የኢትዮጵያ ሕዝብ በአሸባሪውና በፋሽስቱ ወያኔ ቁጥጥር ሥር ወድቆ 25 የመከራና የፍዳ ዓመታትን አሳልፎ 26ኛውን ጀምሮዋል:: በዚህ ረጅም የመከራ ዓመታት አንድም ቀን ወያኔን ከመታገል የተቆጠበበት ጊዜ ግን አልነበረም:: ወያኔም ባደራጀው የመጨቆኛ መሳሪያው: በወታደሩ: በስለላ መረቡ እና በመሳሰሉት የዘረኝነት አገዛዙን ለማራዘምና ኢትዮጵያን የማጥፋት ተልኮውን ከፍጻሜ ለማድረስ ከዚያም የኔ የሚለው አዲስ አገር ለመመስረት ባለው እቅድ ሕዝባችን በዘርና በሃይማኖት ከፋፍሎ እርስ በርሳችን ለማባላት ያደረገው ሙከራ በሕዝባችን እምቢተኝነትና አገር ፍቅር ከመከፋፈል ይልቅ አንድነትን በመምርጡ ያቀደውን ከግብ ለማድረስ ቀላል አልሆነለትም:: ይህን ተልኮውን ከግብ ለማድርስ መጀመሪያ ዓማራውን ለይቶ በሌሎች ጎሳወች ለማጥቃት ሞከረ: አልሆን ሲለው ደረጃ በደረጃ ወደሌሎች ጎሳወችም ፊቱን አዞረ:: … [Read more...] about የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ ስብስብ በሰሜን ካሊፎርኒያ
Right Column - Primary Sidebar
የአሁኑ የተለየ ነው
በጎንደር እየተካሄደ ያለውን ሀቅ፤ ሁላችንም በተለያየ መልክ እየተከታተልን ነው። በኢትዮጵያ ያለው መንግሥት የማንና ምን አንደሆነ በግልጽ ታይቷል። ሕዝቡም የደረሰበትን የ”በቃኝ!” ደረጃ እያየን ነው። አሁን በፓልቶክና በደረገጽ፤ በሬዲዮና በቲቪ መወሰናችን ያበቃበት ሰዓት ነው። ይህ ትግል እስከዛሬ ከተደረጉት ማናቸውም ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች የተለየ ነው። በአኝዋክ ዘመዶቻችን አልቀዋል። በኦጋዴን ዘመዶቻችን ረግፈዋል። በኦሮሚያ ዘመዶቻችን ተገድለዋል። በተለያየ መልክ ሕዝቡ ምሬቱን ገልጿል። ከፍተኛ መስዋዕትነት ክፍሏል። ይህ ሁሉ ተደማምሮ አሁን የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ወልዶታል። አሁን፤ የእስከዛሬው ጥርቅም ብሶት ውጤት ነው ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት የተደቀነው። የአሁኑ የተለየ ነው። በጎንደር የወልቃይትን ማንነት ይዞ የተነሳው ወገናችን ጥያቄ፤ የማንነት ብቻ ሳይሆን፤ የወራሪውን … [Read more...] about የአሁኑ የተለየ ነው
የክብር ዶክትሬት ክብሩን እያጣ ነው ተባለ
በሀገሪቱ ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በየዓመቱ ለሁለትና ሶስት ሰዎች የክብር ዶክትሬት መስጠትን እንደ ልማድ መያዛቸው ከክብር ዶክትሬት መሰረታዊ አላማዎች ጋር የሚፃረርና ክብሩን የሚያራክስ ነው ሲሉ የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ገለፁ፡፡ የክብር ዶክትሬት የሚሰጥባቸው መስፈርቶች በመርፌ ቀዳዳ ግመል እንደ ማሽሎክ ያህል ናቸው ያሉት ምሁራኑ፤ በአሁን ወቅት አዳዲስ ዩኒቨርሲቲዎች ጭምር ፉክክር በሚመስል መልኩ ዶክትሬቱን የሚሰጡበት አካሄድ በአስቸኳይ ሊታረም እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡ የክብር ዶክትሬቱ የተሰጠባቸው ግለሰቦችም ለስም መጠሪያነት መጠቀማቸው ተገቢ አይደለም ያሉት ምሁራኑ፤ መገናኛ ብዙኃን የክብር ዶክትሬት የተሰጠውን ግለሰብ፤ “የክብር ዶክተር” እያሉ መጥራታቸውም አግባብ ባለመሆኑ ማረም ይኖርባቸል ብለዋል፡፡ የቋንቋና ስነ ፅሁፍ ምሁሩ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ፤ ከሀገሪቱ … [Read more...] about የክብር ዶክትሬት ክብሩን እያጣ ነው ተባለ
የሕዝብ መብት የማያከብር መንግሥት በሕዝብ አመፅ ይወገዳል
ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ሥልጣኑን በጉልበት ወስዶ፣ የሕዝቡን መብት ገፎ፣ ያገሪቱን ሃብትና ንብረት የሚዘርፈው ቡድን ሥልጣኑና አድራጎቱ ዝንተ-ዓለማዊ እንደማይሆን ከወደቁትና ከተወገዱት ተመሳሳይ መንግሥታት ታሪክ ገና አልተማረም። ከፋፍዬ እኖራለሁ የሚለው ስልቱ እየተጋለጠ በየአቅጣጫው በሕዝብ ተቃውሞ እየተዋከበ ይገኛል። ወደ ታሪክ መቃብር የሚገባበት ቀን እያጠረ መጥቷል። አሁን በጎንደር ቀደም ሲል በሸዋ በተለያዩ ያኦሮሚያ ክልል አካባቢወች በጋምቤላና በሌሎቹም ያገሪቱ ክፍሎች የተነሳው ሕዝባዊ አመፅ ይህን የሚያመላክቱና ውድቀቱን የሚያፋጥኑ ተቃውሞዎች ናቸው።... ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ … [Read more...] about የሕዝብ መብት የማያከብር መንግሥት በሕዝብ አመፅ ይወገዳል
የሀገሬ ዲሞክራሲያዊ የበቀል ፖለቲካ!
* የሰሜኑ ኮከብ አብርሃ ደስታ እንኳንም ተፈታህ! የሰሜኑ ኮከብ ወንድም አብርሃም ደስታ ከእስር እንደሚፈታ ቢገመትም ዘንድሮ ሲሆን እንጅ ሲባል ለማመን ተቸግሬያለሁና ዛሬን መቆየት ነበረብኝ ። እናማ የሰሜኑ ኮከብ ደፋሩና ለእውነት ግንባሩን የማያጥፈው የመቀሌው አብርሃም ደስታ " እውነት ተፈታ " ሲባል ሰማሁ ፣ ደስ አለኝ ! አብርሽ እንኳንም ከቤተሰብ ፣ ከዘመድ አዝማድና ወዳጅ አፍቃሪ ወገንህ ጋር ተቀላቀልክ እልሃለሁ ፣ አብርሽ! ከሁሉ አስቀድሞ አብርሃም ሃብታሙ ከተኛበት ሲጎበኘው የሚያሳየውን ምስል ስመለከት በደስታ ኩራት ስሜቴን መቆጣጠር አቅቶኝ ማንባቴ አልቀረም ... ሁለቱ ወንድሞች ገርድሰው የጣሉት ልዩነትና ህብረታቸው ሳውቀው ዛሬ እንደ ብርቅ ነገር አስደሰተኝ ! በዚህ ዛቢያ ስማስን የዘር ፖለቲካው ክፋት አንደርድሮ ወደ ሌላ አቅጣጫ ወረወረኝ ... ከምንም … [Read more...] about የሀገሬ ዲሞክራሲያዊ የበቀል ፖለቲካ!
የህወሃቱ ሹም ራሳቸውን በራሳቸው ካዱ
በአዲስ አበባ ከተማ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሀና ማርያም፣ ፉሪ፣ ማንጎ ጨፌ ሌሎች በክፍለ ከተማው ስር ባሉ መንደሮች ከቤት መፍረስ ጋር በተያያዘ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ይታወሳል፡፡ ሁለት ፖሊሶችና አንድ የወረዳው ሥራ አስፈጻሚ ህይወታቸው እንደጠፋ በይፋ ቢነገርም የዚያኑ ያህል ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ባቀናበረው መረጃ ላይ እንዳመለከተው “መኖሪያ ቤቶቹ ይፈርሳሉ በመባሉ ከአካባቢው ነዋሪዎች የተወሰኑት አቤቱታ እያቀረቡ ባለበት ወቅት የመንግስት አፍራሽ ግብረኃይሎች ቤቱን ለማፍረስ የመብራት ትራንስፎርመር መንቀል እንደጀመሩና በዚህ መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደተፈጠር ነዋሪዎች ይናገራሉ”። ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች በዶዘር በሚፈርሱበት ወቅት ወንዶች በአካባቢው እንዳይጠጉ መከልከሉን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ከተነሳው ግጭት … [Read more...] about የህወሃቱ ሹም ራሳቸውን በራሳቸው ካዱ
“ሰው አይደለም ! …” አለኝ
ገና ቁጭ እንዳልኩኝ ቀጥሮኝ እንዳገኘኝ እከሌ ጨርሶ «ሰው አይደለም!» አለኝ ምነው? ምን አ’ረገህ ? «ሰው አይደለም!» ስልህ እኮ! ምን አ’ረገህ? «ሰው አይደለም!» አልኩህ። ቢራችንን አዘን በዝምታ ቆየን እንደገና ደግሞ ሳሉን እየሳለ አንገቱን ነቅንቆ «ሰው አይደለም!» አለ። ሰው ይመስላል አልኩኝ ስሜቱን ልረዳ ፊቱን መረመርኩኝ ባ’ይኑ እየገረፈኝ አይምሰልህ! አለኝ ግንባሩ ታጠፈ ጥርሶቹን ነከሰ ጠረጴዛ መታ፣ ቢራችን ፈሰሰ ልጠራርግ መጥታ - ልጅት እያየችኝ በፊቷ ምልክት ምን ሆኗል? አለችኝ መዳፌን አሳየሁ፣ ከንፈሬን አስረዘምኩ እኔም ልክ እንደሷው በምልክት መለስኩ እሱ ግን ቀጠለ «ሰው አይደለም» ማለት «ሰው አይደለም!» አልኩኝ እኔም ተመቸሁት በቢራ ተራጨን በውስኪ ታጠብን ስሙን እያነሳን «ሰው አይደለም!» አልን። ልጅትም … [Read more...] about “ሰው አይደለም ! …” አለኝ
ደብዳቤ
ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለጓደኞቻቸው በሙሉ፤ ሰላምታዬን አቀርብላችኋለሁ፡፡ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር አገር ነች፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ የእግዚአብሔር ሕዝብ ነው፤ ክርስቲያኑም፣ እስላሙም፣ አረመኔውም የእግዚአብሔር ነው፤ እንደየእምነቱ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚኖር ነው፡፡ የእግዚአብሔር ጊዜ የተለየ ነው፤ ትእግስቱን ስለሚያረዝመው የተረሳ ያስመስለዋል፤ እግዚአብሔር ግፍን አይረሳም፤ እግዚአብሔር ሁሌም ለአቅመ-ቢሶች ጉልበት የሚሆንበት መንገድ አለው፤ ግፍ በእግዚአብሔር በር ላይ እንደተጣለ ግም ቆሻሻ ነው፤ እግዚአብሔር ሲፈቅድ ይጠርገዋል፤ ወይም ያስጠርገዋል፡፡ እግዚአብሔር መንገዱ ብዙ ነው፤ ግፍን የሚያስከፍለው በተለያየ መንገድ ነው፤ በግፈኛው ቤተሰብ ላይ ሁሉ የግፈኛነት ጠባሳን ያሳርፍበታል፤ ሰዎች ለሥልጣናቸው ባላቸው ቅናት የእግዚአብሔርን ሥልጣን ይጋፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ሥልጣን መጋፋት … [Read more...] about ደብዳቤ
አበራ ነጋሣ
የልጁን ፊት አተኩሮ እየተመለከተ፤ በልቡ በጣም ሩቅ ወደሆነ የማያውቀው ሀገር ዘመተ። ልጁ የአስራ ስድስት ዓመት ወጣት ነው። አባቱን አስታውሶ ነጋሳ ብሎ ስይሞታል። እናም የልጁ ስም ነጋሳ አበራ፤ የሱ ስም አበራ ነጋሳ ነው። አበራ ነጋሳ የተወለደው አዘዞ ከተማ ነበር። አዘዞ፤ ከጎንደር ከተማ ወደ አየር ማረፊያው ሲሄዱ፤ ከከተማው አስራ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ፤ አየር ማረፍያው ከመድረሱ በፊት ደግሞ፤ ሶስት ኪሎ ሜትር ቀድማ ትገኛለች። አዘዞ የወታደር ሰፈር ነበረች። ባለፈው የ፳ኛው ምዕተ ዓመት አጋማሽ አካባቢ፤ የሰሜኑን ሀገራችንን ለመከላከል የተቋቋመው የ፪ኛ ክፍል ጦር፤ ከሶስቱ ብርጌዶች አንዱ፤ የ፰ ብርጌድ፤ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ ያለውን ደንበር ለመጠበቅ አዘዞ ሰፍሮ ነበር። ይህ የ፰ ብርጌድ፤ ሶስት የሻለቃ ጦሮችና አባሪ የከባድ መሳሪያ፤ የሕክምና፣ የመገናኛና የዋናው … [Read more...] about አበራ ነጋሣ
“ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል”
ከጥቂት ቀናት በፊት “ሀገር አለኝ!! ወገን አለኝ!!” በማለት በፌስቡክ ገጹ ላይ ይህንን የለጠፈው የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ ሃብታሙ አያሌው በጠና ታምሞ በኮማ ውስጥ ይገኛል፡፡ “እዉነት እዉነት እላችሁአለሁ ስቃይና መከራ የምቀበልላት ብቻ ሳትሆን የምሞትላት ሀገር አለችኝ!! "ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለዉ" ከሚል ጀግና ህዝብ ተወልጄ በእስካሁኑ ስቃይ ጉልበቴ አይዝልም። እንድበረታ ዛሬም ከጎኔ ላልተለያችሁ ቃሌ ይሄ ነዉ። አመሰግናለሁ” ነበር ያለው! የትግል አጋሩ ዳንኤል ሺበሺ (Daniel Shibeshi) በጥቂት ሰዓታት በፊት በፌስቡክ ገጹ ላይ ከላይ የሚታየውን የሃብታሙን ፎቶ አድርጎ ያሰራጨው ጽሁፍ እንዲህ ይላል፤ “በሀብታሙ አያሌው ጤና መታወክ፣ እየተረባበሻችሁ ላላችሁ ሁሉ በያላችሁበት ሆናችሁ ፀሎታችሁን ቀጥሉበት። አሁንም በኮማ ውስጥ ነው ያለው። ለውጥ … [Read more...] about “ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል”










![“ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል”](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2016/06/habtamu-300x225.jpg)