ጥቅጥቅ፡፡
    ይህ ግጥም የሚያሳየው ትሻልን ትቼ ትብስን እንዲሉ አይነት ነው። ብቻ የጋራ የሆነ ድላችንን እያንቋሸሽን የአንድ ቀን አውሎ ንፋስ የሚደረምሰውን የክልልና የቋንቋ አጥር ስንገነባ ኖረናል ተብለን አፈር ይመለስብናል። አታድርስ ነው። ድንበር ተሻጋሪ ሥራ ከመስራት ላስን አጥቦና አሳንሶ መሞት! እንትፍ ይቅርብኝ!
    አድዋ የጀግኖች የድል ሥፍራ። አድዋ የብዙሃን መቃብር ቦታ። አድዋ የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ጮራ። ኑሪ ለዘላለም ለህያዋን ተስፋ ለወደቁልሽ ሰማእታት የክብር ሥፍራ!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule