የትግሬዎች ነፃአውጪ ግንባር በዘገምታ የመቃብር ጉዞውን ጀምሯል። ሕዝቡ በያለበት ትግሉን አጧጡፏል። የውጭ መንግሥታትም ጥቅማቸውን የሚያስጠብቅላቸውን ወገን ለመለየት ጎራ ይዘው እያዳመጡነው። በግብግቡ ብዙ ወገናችን እያለቀ ነው። ይህ ሆነ ያ፤ አሁን ባለንበት የፖለቲካ ሀቅ፤ ኳሷ ያለችው በታጋዩ ሕዝብ እጅ ነው። የትግሬዎች ነፃአውጪ ግንባር፤ በመላ ሀገሪቱ መግዛት አቅቶት፤ ሀገራችን ያለ መሪ ልትሆን አንድ ሐሙስ ቀርቷታል። በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል፤ ሕዝቡ ካሁን በኋላ በዚህ ዘረኛ ግንባር ሥር አልኖርም ብሎ አምጿል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ኳሷ ያለችው በታጋዩ ሕዝብ እጅ ነው።
Right Column - Primary Sidebar
The struggle toward freedom reached its tipping point?!
When I heard that EPRDF’s Executive Committee held an extraordinary meeting that aimed at addressing the current stalemate, I had mixed feelings. In one hand, I thought for a brief moment, the party may carryout a genuine introspection, assess the situation objectively;most importantly, read the writing on the wall, and respond accordingly. On the other hand, knowing TPLF for more than two decades, I expected some dramas too. Well, they didn’t disappoint! Rather than admitting mistakes, taking … [Read more...] about The struggle toward freedom reached its tipping point?!
የቂሊንጦ ወኅኒ ቤት ቃጠሎ ጉዳይ…
በምርጫ 1997 ማግስት የአደባባይ አመፆች ተበራክተው ነበር፡፡ በጥቅምት 24፣ 1998 አዲስ አበባ በሕዝባዊ አመፅ ስትናወጥ፣ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ውስጥም ሊሰጠው ይገባው የነበረውን ያክል ትኩረት ሳያገኝ ያለፈ ትራጄዲ ተከስቶ ነበር፡፡ በወቅቱ እልፍ በኦ.ነ.ግ. ሥም ተወንጅለው የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች የቃሊቲ ግቢ ውስጥ ታጉረው ነበር፡፡ ታዲያ ግቢው ውስጥ በተፈጠረው ግርግር ‹ሊያመልጡ ሞክረዋል› በሚል 163 የሚደርሱ ታራሚዎች በተተኮሰባቸው ጥይት ሕይወታቸውን አጥተው ነበር፤ መንግሥት የሟቾቹ ቁጥር ዐሥር እንኳን እንደሚሞላ አላመነም ነበር፡፡ ‹ሻዕቢያ› በቂሊንጦ እና ቃሊቲ ወኅኒ ቤቶች እጅግ ዝነኛ ሥም ነው፡፡ ‹ሻዕቢያ› በሚባል ቅፅል ሥም የሚጠራው የዋርድያዎች ኃላፊ፣ በቂሊንጦ የሚገኙ ተመላላሽ እስረኞች በፍርሐት ይርዱለታል፡፡ ‹ሻዕቢያ› ከ1998ቱ የቃሊቲ እስረኞች እልቂት ጋር … [Read more...] about የቂሊንጦ ወኅኒ ቤት ቃጠሎ ጉዳይ…
ከሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የተሰጠ የነፍስ አድን ጥሪ!
የተከበርከውና ጀግናው የዐማራ ሕዝብ ሆይ! የትግሬ ወያኔ አገዛዝ «ዐማራውን አከርካሪውን ሰብረነዋል»፣ «ዐማራው ላይመለስ ገድለን ቀብረነዋል» በማለት ይሳለቅብሃል። በእርግጥም ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮችን ገድሎ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን ደግሞ አሰድዶ ከመኖሪያ ቀያቸው አፈናቅሏል። ሆኖም ግን ከሞቱት በላይ፣ ካሉት በታች ሆነህ የምትኖረው የቀረኸው ዐማራ፣ ከገባህበት የቁም መቃብር ለመውጣት ዘወትር ትግልህን እንዳላቋረጥክ እኛ አብረንህ የምንታገለው ልጆችህ ቀዳሚ ምሥክሮችህ ነን። በተለይም ከሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ መግነዝህን ቀደህ እና በጣጥሰህ፣ የተጫነብህን የመቃብር ድንጋይ እና አፈር ፈነቃቅለህ ከፈጽሞ ጥፋት ራስክን ለማዳን እያደረግኸው ላለው ተጋድሎ እና የጀግንነት ተግባር ያለን አድናቆት እና አክብሮት እጅግ ከፍ ያለ ነው። … [Read more...] about ከሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የተሰጠ የነፍስ አድን ጥሪ!
ሕዝቤን ልቀቅ!
አሁን በሥልጣን ላይ ያለው የኢትዮጵያ አገዛዝ (የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ሕ.ወ.ሃ.ት.) ከ25 ዓመታት በፊት የመንግሥት በትረ ሥልጣንን እንደ ፈረኦን ከጨበጠ ማግሥት አንስቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ቀዳሚ ዒላማው በማድረግ የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ተጥሶ መንበሩ ላይ የተቀመጠ ፓትሪያርክ በህይወት እያለ ያለውን ከመንበሩ በማባረርና በማሳደድ በምትኩ ከራሱ ጎሳ መርጦ ፖትሪያርክ አድርጎ ሾመ። ይህ የፖትሪያርክ ሹመት ቀኖናን ቤተ ክርስቲያንን ከመጣስ ባለፈ ፖለቲካዊና ከፖለቲካም የከፋው የዘረኝነት ፖለቲካን (ethnocratic politics) የተከተለ ስለነበር በተቀረው የአገዛዝዙ የዘረኛ መንግሥታዊ መዋቅሮች እንደረደረገው ሁሉ በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥም የዘረኝነት መዋቅር እያደገ ሄዶ ለወደፊት ቤተ ክርስቲያኗንም ሆነ አጠቃላይ ሃገሪቱን ለከፋ አደጋ ያጋልጣል በሚል … [Read more...] about ሕዝቤን ልቀቅ!
የሕወሃት ብጥብጥ እና ሽሽት- ከውስጥ አዋቂ ምንጭ
ሕዝባዊ አመጹ ያመጣውን ቀውስ ተከትሎ በህወሃት ከፍተኛ አመራር ውስጥ ከፍተኛ መበጣበጥ እና የርስ-በርስ ፍጥጫ መከሰቱን ከታመነ የውስጥ አዋቂ ምንጭ መረጃ ደርሶናል። "አመራሩ ክፉኛ ከመከፋፈሉ የተነሳም የርስበርሱ ችግራቸው ላይ ተወጥረዋል" ይላል መረጃው። ቀንደኞቹ የህወሃት አባላት ስርዓቱ እንዳበቃለት ስለተገነዘቡ ንብረት እና ልጆቻቸውን በማሸሽ ላይ ናቸው። ሕዝቡ ሁሉ እንደተፋቸው በግልጽ እየነገራቸው ስለተገነዘቡ፤ የህወሃት የደህንነት አባላት ሕዝቡን ትተው የራሳቸውን ሰራዊት እና ፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሰልሉ ተነግሯቸዋል። "ተጠርጣሪ" የኦህዴድ እና ብአዴን አባላት በነዚህ ሰላዮች ስለተከበቡ በፍርሃት መወጠራቸውን ከራሳቸው አንደበት እየተሰማ ነው። የርስበርስ ውጥረቱ የተከሰተው ወቅታዊ ችግሩን እንዴት እንፍታ በሚለው ሃሳብ ላይ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በሙሉ በመጥራት … [Read more...] about የሕወሃት ብጥብጥ እና ሽሽት- ከውስጥ አዋቂ ምንጭ
«AmOr!» «አሞር!»
ወደ ዋናው ርዕሴ ከመግባቴ በፊት በቅድሚያ በወያኔ ጥይት በቅርቡ በግፍ ለረገፉት የአገራችን ጀግና ወጣቶች ጥልቅ የሆነ ሀዘኔን እየገለጽኩ፤ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው ፍትህ፤ ዲሞክራሲና ነፃነት ናፋቂው የኢትዮጵያ ህዝብ እግዚአብሔር መጽናናቱን እንዲሰጠው ከልብ እመኛለሁ፡፡ በጉልበት በሚገዙ አምባገነኖች ስር ያለች አገር የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ከጦር ኃይላቸው ባላነሰ ሁኔታ የሚተማመኑበት ስርአታቸውን ይዞ ካቆመው አንዱ ምሰሶ ነው ማለት ይቻላል፡፡ የወያኔንም ስርአት እና ስልጣን ከተሸከሙት ከአምስት ያልበለጡ ምሰሶዎች (the supporting/bearing wall)ውስጥ ይሄ የከፋፍለህ ግዛ ምሰሶ አንዱ ነው፡፡ ሌሎቹ ምሰሶዎች በአጭሩ፦ 1)የጦር ኃይሉ፤ ደህንነቱና ካድሬዎቹ 2)ኤኮኖሚው-ያከማቸው የተዘረፈ ገንዘብ፤ ሀብት ንብረት የኢትዮጵያ መሬት በሙሉ 3)ድርጅቱን ከመነሻው የደገፉትና፤ … [Read more...] about «AmOr!» «አሞር!»
ከትናንት ወዲያ፣ ትናንትና ዛሬ
ዛሬ ላይ ቆሜ ወደኋላ ሳይ የትናንት ወዲያው ይናፍቀኛል፤ ትናንት ወዲያን አይቼዋለሁ፤ አውቀዋለሁ፤ ትናንትንም አይቼዋለሁ፤ አውቀዋለሁ፤ ዛሬንም እያየሁትና እያወቅሁት ነው፤ ከትናንት ወዲያ በጃንሆይ ዘመን የአገዛዙ ነቃፊ ነበርሁ፤ የወደፊቱን የማየት ችሎታ ስለሌለኝ የጃንሆይን አገዛዝ ነቃፊ ነበርሁ፤ በትናንት ወዲያ ላይ በጃንሆይ ዘመን ላይ ቆሜ ዛሬን የማየት ችሎታ ቢኖረኝ የጃንሆይን አገዛዝ ነቃፊ አልሆንም ነበር፤ ትናንትን፣ የደርግን ዘመን ከዛሬው ከወያኔ ዘመን በመሠረቱ እምብዛም የማያለይ በመሆኑ አይናፍቀኝም፤ የዛሬው የወያኔ ዘመን አስመረረኝ፤ ምርር ብሎኛል፤ እንዳልሰደድ ቀዳማዊ ምኒልክ ያለውን ተከታይ ነኝ፤ እንዲህ ብሏል፡-- ‹‹እናቴንና አገሬን እተው ዘንድ አይቻለኝም፤›› እናቴ ‹‹በጡቶቿ አምላኛለችና››፡፡ እናትና አባቴ የኢትዮጵያን ምድር ሆነዋል፤ አባቴ በማይጨው ዘምተው … [Read more...] about ከትናንት ወዲያ፣ ትናንትና ዛሬ
ECOLOGICAL DEGRADATION, ETHNO-NATIONALISM & POLITICAL CONFLICT IN ETHIOPIA
This article has bearing on the ethno-genesis of the TPLF as an ethno-nationalist movement. Although the alleged "Amara oppression in Tigrai" is projected as the main cause for the emergence of, what has now become, a very virulent Tigrean ethnic nationalism, the underlying problem of ecological degradation in Tigrai which significantly contributed to the ethno-genesis of this movement has been hardly touched upon. It is this salient aspect which I have tried to elucidate in this article. One … [Read more...] about ECOLOGICAL DEGRADATION, ETHNO-NATIONALISM & POLITICAL CONFLICT IN ETHIOPIA
“የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት
የመረጃ መረቡ ከሃገር ቤት በሚሰማው የህዝብ እንቢተኝነት አመጽ ተጨናንቆ እኛንም አጨናንቆን ከርሟል። በዚህ የመረጃ ቅብብሎሽ መካከል ወደ ምሥራቅ ሳውዲ ለስራ ጉዳይ አቅንቸ ነበር። ርያድ፤ ደማም፡ ጁቤል፤ ሃፍር አልበጠንን ለአንድ ሳምንት ሳካልል ከሃገር ቤት ከሚሰማው መረጃ እኩል በሳውዲ ዙሪያ ያሉ በርካታ ወገኖቸ የተለያዩ መረጃዎች በስልክ አድርሰውኛል። በተዘዋዎርኩባቸው ከተሞች ያገኘኋቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቸም የሚያመውን የስደት ህመም ሳይደምቁ አጫውተውኛል። ሁሉም አሳሳቢ ናቸው፣ ሁሉም ቢያንስ መፍትሔ ይሻሉና ዝም የማይባለውን የወገንን ድረሱልኝ ጥሪ አሳውቃችኋላሁ! ዛሬም በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተኑ ችግር የገጠማቸው ዜጎች መብት አስከባሪ አጥተው ሲንከራተቱ፣ ሲንገላቱና የድረሱልኝ ጥሪ እያሰሙ ነው! በአንጻሩ አዲስ ኮንትራት ውል ከሳውዲ አረቢያ ጋር ለመስማማት ደጋግሞ … [Read more...] about “የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት










