ባለፈው ሳምንት ጌታቸው ረዳ ከአልጃዚራ ቴሌቭዥን ጋዜጠኛ ጋር ተጋፍጦ ነበር። አንድ ጥያቄ ቀረበለት። "በራሳችሁ የምትተማማኑ ከሆነ ለምን የተባበሩት መንግስታት ታዛቢዎች እንዳይገቡ ከለከላችሁ?" ሚኒስትር ጌታቸውም። "የተባበሩት መንግስታት አያስፈልገንም። እኛው ራሳችን ከህዝቡ ጋር እንነጋገራለን።" ሲል ነበር የድፍረት መልስ የሰጠው። ይህ የትእቢት መልስ ለጋዜጠኛዋ እንግዳ አይሆንም፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ግልጽ ነበር። እነሆ ከህዝብ ጋር ንግግር መጀመራቸውን እያሳዩን ነው። እንደ ፋሺሽት ጣልያን በከባድ መሳርያ ሕዝብን ለመደብደብ ቆርጠው መነሳታቸውን ተመልከቱ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማእረግ ሃገሪቱን የጠቆጣጠሩት ዶ/ር ደብረጽዮን በዛሬው እለት በፌስቡክ ገጻቸው ላይ አንድ የጦር አዋጅ አስነብበውናል። በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የታወጀ ጦርነት። የጦርነት መግለጫው … [Read more...] about ህወሃት በሕዝብ ላይ የደገሰው በዶ/ር ደብረጽዮን አንደበት
Right Column - Primary Sidebar
The TPLF on retreat
* (Woyane - the cornered Beast.) This time it looks like we have found the formula to start building a harmonious Ethiopia. The Tigrai Woyane Liberation Front that refused to grow up is on retreat mode. The Forces arrayed against the gangster organization are now speaking in one voice. Will TPLF elite wave the white flag without further bloodshed is in everyone's mind. The question is not easy to answer. From experience, the most corrupt and ethnic based regimes come out bloodied if lucky; but … [Read more...] about The TPLF on retreat
በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በትግሬ-ወያኔ ግፍ የተጨፈጨፉትን እንድናውቃቸውና እንድንዘክራቸው!
ዘረኛው የትግሬ ወያኔ የወልቃይት ጠገዴን የማንነት ጥያቄ ደግፈው በወጡ የባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በግፍ የገደላቸው ወገኖቻችን ዝርዝር በከፊል። «የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ፣ የእኛም የዐማራነት ጥያቄ ነው፣» ብለው እሑድ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓም ላይ በባሕርዳር ከተማ፣ በሰላማዊ መንገድ ድምፃቸውን ለማሰማት በወጡ ዐማሮች ላይ፣ የትግሬ ወያኔ ዘረኛ ቡድን በርካታ፣ ሩቅ አሳቢ፣ ለሥራ የጓጉ፣ ላገርና ለወገን ታላቅ ተስፋ ሰንቅው የነበሩ የአያሌ ወጣቶችን ሕይዎት በግፍ ነጥቋል። በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወያኔ ከገደላቸው በርካታ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች መካከል ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በውስጥ የመረጃ ምንጮቻችን የከፊሎቹን አገኝቷል። ከሰንጠረዡ ለመረዳት እንደሚቻለው፣ በግፍ ከተገደሉትና ዝርዝራቸውን ማወቅ ከተቻለው አርባ ዘጠኝ(49) ሰዎች ውስጥ፣ ዕድሜአቸው ሰላሳና ከዚያም … [Read more...] about በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በትግሬ-ወያኔ ግፍ የተጨፈጨፉትን እንድናውቃቸውና እንድንዘክራቸው!
ለመሆኑ አማራ ማነው?
ዛሬ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ መንግሥት ዐማራ በተባለው ኅብረተ-ሰብ ላይ ብዙ ግፍና ዐመፅ እንደፈጸመና እንዳስፈጸመ በገፍ ይነገራል። በኅብረተሰቡ ላይ ተፈጸሙ ከተባሉት ድርጊቶች አብዛኞቹ በሥዕል የተቀረጹ፣ ለሰው መብት በቆሙ ባስተማማኝ ብሔራዊና ዓለም-ዐቀፍ ድርጅቶች ከነማስረጃቸው የተጠናቀሩ፣ እሙን በሆኑ ያይን ምስክሮች የተደገፉ ስለሆኑ ማስተባበሉ ከመደናቈርና የአተካራ ግብግብ ከመግጠም ውጭ ሌላ ፋይዳ ያለው አይመስለኝም። የግፎቹ ኢሰብኣዊነትና የፈጻሚዎቻቸውም አውሬነት ለሚሰማ ሁሉ ከመዘግነን አልፎ፣ ሰው ሁኖ መፈጠሩን ራሱን የሚያስጠላ ከመሆኑ የተነሣ፣ ልቦና ያለው ተመልካችም ሆነ ሰሚ፣ መንግሥት ነን ባዮቹ የወያኔ ገዢዎች በጀርመንና በኢጣሊያን ምድር ከታዩት ከናዚና ከፋሽስት መንግሥታት መሪዎች በምን ይለያሉ ብሎ ለመጠየቅ ይገደዳል። በበኩሌ ጥላቻው ከየት መጣ ብዬ አውጥቼ … [Read more...] about ለመሆኑ አማራ ማነው?
የአማራውን ሕዝብ ሁለገብ የሕልውና ትግል ለማገዝ መደራጀት ያስፈልጋል!
ከኃይለገብርኤል አያሌው የቀድሞው የመዐሕድ አመራር አባል ለአመታት በሕዝባችን ላይ ተከማችቶ የቆየው የጭቆና አገዛዝ የፈጠረው ምሬትና ቁጣ በመላው ሃገሪቱ መፈንዳት ጀምሮል። በተለይም በኦሮምያ ባለፉት ተከታታይ ወራት የቀጠለው ሰላማዊ ተቃውሞ የአያሌ ወገኖቻችንን ህይወት እየቀጠፈ ቀጥሏል። ይህም ትግል የኦሮሞ ህዝብ ትግል ተብሎ በሃገር ወስጥና በውጭ ሚድያዎች እውቅና አግኝቷል። በተለያዩ ልዩነቶች ተብታትኖ የኖረውን የኦሮሞ ፖለቲካ ሃይሎችና ሊህቃንን አቀናጅቶ ሃገር ውስጥ ያለውን ትግል ማዕክል ያደረገ እንቅስቃሴ ሲደረግ ይታያል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የአማራውን ሕዝብ ሁለገብ የሕልውና ትግል ለማገዝ መደራጀት ያስፈልጋል!
ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ወይም “ጉማሬው” ዋናተኛ
አቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ከተጫነባቸው በኋላ በUN ኢትዮጵያን ወክሎ የመቀመጥ ስልጣናቸው ቀረና ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ። እድገት ወይም ውርደት (promotion ወይም demotion) ሳንል፣ ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ እንላለን። አቶ ዠ የሃገሪቱ የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው ተሾሙ። እንግዲህ “ፕሬዚደንት” የሚለው ቃል እስካለ ድረስ፣ ሹመቱ፣ ማዕረጉ ትልቅ ነው ተብሎ እንዲታሰብ የአቶ ዠ መልካም ፈቃድ ነው እንላለን። የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙበት ጊዜ ደግሞ እንዳጋጣሚ ሆኑ የኦሎምፒክ ውድድር የተቃረበበት ጊዜ ነበር። ዠ አዲሱ ቢሮአቸው ሆነው አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው። ሃገራቸውን በኦሎምፒክ መወከል። የሃገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ በኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ ተገኝቶ ማውለብለብ...። እንዴት ያለ ድንቅ ሃሳብ ሲሉ አሰቡ አቶ ዠ። እንግዲህ መሰደብ፣ መዋረድ፣ መሰደድ፣ … [Read more...] about ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ወይም “ጉማሬው” ዋናተኛ
የህዝባችንን የትግል ፈር እንከተል!!
ለወራት በኦሮሞ ወጣቶች ሲካሄድ የቆየው ለዴሞክራሲ የሚደረገው ህዝባዊ ትግል ሳያቋርጥና እየሰፋም እየሄደ ባለበት በአሁኑ ወቅት ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እየደጋገሙ ሲታገሉለት የቆየው የህዝቦች ወንድማማችነትና የትግል አንድነት ጥያቄም ባለፉት ሳምንታት በአማራውና በኦሮሞ ክልሎች በሚካሄዱት ሰላማዊና ህዝባዊ ትግሎች አማካኝነት ስር እየሰደደ መሆኑን እየታዘብን ነው፡፡ በዚያው ልክ ደግሞ በትግሉ ማየልና መስፋት ብርክ የያዛቸው የወያኔ/ ኢህአዴግ መሪዎች ህዝቡ በሰላማዊ መንገድ ለሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ለመስጠት የሚሞክሩት አጸፋ በለየለት ጸረ ህዝብ አመጽ መሰማራት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ በዚህ መልክ ባለፉት ወራት በኦሮሞ ታጋዮች ላይ ያወረዱትና በመቶ የሚቆጠሩ ንጹህ ዜጎችን መግደልና በሽህ የሚቆጠሩ ሌሎችን ለእስር መዳረግ ሳይበቃቸው አሁን ደግሞ በኦሮሞም በአማራም ታጋዮች ላይ ይህንኑ … [Read more...] about የህዝባችንን የትግል ፈር እንከተል!!
የትግሬዎች መንግሥት አወዳደቁና ክፋቱ!
ባሁን ሰዓት፤ በገዥነት ሕልሙ እየተንሳፈፈ ካለው የትግሬዎች ቡድን በስተቀር፤ ኢትዮጵያን አደጋ ላይ የጣላት ይሄው ቡድን፤ የውድቀት አፋፉ ላይ መሆኑ ለሁላችን ግልጽ ነው። አሁን ካለንበት ሰዓት እስከመጨረሻው ውድቀቱ ያለው ጊዜ ግን፤ በጣም የከፋና የተመሰቃቀለ ነው። ይህ የሚሆነው፤ ከፊል በዚህ ወራሪ ቡድን ተግባር ሲሆን፤ ከፊሉ ደግሞ በኛው በታጋዩ ክፍል ያለነው ለዚህ ውድቀት በማድረግና ባለማድረግ ላይባለው ሂደታችን ነው። በተጨማሪ ደግሞ፤ የሃያ አምስት ዓመት የዚህ ቡድን ፀረ-ኢትዮጵያ አገዛዝ፤ ሀገራችንን ለከፋ ወደፊት አዘጋጅቷታል። ሀቁን ተቀብለን ከአሁኑ መደረግ ያለበትን ካላደረግን፤ በኋላ ይሄን ብናደርግ ኖሮ ብለን የመቆጫ ሰዓት አናገኝም፤ ያኔ ሁኔታውን አንገዛውምና! ይህ ወራሪ ቡድን፤ የመጨረሻ እስትንፋሱን የሚያወጣው በቃሬዛ ነው።ሕዝቡ አቸናፊ ሆኖ እንደሚወጣ ምንም ዓይነት … [Read more...] about የትግሬዎች መንግሥት አወዳደቁና ክፋቱ!
በሆላንድ የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ
A Breakthrough agreement between ODF and Patriotic G7
Memorandum of Understanding (MoU) Oromo Democratic Front (ODF) and Patriotic Ginbot 7 (PG7) August 11, 2016 After several candid discussions and careful considerations of the current political, social, economic and humanitarian situations in Ethiopia, and all the damages caused by successive regimes and the TPLF/EPRDF regime in particular on the welfare and national interests of the peoples of Ethiopia and the security and sovereignty of our country, the ODF and PG7 have made important … [Read more...] about A Breakthrough agreement between ODF and Patriotic G7










