• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ወይም “ጉማሬው” ዋናተኛ

August 18, 2016 12:01 pm by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ከተጫነባቸው በኋላ በUN ኢትዮጵያን ወክሎ የመቀመጥ ስልጣናቸው ቀረና ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ። እድገት ወይም ውርደት (promotion ወይም demotion) ሳንል፣ ወደ ሌላ ሥልጣን ተሻገሩ እንላለን። አቶ ዠ የሃገሪቱ የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው ተሾሙ። እንግዲህ “ፕሬዚደንት” የሚለው ቃል እስካለ ድረስ፣ ሹመቱ፣ ማዕረጉ ትልቅ ነው ተብሎ እንዲታሰብ የአቶ ዠ መልካም ፈቃድ ነው እንላለን። የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ሆነው የተሾሙበት ጊዜ ደግሞ እንዳጋጣሚ ሆኑ የኦሎምፒክ ውድድር የተቃረበበት ጊዜ ነበር። ዠ አዲሱ ቢሮአቸው ሆነው አንድ ሃሳብ ብልጭ አለላቸው። ሃገራቸውን በኦሎምፒክ መወከል። የሃገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ በኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ ተገኝቶ ማውለብለብ…። እንዴት ያለ ድንቅ ሃሳብ ሲሉ አሰቡ አቶ ዠ።

እንግዲህ መሰደብ፣ መዋረድ፣ መሰደድ፣ መደብደብ፣ መራብ… ወዘተርፈ… ባጨሩ ያለም ሁሉ መከራ ተሰብስበው የሃገሪቱ ህዝብ ላይ የወረዱበት ዘመን መሆኑ አይረሳም። የዚህ ሁሉ ምክንያት ደግሞ ያው “ዠ”ዎች ናቸው ተብሎ በሰፊው ይታመናል። ሙሰኝነት፣ ቅጥ ያጣ ስግብግብነት፣ ዘረኝነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም… ወዘተርፈ (ላበ-ተርፈ ሊባል አይችልም። ዛሬ “ዠ”ዎች ወዛም እንጂ ላባም አይደሉምና) ያመጡት ጣጣ ነው።

ሰሞኑን የሃገሬው ህዝብ ያፈረበትና የተሰደበበት ሁኔታም በዚሁ ምክንያት ነው፣ የስግብግብነትና በሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም ውጤት ናቸው። አባት ልጁን ከሌሎች፣ ችሎታ ካላቸው የማስቀደም – ዠ  “ጉ” ን ከሌሎች፣ ችሎታው ካላቸው የማስቀደም ውጤት ናቸው። “ዋናተኛው” ጉን ማስቀደማቸው። “ዋናተኛው” ጉ ሃገሩን ወክሎ “ዋኝቶ” ህዝቡንና ሃገሩን አሳፍሯል። የሃገሬው አትሌቶች ህዝባቸውን በማኩራትና ሃገራቸውን በበጎ በማስጠራት ነበር የሚታወቁት። ጉ፣ የአቶ ዠ ልጅ ደግሞ በበኩሉ በአለም ታይቶ የማይታወቅ ቀርፋፋነትን በማሳየት ሃገሪቷን ዳግም አስጠራ። ዳግም አዋረዳት! ጋዜጦች ጻፉ፣ “ሃገሪቷ እኮ ባህር የላትም፣ መሬት ብቻ ነች።” ሲሉ። “ጉ የሚዋኝበት፣ የሚለማመድበት የለም እኮ” እንደማለት ከጀላቸው። ሰው ዋና የሚዋኘው ባህር ውስጥ ብቻ ነው? ሃይቆችና ወንዞች የሉም እንዴ?

“ዋናተኛው” ጉ እጅግ ወደኋላ ከመቅረቱ የተነሳ ከቴሌቪዢን ካሜራ እይታ ውጪ ነበር። ሌሎቹ ዋኝተው ጨርሰው ኮፍያቸውንና መነጽራቸውን አውልቀው ሰውነታቸውን ለማደራረቅና ልብሳቸውን ለመቀየር ሲዘጋጁ “ጉማሬው” ዋናተኛ ጉ ውሃ ውስጥ ይጎማለላል። አንዳንዶች ”ምናልባት ነዳጅ እየፈለገ ይሆናል” ሲሉ አላገጡ። አንዳንዶች ደግሞ  “አሳነባሪው” ጉ ብለው አንሾካሾኩ (tweet አደረጉ)። “አሳ ነባሪ እኮ በጣም ይዋኛል። ውቅያኖስ ያቋርጣል” ሲሉ ሌሎች ተከራከሩ። በመጨረሻ “ጉማሬው” በሚለው ቅጽል ተስማሙ።

“ጉማሬው” ዋናተኛ የሃገሪቱ ምርጥ ዋናተኛ አይደለም ሲል አንድ አንድ ታዋቂ ጋዜጣ ደግሞ እንዲህ ሲል ዘገበ፣ “ጭምጭምታ ከሁነኛ ምንጮች እንደሰማነው ጉ የሃገሩ ምርጥ ዋናተኛ አይደለም። በተለየ ችሮታ ነው እንዲወዳደር የተደረገው፣ አባቱ አቶ ዠ የሃገሪቱ የዋና ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት ናቸው።” ይለናል። አቶ ዠ ከልጃቸው ከ ጉ ጎን ሆነው የሃገራቸውን ሰንደቅ ዓላማ ይዘው የታዩበትን ፎቶ ጋዜጣው ጎልጉሎ አውጥቶ ለጥፎታል።

ከውድድሩ በኋላ“ጉማሬው” ዋናተኛ ቃለ መጠይቅ ተደርጎለት ሲመልስ፣ “በኦሎምፕክ ስወዳደር የመጀመሪያ  ጊዜዬ  ነው። ባገኘሁት ውጤት በጣም ተደስቻለሁ። በኦሎምፒክ መሳተፍ በጣም ትልቅ ክብር ነው። ስለዚህም ደስተኛ ነኝ። እኔ ሃገር ሁሉም ይሮጣል፣ ይሮጣል…እኔ ግን እንደነሱ መሮጥ አልፈለግኩም፣ በዋና ነው ሃገሬን መወከል የፈለግኩት” አለ። ጋዜጠኛው፣ “ምናልባት ብትሮጥ ኖሮ ቦርጭህ ስለሚረግፍ፣ በዋና ከዚህ የተሻለ ውጤት ልታገኝ ትችል እንደነበር ትገምታለህ” ሲል አከታትሎ ጠየቀው። ጉ አልመለሰም። አንገቱን አቀርቅሮ የዋና መነጽሩን ማሻሸት ያዘ።

የሃገሬው ህዝብ፣ “ይሄ ነገር እንዴት ነው?” ሲል ማሰላሰል ያዘ።

“የመጀመሪያዬ” የሚለው ቃል የሃገሪቱን ህዝብ አበሳጨ። “የመጀመሪያዬ”? ”ይሄ ሰው፣ ጉ ዠ ሃገራችንን ደጋግሞ ሊያሰድብ ይፈልጋል እንዴ?” ሲል የሃገሬው ህዝብ በቁጨት ጸጉሩን ነጨ። ህዝቡ “የሃገሩ ምርጥ ዋናተኛ ሳይሆን ይህ ዕድል ለሱ የተሰጠው በምን ምክንያት ነው? ሌሎች፣ ከሱ የተሻሉ ስንት አመት ሙሉ ለዚህ ዕድል፣ ለዚች ቀን፣ ለኦሎምፒክ ሲሉ ሲዘጋጁ የከረሙ እያሉ እሱ በምን ምክንያት፣ ያለችሎታው ለኦሎምፒክ በቃ? እስከመቼ ነው እንዲህ በቅጥ ያጣ ስግብግብነት፣ በዘረኝነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ በመጠቀም በሚመጣ ውርደት ተሸማቀን የምንኖረው?” ሲል የሃገሬው ህዝብ ተቆጣ።

“ከሱ የላቀ ችሎታ ያላቸው እያሉ እሱ እንዴት ይህንን፣ ሃገራችንና እኛን እንዲወክል ተደረገ? በምንሥ ምክንያት ነው? የዚህ ሁሉ ፈላጭ ቆራጭ፣ የዋና ፌዴሬሺኑ ፕሬዚደንት፣ አቶ ዠ ተጠያቂ ይሆናሉንስ?” ሲል ህዝቡ እንደዝናብ አጉረመረመ፣ ከዚያም እንደነጎድጓድ አስጎመጎመ፣ አስጎምጉሞም አልቀረ። እንደ በልግ ዝናብ ድንገት መውረድ ጀመረ፣ እንደ ሃምሌ ወንዝ ጎዳናውን ሞላው፣ በቁጣ ሞገድ ጎዳናውን እንደ ማዕበል አናወጠ።

“መዋራድ በቃን! መሰደብ በቃን!”

“ክብራችንን ያዋረደው ዠ ተጠያቂ ይሁን!”

“ቅጥ ያጣ ስግብግብነት፣ ዘረኝነት፣ በሥልጣን ያለአግባብ መጠቀም አሁኑኑ ይቁም !”

አቶ ዠ ደግሞ ቢሮአቸው ሆነው በመስኮት ማዕበሉን ይመለከቱ ጀመር። የማዕበሉ ሞገድ እቢሮአቸው ገብቶ  ጠራርጎ እንዳይወስዳቸው ሰጉ።

ከህዝቡ፣

“ሥራና ሃላፊነት በችሎታ እንጂ በችሮታ መሆኑ ዛሬውኑ ይቁም!” የሚሉ ቃላት እንደነጎድጓድ ያስጎመጉሙ፣ እንደ መብረቅ ያብለጨልጩ ጀመር።

በዚያ ብልጭታ ህዝቡ ተስፋ ማየት ጀመረ። የእኩልነት ተሰፋ፣ የማደግ ተስፋ፣ የመኖር ተስፋ፣ በችሎታ እንጂ በችሮታ ያለመኖርን ተስፋ…

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature, Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule