አዋቂው፣ ዕውቁ እና ተወዳጁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ትሁቱ እና ሠላማዊው ፖለቲከኛ አንዱዓለም አራጌን በአካል ያየኋቸው በ2003 መጨረሻ በአንድነት ፓርቲ በተዘጋጀ የውይይት መድረክ ላይ ነበር። ያኔ በጋራ የምንጦምርበትና ለእስር የዳረገን ዞን ዘጠኝ አልተመሠረተም ነበር። ነገር ግን ጓደኞቼ እና ባልደረቦቼ Soleyana እና Atnaf ሳንተዋወቅ በፊት እዚያ እንደነበሩ ኋላ ስናወራ ሰምቻለሁ። በርካታ ሰዎች በተገኙበት ያ ስብሰባ ላይ ዛሬ ዝዋይ ወኅኒ የተጣለው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ተገኝቶ ነበር። ያቺ ስብሰባ እስክንድር ጥናታዊ ንግግር ያቀረበባት ስብሰባ ነበረች። ጥናታዊ ንግግሩ እና ውይይቱ በጥቅሉ በእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ የተከሰሱት 24 ሰዎች ላይ ማስረጃ ሆኖ መጥቷል። የእነአንዱዓለም አራጌ መዝገብ ብዙ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች የተከሰሱበት መዝገብ ነው። የአዲስ … [Read more...] about የሁለት እስረኞች ወግ!
Right Column - Primary Sidebar
ልዑል በሉዓላዊ መንግስት ይሰለጥናል!
‶…ልዑሉ በሰዎች መንግስት ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን እንዳለውና እነዚህንም መንግስታት ለወደደው እንደሚሰጥ እስክታውቅ ድረስ…″ ዳን.4፡32 ሉዓላዊ መንግስት (sovereign nation) በሌሎች ቅኝ ግዛት ወይም ባርነት ስር ያልወደቀ ራስ-ገዝና ነጻ መንግስት ሲሆን የሃገሪቱ የአመራር አካላት እንደመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካላት ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ የህዝቡም ሰላምና የሁለንተና እድገት በሃገሪቱ አመራር አካላት ብቃትና ቅንነት ይወሰናል፡፡ ሉዓላዊነት ሌሎች አካላት በአንድ ሃገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ (meddle) ዋስትና እንደሚሰጥ በማሰብ አንዳንድ መንግስታት በማንአለብኝነት ከእግዚአብሔርም ከሰውም የሚያነካካ እርምጃ ሲወስዱ ይስተዋላሉ፡፡ ከነዚህም አንዱ ለትምህርታችን በቅዱሱ መጽሀፍ በስፋት የተተረከልን የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነጾር ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔር ባርያዬ/አገልጋዬ … [Read more...] about ልዑል በሉዓላዊ መንግስት ይሰለጥናል!
የእናት ለቅሶ
እናት በፍቅር፣ ጽንስ ይዛ፣ ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ ራስዋን ምግብ አድርጋ፣ በማኅጸንዋ ሸሽጋ፣ ሽሉን ወደሰውነት አሳድጋ፣ የፈጣሪን ባሕርይ ተጋርታ፣ ሰው ሆና ሰው ፈጣሪ የሕይወት አለኝታ፣ በጻዕር አምጣ ወልዳ፣ አቅፋ በፍቅር አጥብታ፣ ተጨንቃ አሳድጋ፣ እንቅልፍ አጥታ፣ ሲስቅ ሲያስቃት፣ ሲያለቅስ ሲያስለቅሳት፣ ስትቆጣው እንዲያድግላት እንዲማርላት፣ ክቡር ሰው ሆኖ እንዲያኮራት፣ ያላትን ሁሉ ከፍላ መስዋእት፣ በጉጉት ስትጠብቅ -- ጨካኞች ሬሳውን ጣሉላት፡፡ ማኅጸንዋ ተኮማተረ፤ አንጀትዋ አረረ፤ አስፋልቱ ላይ የተንጣለለው ደም፣ ከልጅዋ አካል ጠብታም አልቀረም፤ ሙት አደረጋት በቁም፤ ከማኅጸንዋ እንደፈሰሰ ተሰማት፤ ተወልዶ ያደገ ልጅ አስወረዳት፤ በወጣት ልጅዋ የፈራረሰ አካል እስዋም ፈራረሰች ወየው ልጄ! ስትል፤ አካልዋ ተፍረከረከ፤ ጉልበትዋ … [Read more...] about የእናት ለቅሶ
ዲገላው የጎረቤታችን ድመት የገጠመው የሞት አደጋና የወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በንፅፅር ሲታዩ
በተወለድኩበት በሂርና ከተማ ጎረቤታችን የሆኑ እማማ የልፍተለው እናት የሚባሉ ደግ ሴትዮ ነበሩ። ታዲያ አንድ እሳቸው ያሳደጉት ድመታቸው ከቤት ሸሽቶ ወጥቶ በራሱ ተዳዳሪ ሆነ። በሀረርጌ ከአሳዳሪ ጌታው ቁጥጥር ውጭ ወጥቶ ዱር ገብቶ በራሱ የሚተዳደር ድመት ዲገላ ድመት (ማለትም እንደ አውሬ ዱር የገባ ድመት ማለት ነው) የሚል ስም ይሰጠዋል። ዲገላ ቃሉ ከኦሮምኛ ቋንቋ የመጣ ሲሆን ዛሬ ግን በሀረርጌ ያሉ አማሮችም የአማርኛ ቃል አድርገውት ከላይ በገለጽኩት ትርጉሙ ይጠቀሙበታል። ይህ ድመት በራሱ ተዳዳሪ ከሆነም በኋላ በሰፈራችን ውስጥ ያሉ ጫጩቶችን እየበላ፤ ድስት እየከፈተ፤ የተሰቀለ ቋንጣ እያወረደ ወዘተ የሰፈሩን ነዋሪ በጣም አስቸገረ። ይህ ድመት የእኛንም የዶሮ ጫጩቶች በተደጋጋሚ በልቶብናል። ይህን ድመት እግዚሃብሄር ከገላገላቸውና ከገደለላቸው ለሂርና ስላሴዎች እጣን ይዘን … [Read more...] about ዲገላው የጎረቤታችን ድመት የገጠመው የሞት አደጋና የወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በንፅፅር ሲታዩ
Ethnic cleansing and Ethiopia
The TPLF Party (ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) that is in charge of Ethiopia but that mostly parades around as EPRDF is currently on an apology mode and no resource is spared in spreading the well-rehearsed lie. They have activated former leaders from retirement. Old trusted and reliable Cadres are brought out to prove their worthiness in this time of crisis for the mafia group and bloggers and social media activists are on double time. Their task is very easy in Ethiopia. There are no dissenting voices … [Read more...] about Ethnic cleansing and Ethiopia
ሙስናውና የሕዝብ አመፁ በኤኮኖሚው ላይ እያደረሰ ያለው ጣጣና መኮታኮት
ዶ/ር ሰይድ ሃሰን (መሪ ስቴት ዩኒቨርሲቲ) መስከረም 1፣ 2009 በሲንሲናቲና አካባቢዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ያቀረቡት አጭር የንግግር ንጥረ ሀሳብ (ተቀርፎ የወጣ) የንግግሬ ንጥረ ሀሳቦች በ4 ይከፈላሉ፡ በኢትዮጵያ የተከሰተው ሙስና ምን ይመስላል? እንደትስ ማስወገድ ይቻላል? ሙስናው በኤኮኖሚው ላይ ያመጣው ክስረት፤የሙስና ንቅዘት የሕዛባዊ አመፁ አንዱ ምክንያት መሆኑ፤ የህዝባዊ አመፁ በኤኮኖሚው ላይ እያደረሰ ያለው ክስረት፤ ከኛ (ከዲያስፖራው) ምን ይጠበቃል? ሀ) በኢትዮጵያ የተንሰራፋው የሙስና ንቅዘት ጠባይ ምን ይመስላል? የኢትዮጵያን ሙስና በሚመለከት በርከት ያሉ ጽሁፎችንና ንግግሮችን አድርጌአለሁ። በዚህ ጉዳይም እቀጥላለሁ። በኢትዮጵያ ኢላይ ተንሰርፍቶ ያለው ሙስና ተመሳሳይነቱ በዩክሬይን፤ በራሽያና ተመሳሳይ ሀገሮች የተከትሰተውን አይነት … [Read more...] about ሙስናውና የሕዝብ አመፁ በኤኮኖሚው ላይ እያደረሰ ያለው ጣጣና መኮታኮት
ቢወሳሰብም መፍትሔው ቀላል ነው
የአገር ጉዳይ ለጥቂቶች የሚተው አይደለም፤ አያገባህም ሊል ወይም ሊባል የሚገባው ዜጋ የለም። እያንዳንዱ በቻለው መጠን አሳቡን ማካፈልና ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር መትጋት አለበት። መንግሥት የሕዝቡ አካልና አገልጋይ እንደመሆኑ ዜጎች ተሳትፎአቸው እንዳይገታ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ግዴታው ነው። አሁን የሚታየው አዝማሚያ እጅግ አሳሳቢ ነው። ሕዝብና መንግሥት፣ ሕዝብና ሕዝብ፣ መሪዎች ተፈራርተዋል። መተማመን አቅቷቸዋል። አይመለከተኝም ማለት የማይቻልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። የተለያየ ዓላማ ያነገቡ ቡድኖች ከየአቅጣጫው መንቀሳቀሳቸው ነገሮችን አወሳስቦአቸዋል። እነዚሁ ቀጥተኛ ዓላማቸውን ማስረዳት ሆነ እርስ በርስ መስማማት አልቻሉም። አንዳንዶችም ሁሉን ጠርገን አስወግደን አዲስ አሠራር እንመሠርታለን የሚሉ ናቸው። በስድሳ ስድስት እና በሰማንያ ሦስት ማግሥት ያየነውን ስንፍና መድገም ብቻ ሳይሆን … [Read more...] about ቢወሳሰብም መፍትሔው ቀላል ነው
ይድረስ ለብአዴን አባላት
ወያኔዎች “ሕዝቡን አረጋጉ፤ ሰላም ፍጠሩ” ወዘተ. እያሉ ቁም ስቅላችሁን እያበሏችሁ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ እናንተም እኛም አሳምረን እንደምናውቀው ግን የሕዝባችን ሰላም ያደፈረሰው ራሱ ወሮበላው የወያኔ ቡድን ነው፡፡ በሕዝባችን ላይ የዘር ማጥፋት ጦርነት አውጆ ንጹሐንን የሚፈጀው፣ እንቡጥ ሕጻናትን የሚጨርሰው፣ በሺሕዎች የሚቆጠሩ የአማራ ወጣቶችን በየእስር ቤቱ አጉሮ ዘግናኝ ቶርቼር የሚፈጽመው፣ በርካታ ንጹሐን አማሮችን ከረሸነ በኋላ የወልቃይት ጠገዴን ጉዳይ ሁለቱ ክልሎች ተወያይተው ይፈቱታል እያለ በደማችን ላይ የሚቀልደው፣ የሰላም ጉባኤ እያለ እየሰበሰበ በብሶት የሚናገሩትን ወገኖቻችንን እየነጠለ የሚያስረው ወዘተ ወዘተ ራሱ ነብሰ ገዳዩ ወያኔ እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ሕዝባችን ሰላም ወዳድ ነው፡፡ የሰላም ጠንቅ፣ የሽብርና የሁከት አባት ወያኔ ነው፡፡ ስለሆነም ሰላም … [Read more...] about ይድረስ ለብአዴን አባላት
ETHIOPIA AT THE CROSSROADS – Win-Win or Zero-Sum?
Ethiopia is in crisis.The country is experiencing widespread civil disobedience manifesting itself in demonstrations, strikes, boycotts and in some cases armed resistances. Under the current federal arrangement, Oromia and Amhara regional states are the two largest parts of the federation, constituting 30 and 18 million population, respectively.That is close to half of the country's population.Based on news reports from inside and outside sources, in almost all parts of these two largest … [Read more...] about ETHIOPIA AT THE CROSSROADS – Win-Win or Zero-Sum?
ይድረስ — ለኃይለማርያም ደሳለኝ!
ለ’ክቡር’ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ለኢሕአዴግ ሊቀ-መንበር፣ ጠቅላይ ‘አዛዥ’ ለ"አግዓዚ" ጦር...፤ ይድረስ ለአቶ ኃይለማርያም! በስምዎ ባዘሏት ወላዲተ-አምላክ.. በወልድ በእየሱስ ክርስቶስ ስም ልያዝዎ፣ ኢትዮጵያን በጥይት አያቃጥሏት... እግዚአብሔር አባት ይቅር ይበልዎ! በደርግም ሆነ በወያኔ ዘመን ባገር ያሴሩ፣ እስከዛሬ ሕዝብን ሲያስጨፈጭፉ የኖሩ፣ “እግዚአብሔርን አናውቅም” ብለው የካዱ ነበሩ፤ እርስዎ ግን፣ ከቤተሰብዎ ጋር ማዕድ ሲጋሩ፣ የየዕለቱን ጸሎትዎን ሲያበስሩ፣ የአምላክን ስም ነጋ-መሸ እየጠሩ፣ ይመስለኝ ነበር በእምነት የከበሩ፤ ... ግና ከልብ እውነት ካልዘመሩ፣ ትዕዛዛዊ ቃላቱን ካልተገበሩ፣ እምኑ ላይ ነው ታዲያ አምልኮዎ? የአምላክን መሻት መፈጸምዎ? ከአረመኔዎች ጋር … [Read more...] about ይድረስ — ለኃይለማርያም ደሳለኝ!










