• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጨለማው ሳምንት

April 20, 2015 01:02 am by Editor Leave a Comment

ወጣት እየሩሳሌም አስፋው እንደወትሮው ቴሌቭዥን ከፍታ እየተመለከተች ነው። ብርቱካንማ ቱታ የለበሱና፣ እጆቻቸው የፍጢኝ የታሰሩ ወጣቶች በአሸባሪዎች ታጅበው ሲጓዙ ያሳያል ቴሌቭዥኑ። ለእርድ ከተሰለፉት ወገኖች ፊት ለፊት ላይ ያለው የእየሩሳሌም ወንድም ነበር። ሌላኛው ወንድሟም ከበስተኋላ ተሰልፏል። እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ፤ ሁለቱም በዚያች ቅጽበት ክቡር ነብሳቸውን በግፈኞች ተነጠቁ። ከሁሉም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ወዳጅ ዘመዶች የነዚህን ወገኖች አስከሬን አግኝተው ለመቅበር እድል እንኳን ባለማግኘታቸው ነው። የሁሉንም ልብ የሚሰብር ክስተት!

“ወንድሞቼ ያልፍልኛል ብለው ከቤት እንደወጡ እዚያው በበረሃ ቀሩ።” ትላለች እየሩሳሌም። እትብታቸው የተቀበረባትን ሃገር ለቀው ሲወጡ ጣሊያን ለመግባት ነበር ዕቅዳቸው። አውሮፓን አልመው ቀዬአቸውን ለቅቀው የወጡ እነዚህ ወጣቶች ህልማቸው እውን ሊሆን አልቻለም። ከሌሎች 28 ወገኖቻችንን ጋር ፍጹም ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ህይወታቸው አለፈች። ‎ISIS የተባሉ ጨካኞች ሲያርዷቸው በቪደዮ አሳዩን።

የሳምንቱ ሃዘን እጥፍ ድርብ ነው። ኢትዮጵያዊ ላይ ያነጣጠረ እስከሚመስል ድረስ ነው እየተካሄደ ያለው። ብሔራዊ መንግስት ስለሌለን ብሄራዊ ውርደታችን አላቆመም።  ከ 700 በላይ ስደተኞችን ይዛ ወደ አውሮፓ ትጓዝ የነበረች ጀልባም በዚህ ሳምንት ነበር በሜዲትራኒያን ባህር ላይ የሰመጠችው። ቁጥሩን ለማረጋገጥ ባይቻልም፣ ከሞቱት ገሚሱ ኢትዮጵያውን እንደሆኑ ከወደ ጣልያን የሚመጣው መረጃ ይጠቁማል።

በደቡብ አፍሪካ ዉስጥ ያሉ ኢትዮጵያውያንም በቁም ሲቃጠሉ እና ሲገደሉ እያየን ነው። በተለይ ደርባን ውስጥ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እስካሁንዋ ደቂቃ በፍርሃት ቤታቸውን ዘግተው ተቀምጠዋል።

የመን ያሉ ወገኖቻችንም ምጥ ላይ ናቸው። የመን ያሉ ኢትዮጵታውያን ቁጥር ከምናስበው በላይ መሆኑ እጅግ ይረብሻል። አለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት አይ.ኦ..ኤም እንደሚለው ከሆነ በየመን ያሉ ኢትዮጵያዊያን ቁጥር አንድ ሚልዮን ይጠጋል። ሁሉም በጭንቅ ላይ ናቸው። ያለመታደል ሆኖ የሚቆረቆርላቸው መንግስት ግን አላገኙም። ልብ በሉ ከአንድ ሚሊዮን ዜጋ፤ በስልጣን ላይ ያለው መንግስታችን 30 ዜጎቼን በጅቡቲ አድርጌ ወደ ሀገር ቤት አስገባሁ ሲል አብስሮልናል። በእርግጥ ይህ ጉዳይ በሊቢያው ክስተት ከሰጡት ምላሽ አይብስም። የ ISIS አሸባሪዎች ኢዮጵያውያንን አረድን ባሉ ግዜ “ጉዳዩን እናጣራለን” ሲሉ ነበር የቀልዱብንል። ከዚህ ድርጊት የባሰ ምን ሊመጣ ይችል ይሆን? በበረሃ የወደቀን ወገን፣ የትና በምን አግኝተው ነው የሚመረምሩት። አለሁ ባይ አካል ስለሌለን የተረሳን እና የተዋረድን ህዝቦች ነን።

እንደሌሎች ሀገሮች በአለማቀፍ መድረክ የሚከራከርልን አካል ስለሌለን የጥቃት ሰለባ እንድንሆን ተደርጓል። ሃገራችንም ጥርስ የገባች ሃገር ሆናለች።

ይህንን ስረዓት እየሸሹ እየሄዱ አውሬ የሚበላቸውና በረሃ ወድቀው የሚቀሩትን ወገኖች ቤቱ ይቁጠረው። በሳውዲ ጀምሮ የመን ተከትሎ ከዚያም በደቡብ አፍሪካ እና በሊቢያ፣ በደቡብ ሱዳን እና በተለያዩ አረብ ሃገሮች በቃላት መግለጽ የማይቻል ድርጊት እየተፈጸመብን ነውና ሁላችንንም እንቅልፍ የሚነሳ ጉዳይ ነው።

ሰው ወድዶ አይሰደድም። ተስፋ የቆረጠ ህዝብ ይሰደዳል፣ የተገፋ ህዝብ ይሰደዳል፣ ፍትህ ያጣ ህዝብ ይሰደዳል፣ የተራበ ህዝብ ይሰደዳል። ስደት እስካለ መከራውም ይኖራል።

የሃዘን ቀን ቢታወጅልንም፣ ባይታወጅልንም ከንፈር ከመምጠጥ ያለፈ ፋይዳ ሊኖረው አይችልም። በዚህ ጨለማ ሳምንትም ሆነ ከዚያ በፊት በሆነው ነገር ሁሉ ልባችን ተነክቷል። ኢትዮጵያውያን ሁሉ በጠለቀ የሃዘን ስሜት ውስጥ ነን።

በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ አሜሪካዊትዋ ባለስልጣን፣ ዌንዲ ሼርማን መንግስታችን ስኬትን እያስመዘገበ እንደሆነ በዚሁ ሳምንት ነበር ያበሰረችን። ዜጋው ሁሉ ተስፋ ቆርጦ እየተሰደደ በየበረሃው መውደቁን ይሆን ዌንዲ እንደ ስኬት የቆጠረችው?

የማያልፍ የለምና ይህም ጊዜ ያልፋል። እስከዚያው ግን ወዳጅ ዘመዳቸውን ያጡ ሁሉ ፈጣሪ ብርታቱን ይስጣቸው። መፍትሄው ታድያ ፍትሃዊ ስርዓትን እና ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍልን መፍጠር ሲቻል ብቻ ነው። ይህ ሲሆን የስደት ምንጩ ይደርቃል።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule