ኳ! ኳ! ኳ! ይላል፤ በማርያም ደጃፍ - በገብርኤል፤ በጎርጊስ ደጅ - በሩፋኤል፤ በጨርቆስ ደጃፍ - በአማኑኤል፤ በተክልዬ - በሚካኤል፤ ኳ! ኳ! ኳ! እያለ፤ የመጨረሻው ደወል ተደወለ፤ አትንበርከክ በቃ ! ቆመህ የጴጥሮስን ሞት ሙት አለ:: (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የመጨረሻው ደወል !
Right Column - Primary Sidebar
ከጩኸት ወደ ተግባር የሚነገድበት የስደት ማእበል ትውልድ ከየት መጣ?
የውጭ ጠላቶቻችንና የውስጥ ገዢዎቻችን በአንድ ድምጽ የሚሰሩ መሆናቸውን በተደጋጋሚ አይተናል። በጥቃቅን ልዩነቶች ላይ ማተኮሩን እንተወው፤ አስጠቅቶናል፤ አሳፍሮናል፤ አድክሞናል። በገፍ ለሚሰደደውና ለሚዋረደው ብዙ ሚሊየን ወጣት ትውልድ እንደምናስብ አምናለሁ። እምነት፤ ጩኸት፤ ፀሎት አስፈላጊ ቢሆኑም አንገት ቆራጭ ሽብርተኞችን አይከላከሉም። አፋኝ፤ አግላይና ራሱን አገልጋይ የሆነ የመንግሥት ስርዓትን አይለውጡም። ሁለቱንም አብሮና ተባብሮ ለመለወጥ ይቻላል የሚል እምነት አለኝ [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ]። … [Read more...] about ከጩኸት ወደ ተግባር የሚነገድበት የስደት ማእበል ትውልድ ከየት መጣ?
አሜሪካ አይሲስን ለምን ፈጠረችው?
ግብጽ የሃያ አንድ ክርስቲያን ዜጎችዋን በአይሲስ መታረድ ዜና እንደሰማች ዝም ብላ አልተቀመጠችም ነበር። ብሄራዊ የሃዘን ቀንም አላወጀችም። እንዲህ ነበር የሆነው። ከመቅጽበት ተዋጊ አውሮፕላኖችዋን አስነስታ ወደ ሊቢያ ላከቻቸው። የአይሲስ አራጆች የተከማቹበትን ደርና የተሰኘ ስፍራ እያከታተለች በቦምብ ቀጠቀጠችው። ብዙ አራጆች በድብደባው አለቁ። እንደ ግብጽ አጀማመር ቢሆን የሊብያው አይሲስ ክንፍ ድሮ-ድሮ ከምድረ-ገጽ ይጠፋ ነበር። ግና አልሆነም። አሜሪካ ጣልቃ ገባች። ግብጽ የአሜሪካን "ጸረ-ሽብር" ዘመቻ በማገዝዋ ምስጋና ማግኘት ሲገባት በተቃራኒው ተወገዘች። ከጥቂት ድብደባ በኋላ ፔንታጎን ግብጽን አስጠነቀቀ[0]። የኦባማ አተዳደርም ደብደባው በአፋጣኝ እንዲቆም ቀጭን መልእክት ላከ። ይህ ድርጊት ከዚህ ቀደም ስለ አይሲስ አፈጣጠር ኤድዋርድ ስኖደን[1] የለቀቀው ምስጢራዊ መረጃ ጋር … [Read more...] about አሜሪካ አይሲስን ለምን ፈጠረችው?
አልሸባብ አይሲስን ሊቀላቀል ነው
በሶማሊያ የሽብር ተግባራትን በመፈጸም የሚታወቀው አልሸባብ ደመኛና አረመኔውን አይሲስን ሊቀላለቀል መሆኑ ተሰማ፡፡ አገራችንን በተጨማሪ የሽብር ስጋት ውስጥ እነደሚጥላት ተገምቷል፡፡ የሶማሊያን ስፊ ግዛት የሚቆጣጠረው አልሸባብ የማእከላዊ ስልጣኑን ካጣ ወዲህ በደረሰበት ወታደራዊ ኪሳራ የአለም አቀፍ አሸባሪው አልቃይዳ ክንፍ በመሆን እያካሄደ ባለው የደፈጣ ውጊያ ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ርቋት በንጹሃን ደም የታጠበች መንግስት አልባ ጦር ሜዳ ከሆነች ከሁለት ዓስርት አመታት በላይ አስቆጥራለች። ሟቹ አቶ መለስ የቆሰቆሱት የሶማሊያ ችግር እስካሁን አልበረደም፤ የኢትዮጵያን ጦር ጨምሮ ከተለያዩ አፍሪካ ሃገራት የተውጣጡ ወታደሮች የሶማሊያን ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረጉ ያለው ጥረት መና ቀርቶ የእሳቱ ወላፈን ድንበር ተሻግሮ ለዜጎቻቸው ጦስ እስከ መሆን ርቆ የሄደበት አጋጣሚ የሰላም … [Read more...] about አልሸባብ አይሲስን ሊቀላቀል ነው
CREW Condemns the Massacre of Innocent Ethiopians by Extremists
Center for the Rights of Ethiopian women (CREW) strongly condemns the brutal murder of Ethiopian Christians in Libya and the recent xenophobic attacks of Ethiopians and other African migrants in South Africa. Thirty Ethiopians were brutally murdered by ISIS in Libya. Half of them were beheaded at a Libyan shoreline and the other half were shot dead in southern Libya, hundred miles from the shores. The released video showing the mass brutal killing refers to victims as those “belonging to … [Read more...] about CREW Condemns the Massacre of Innocent Ethiopians by Extremists
“እኛን ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው”
አይሲስ በሊቢያ ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን መያዙን ከአይሲስ ያመለጠው ኢትዮጵያዊ ለቪኦኤ ገለጸ፡፡ እርሱንና ሌሎችን በአይሲስ እንዳይወሰዱ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ማስጣላቸውን ተናገረ፡፡ ይኸው ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቀው ወገን እንደተናገረው እኛን ከአይሲሲ ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው፤ በሀገራችን በፍቅር ነው የኖርነው ክርስቲያኖቹን ለይታችሁ አትወስዱም በማለት ሙስሊሞቹ እንደተከራከሩላቸው፤ እንደጮሁላቸው አስረድቷል፡፡ በዚህም ምክንያት እርሱና ሌሎች ላሁኑ ከመሞት ተርፈዋል፤ ከዚህ ወዲህ የሚሆነውን ግን ለመናገር እንደማይችልና ሁሉንም “እግዚአብሔር ነው የሚያውቀው” በማለት በእምነት እየጠበቁ መሆናቸውን ከተሰወረበት ቦታ ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ተናግሯል፡፡ ይኸው ከአይሲስ ያመለጠው ኢትዮጵያዊ ከዚህ በፊት ቤንጋዚ ላይ ከሌላ የትግራይ ተወላጅ ጋር ተይዘው በኤሌክትሪክ … [Read more...] about “እኛን ያዳኑን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ናቸው”
“በሃይማኖት ማስገደድ የለም!”
የፌስቡክ ወዳጃችን Abubeker Siraj ከዚህ በታች ያለውን ጽሁፍ ከመልዕክት ጋር ልከውልናል፤ ሁሉንም እንዳለ አቅርበነዋል፡፡ ለፌስቡክ ወዳጃችን Abubeker Siraj ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ ሰላም እና በረከት ቅኑን መንገድ በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን ጎልግሎች ሆይ! እኔ አንድ አንባቢያቹ ነኝ ከአዲስ አበባ። ፅሁፎቻቹን አነባለው አደንቃለው። ከምንም በላይ አገር ወዳድነታችሁ እና ሚዛናዊነታችሁን ሳላደንቅ አላልፍም። ዛሬ አንዲት ጉዳይ ላወራቹ ፈልጌ ነበር። እሱም አሁን ከዚህ በታች ያለው ሊንክ ላይ የሚገኘው የወንድሜ ኢብኑ ሙነወር (Ibnu Munewor) ፅሁፍ የሚያጠነጥነው ሰሞኑን አይ ኤስ አይ ኤስ በፈፀመው ዘግናኝ ኢ ሰብአዊ ተግባር ላይ ሲሆን በጥቅሉ እኛ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከዚህ አፀያፊ እና ዘግናኝ ተግባር ፍፁም የፀዳን መሆናችንን እና ከክርስቲያን ወገኖቻችን … [Read more...] about “በሃይማኖት ማስገደድ የለም!”
መፍትሔው የአማራ ተራድኦና የዕርቅ ድርጅት አይደለም
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ! … [Read more...] about መፍትሔው የአማራ ተራድኦና የዕርቅ ድርጅት አይደለም
ጨለማው ሳምንት
ወጣት እየሩሳሌም አስፋው እንደወትሮው ቴሌቭዥን ከፍታ እየተመለከተች ነው። ብርቱካንማ ቱታ የለበሱና፣ እጆቻቸው የፍጢኝ የታሰሩ ወጣቶች በአሸባሪዎች ታጅበው ሲጓዙ ያሳያል ቴሌቭዥኑ። ለእርድ ከተሰለፉት ወገኖች ፊት ለፊት ላይ ያለው የእየሩሳሌም ወንድም ነበር። ሌላኛው ወንድሟም ከበስተኋላ ተሰልፏል። እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ፤ ሁለቱም በዚያች ቅጽበት ክቡር ነብሳቸውን በግፈኞች ተነጠቁ። ከሁሉም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ወዳጅ ዘመዶች የነዚህን ወገኖች አስከሬን አግኝተው ለመቅበር እድል እንኳን ባለማግኘታቸው ነው። የሁሉንም ልብ የሚሰብር ክስተት! "ወንድሞቼ ያልፍልኛል ብለው ከቤት እንደወጡ እዚያው በበረሃ ቀሩ።" ትላለች እየሩሳሌም። እትብታቸው የተቀበረባትን ሃገር ለቀው ሲወጡ ጣሊያን ለመግባት ነበር ዕቅዳቸው። አውሮፓን አልመው ቀዬአቸውን ለቅቀው የወጡ እነዚህ ወጣቶች … [Read more...] about ጨለማው ሳምንት
ወያኔ እና የቅድመ-ምርጫ ግምገማው
ወያኔ የአምስት ዓመቱ "የዕድገት እና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ" እንዲሁም የዐባይ ግድብ ግንባታ እንዳልተሳካለት አመነ፣ በመጭው ምርጫም የሚያሰጋኝ የድርጅትም ሆነ የግለሰብም ተወዳዳዳሪ የለኝም አለ የትግሬ-ወያኔ መራሹ ዘረኛ አገር እና ትውልድ አጥፊ ቡድን፣ መጭው የይስሙላ ምርጫ ሊያስከትል የሚችለውን ሕዝባዊ ቁጣ እና እምቢተኝነት በከፍተኛ ደረጃ በመፍራት፣ ሊነሣ የሚችለውን ሕዝባዊ አመፅ በወያኔ ፍላጎት ሥር ለማዋል እንዲቻል፣ አባላቱን በመከፋፈል፣ ሰሞኑን በከፍተኛ ደረጃ የተያዘ ጥብቅ ሚሥጢራዊ ግምገማ እና ውይይት ማድረጉን የታመኑ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ውስጥ-ዐወቅ የመረጃ ምንጮች አረጋግጠዋል። የሕወሓት/ኢሕአዴግ አባል በሆኑ እና ለወያኔ ታማኝ የሆኑ የየድርጅቶቹ አባሎች ተሣታፊ የሆኑበት ለበርካታ ቀኖች በተከታታይ ግምገማ እና ውይይት የተደረገባቸው … [Read more...] about ወያኔ እና የቅድመ-ምርጫ ግምገማው










