• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አልሸባብ አይሲስን ሊቀላቀል ነው

April 27, 2015 07:40 am by Editor Leave a Comment

በሶማሊያ የሽብር ተግባራትን በመፈጸም የሚታወቀው አልሸባብ ደመኛና አረመኔውን አይሲስን ሊቀላለቀል መሆኑ ተሰማ፡፡ አገራችንን በተጨማሪ የሽብር ስጋት ውስጥ እነደሚጥላት ተገምቷል፡፡

የሶማሊያን ስፊ ግዛት የሚቆጣጠረው አልሸባብ የማእከላዊ ስልጣኑን ካጣ ወዲህ በደረሰበት ወታደራዊ ኪሳራ የአለም አቀፍ አሸባሪው አልቃይዳ ክንፍ በመሆን እያካሄደ ባለው የደፈጣ ውጊያ ሶማሊያ ሰላምና መረጋጋት ርቋት በንጹሃን ደም የታጠበች መንግስት አልባ ጦር ሜዳ ከሆነች ከሁለት ዓስርት አመታት በላይ አስቆጥራለች።

ሟቹ አቶ መለስ የቆሰቆሱት የሶማሊያ ችግር እስካሁን አልበረደም፤ የኢትዮጵያን ጦር ጨምሮ ከተለያዩ አፍሪካ ሃገራት የተውጣጡ ወታደሮች የሶማሊያን ሰላምና ጸጥታ ለማስከበር እያደረጉ ያለው ጥረት መና ቀርቶ የእሳቱ ወላፈን ድንበር ተሻግሮ ለዜጎቻቸው ጦስ እስከ መሆን ርቆ የሄደበት አጋጣሚ የሰላም አስከባሪ ሃገራቱን ዜጎች በሰላም ወጥቶ የመግባት ደኅንነት ስጋት ውስጥ ጥሎታል።

ሶማሊያ ውስጥ ወታደሮቻቸውን ካሰለፉ ሃገራት መሃከል በዩጋንዳ እና ኬንያ ዜጎች ላይ ይህ እስላማዊ ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን “አልሸባብ” ድንበር ተሻግሮ በንጹሃን ላይ የፈፀመው ዘግናኝ ድርጊት ሳይጠቀስ የማይታለፍ ነው።

አልቃይዳን በይፋ ከተቀላቀለ ወዲህ ከአለም ህዝብ የተገለለው አልሸባብ አለም አቀፋዊ ትኩረትን ለመሳብ በአሜሪካ ላይ ጥቃት ለመፈጸም እቅድ እንዳለው በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው የዛቻ መግለጫዎቹ ቡደኑ ሃያል ነን ለሚሉ ሃገራት ሳይቀር ራስ ምታት ሆኗባቸዋል።

በኢህአዴግ ድጋፍ ወፌ ቆመ እያለ የሚገኘውን ሞቃዲሾ ላይ የተገደበ በአምሳሉ የፈጠረውን ስርዓት ባለስልጣናት አልሸባብ ሲሻው በሽብር ጥቃት በመግደል አሊያም እርስ በርሳቸው እንዲናቆሩ ጀሌዎቹን አሾልኮ በማስገባት ከሚፈጽመው ደባ ባሻገር ጊዜ እየጠበቀ ከርቀት በሚያስወነጭፋቸው የከባድ ጦር መሳሪያ አረር የቤተመንግስቱን ሰላም መቅኖ በማሳጣት ሶማሊያ ውስጥ  አለ የሚባለውን መንግስት ህግና ስርዓት ትርጉም አልባ አድርጎታል።

የሶማሊያ አለመረጋጋት አገርሽቶ ለጎረቤት ሃገራት ጦስ እየሆነ በመጣበት በአሁኑ ጊዜ አልሸባብ የሽብር ስትራቴጂውን በመቀየር በቅርቡ ኬንያ ላይ በአንድ ዩኒቨርስቲ ማዕከል በክርስትና እምነት ተከታይ ተማሪዎች ላይ የፈፀመውን አረመኔያዊ ድርጊት በሌሎች ላይ አጠናክሮ ለመቀጠል አለምአቀፍ አሸባሪ ቡድን ከሆነው አይሲስ ጋር በመዋሃድ እንደ ሊቢያ ቢጤዎቹ የሰው ልጅን አንገት በካራ ለማረድ የነደፈው እቀድ በአልሸባብ የአመራር አባላት መካከል ንትርክን ፈጥሮ መሰንበቱ ይነገራል። አልሸባብ ከቡድኑ ጋር ለመዋህድ ያቀረበው ጥያቄ ወታደራዊ የሎጀስቲክ አሊያም የሰው ሃይል ድጋፍ ከዚህ ከአረመኔ አይሲስ ለማግኘት እያደረገ ያለው ጥረት የአልሸባብን ወታደራዊ አቅም እየተመናመነ መምጣት በግልጽ የሚያሳይ ጣረሞት ነው በማት አንዳንዶች ይገልጹታል፡፡ በአንጻሩ ሌሎች አልሸባብ አለምአቀፋዊ አቅሙን እያጎለበት የመጣውን አረመኔ አይሲስ ተዋጊዎች ሶማሌያ በማስገባት ኢትዮጵያን በማተራመስ ለመበቀል የታቀደ ስትራቴጂ ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን ይገልጻሉ።

በሃይማኖት ሽፋን ምዕራብ አፍሪካ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ቦኮ ሃራም በአካባቢው ሃገራት መንግስታት ወታደሮች በቅንጅት የከፈቱበትን ጦርነት መቋቋም ሲሳነው የቦኮ ሃራም መሪ “ሼካው” ኢራቅ እና ሶሪያ ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የዚህ ራሱን እስላማዊ መንግስት ብሎ የሚጠራው አይሲስ አሸባሪ ቡድን አካል መሆኑን መግለጹ ይታወሳል። አልሸባብ ሰሞኑን እያሰማ ያለው ጩኸት ቡድኑን ለሁለት መክፈሉን ቢሰማም ይህ አጋጣሚ በአባላቱ መሃከል የተፈጠረው ልዩነት ሰፍቶ ለአልሸባብ ከሶማሊያ ምደር መጥፊያው ምክንያት ካልሆነ የ አይሲስ ዱካ ሶማሊያ ውስጥ ከታየ ኢራቅ፣ ሶሪያንና ሊቢያን እያተራመስ የሚገኘው ሰይጣናዊ ሃይል ለሃገራችን ሰላምና መረጋጋት በእንቀርት ላይ ጆሮ ደግፍ ከመሆን ሊያግደው የሚችል ምድራዊ ኃይል እንደሌለ በበርካቶች ዘንድ የሚታመን ሐቅ እየሆነ መጥቷል።

ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች!

(Ethiopian Hagere Jed Bewadi ለጎልጉል የላኩት)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule