• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች

February 17, 2020 09:13 pm by Editor Leave a Comment

በቡራዩ የተከሰተውን ረብሻ አስመልክቶ ቢቢሲና የመንግሥት ሚዲያዎች የተሟላ መረጃ አለማቅረባቸውን የቡራዩ ነዋሪዎች ለጎልጉል ገለጹ። እነሱ እንዳሉት በአንድ መጠነኛ ሆቴል ምረቃ ላይ ለተነሳው ጸብ መነሻው በሽብር ተግባሩ የሚታወቀውና ጃል ማሮ (ኩምሣ ድርባ) የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ፎቶ በጨረታ እንዲሸጥ መቀረቡን ተከትሎ ነው።

ነዋሪዎቹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሲያስረዱ በምረቃው ላይ ጃል ማሮን የሚያወድሱ ሙዚቃዎች በዝተው ነበር። የውዳሴው ሙዚቃ መብዛቱ ከቡራዩና አካባቢው ወይም በተለምዶ የ“ሸዋ” የሚባሉትን ኦሮሞዎች አላስደሰተም። ሙዚቃው ቅይጥ እንዲሆን ቢጠየቅም ሰሚ አልነበረም።

“በዚህ ስሜት ውስጥ እያሉ ነው ጃል መሮ የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ምስል ለጨረታ የቀረበው” ሲሉ በስፍራው የነበሩ ምስክሮች ያረጋግጣሉ። አክለውም “የዚህን ጊዜ ንትርክ ተነሳ። በንትርኩም “ይህ አገር ሻጭ፣ ከሃጂ፣ አሸባሪ፣ ሽፍታ ማን ስለሆነ ነው ፎቶው ለጨረታ የሚቀርበው? የት እናውቀዋለን? ለናንተም አልጠቀመም” በማለት ተቃውሞ ያላቸው ተቆጡ።

“ምክንያቱ በውል ለማይታወቅ ጉዳይ ጫካ ሆኖ ከወያኔ ጋር በማበር አገር የሚወጋ ከሃዲ ፎቶ ለጨረታ መቅረብ የለበትም በሚል አካባቢ ጠቅሰው መሟገት ጀመሩ። ጉዳዩ ከረረና እገሌ ከገሌ ሳይባል እርስ በእርስ መፈናከት ተጀመረ። የዚህን ጊዜ ፖሊስ ጣልቃ ገባ” በወቅቱ በቦታው የነበሩ ለጎልጉል የሰጡት ቃል ነበር።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ አስቀድመው የተፈናከቱት እርስ በርስ መሆኑ እየታወቀ፣ የጸቡ መነሻ የጃል መሮ ፎቶ ጨረታ መቅረብና ከልክ በላይ በዘፋኞቹ መሞገስ መሆኑ እየታወቀ በተጠቀሱት ሚዲያዎች አለመጠቆሙ የቡራዩ ነዋሪዎችን አሳዝኗል።

አዲስ ስታንዳርድና ቢቢሲ አማርኛ ነዋሪነቷ ኖርዌይ የሆነች ሴት ላይ የደረሰውን ፍንከታ አጉልተው ዘገቡ እንጂ በጠርሙስ ጉዳት የደረሰባቸው በርካታ እንደሆኑ የቡራዩ ነዋሪዎች አስረድተዋል። 

ሃዊ ኤች ቀነኒ የምትባለው ይህቺው የኖርዌይ ነዋሪ “በወቅቱ ዘፍነን እየወጣን ነበር። የተጠራው ሰው እየተበተነ ባለበት ወቅት ፖሊሶች ወደ ሆቴሉ መጥተው ኦነግን አሞካሽታችኋል በሚል ነው ድብደባውን የጀመሩት” ስትል ለቢቢሲና ለአዲስ ስታንዳርድ የተናገረችው ሰባራና ያልተሟላ፣ ሃቁን የሸሸገ መሆኑንን በስፍራው የነበሩ ይናገራሉ። አንዳቸውም ሚዲያ ስለ ጃል መሮ ፎቶ ጨረታ ጉዳይ አላነሱም።

ነዋሪዎች የቡራዩ ፖሊስ ጥንቃቄ መርጦ መሸፋፈኑ ሌሎች ሚዲያዎችም ዋናውን ጉዳይ እንዲደብቁት ድጋፍ ማድረጉን በትችት ገልጸዋል። መጠነኛም ቢሆን ሆቴሉ ከወለጋ መጣ የተባለ ሰው እንደሆነም አክለው ተናግረዋል።

የጸቡን መነሻ ያስተዋሉና የተከታተሉት እንደሚሉት ጃል መሮ የሚባለው አሸባሪና ሽፍታ ላይ በኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ የተለያየ አቋም መኖሩን ሲሆን፣ ጉዳዩ የመጪውን ምርጫ ውጤት አመላካች እንደሆነም ጠቁመዋል።

ጃል መሮ መንግሥትና ሕዝብ ላይ ጦርነት ያወጀ፣ የውጪ አገር ዜግነት ያላቸው ገንዘብ በማሰብሰብ የሚመሩት የኦነግ ሸኔ አንድ ጉራጅ መሆኑ ይታወቃል። ዜግነታቸውን መመለስ ስለማይፈልጉ ወደ ውጭ መውጣት የመረጡ ክፍሎች የሚረዱትና የሚመሩት፤ ጦርነት የመረጠ ቡድን በርካታ ንጹሃንን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ መግደሉ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል። 

በኖርዌይ የበርገን ነዋሪዎች እንዳሉት ከዚሁ ከጃል መሮ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ኦሮሞዎች አካባቢና ጎራ በመለየት መነጋገር ካቆሙና የጎሪጥ መተያየት ከጀመሩ ሰንብተዋል። 

በአገር ውስጥ ደግሞ በ“ዲቃላ” የፖለቲካ ጦስ እየታመሰ በሚገኘው ኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ጎራ እየለዩ መከታከት እየተለመደ መጥቷል። በኦሮሞነት ከተመዘገበው ህዝብ ቁጥር ውስጥ እጅግ በርካታ የሆነው የተዳቀለ በመሆኑ በሰሞኑ የ“ዲቃላ” ፖለቲካ ዲስኩር ዙሪያ ይፋ ሆኖ ባይወጣም፤ ትንሽ የማይባል ቁጥር ያለው ሕዝብ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ቁጣውን እየገለጠ ይገኛል።

ከወራት በፊት የኦሮሞ ድርጅቶች እና ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት ሁሉም ተሰብሳቢዎች በሙሉ ድምጽ በወለጋ በአሸባሪነት እየተንቀሳቀሰ በሚገኘው ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ እንዲወሰድ በፊርማ ማረጋገጣቸው ይታወሳል።

ጃል መሮ የተባለው ወንበዴ የመንግሥት ጥቃት በወለጋ በሚደርስበት ወቅት ትግራይ ስለመታየቱ የዓይን ምስክር ነን ያሉ በወቅቱ መናገራቸውን በተለይ በፌስቡክ የተሰራጨ ጉዳይ ነበር።

በውጭ አገር የሚኖሩ ኃይሎች ጃል መሮን የሚደግፉት በዚህችው ሃዊ ቀነኒ በኩል እንደሆነ በስፋት እየታወቀ ሳለ የጃል መሮ ፎቶ ለጨረታ በመቅረቡ ግጭቱ ስለመቀስቀሱ አንድኛውም ሚዲያ ያለመዘገቡ የቡራዩ ነዋሪዎችን ያሳዘነ ብቻ ሳይሆን ጥያቄ የፈጠረም ጉዳይ ሆኗል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule