ዳንኤል ሺበሺ ከወህኒ ያስተላለፈው መልእክት ከቤተሰቡ በተገኘው መረጃ መሰረት ዳንኤል የተወለደው በደቡብ ኢትዮጵያ ነው፡፡ ያደገው እንደአብዛኛው ኢትዮጵያዊ በለምለሟ ቁጫ ወረዳ አረንጓዴ መስክ ሮጦና ተራራና አቀበት ወጥቶ ነው፡፡ ከልጅነቱ ጀምሮ ንቁ ነበርና ቤተሰቡ ወደ ትምህርት ቤት ሰደደው፡፡ ተማረ፡፡ እስከ ዩኒቨርስቲ በመዝለቅም ቀጠለ፡፡ ከዚያም ሳይማር ወዳስተማረው ህብረተሰብ በመመለስ ማገልገሉን ተያያዘው፡፡ ግና ትምህርት የአለማችንን ተጨባጭ ሁኔታ እንዲለይ አስችሎት ነበርና በሚሰራው ስራ ብቻ ሊረካ አልቻለም፡፡ ህዝቡ ላይ የማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊና የማህበራዊ ፍትህ እጦት እንደሚያሰቃየው ተመለከተ፡፡ ወጣቱ ዳኒ በተደጋጋሚ እንደሚናገረው ‹‹ህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ ከንፈር በመምጠጥ ብቻ ማቆም እንደማይቻል አውቅ ነበር፡፡ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ … [Read more...] about “ዉሃ በሌለበትና ቱሃን በበዛበት ጣቢያ እያንገላቱኝ ነው”
ፕሮፌሠር ፍቅሬን ለቀቅ ቧልትህን ጠበቅ
ሰሞኑን በፕሮፌሠር ፍቅሬ ስራዎች ለማሾፍ እና የእርሳቸውን ክብር ለማውረድ በጅምላ እየተካሄደ የሚገኝ የስም ማጥፋት ስራ እየተመለከትኩኝ ነው አንዳንዶቹ ባለማወቅ እና ከብስለት ማነስ የሚያደርጉት መሆኑን ባውቅም የተወሰኑት ግን ሆን ብለው የሚፈፅሙት ተግባር መሆኑን ለማወቅ ችያለው፡፡ በፕሮፌሰሩ ላይ እየተካሄደ የሚገኘው የማንቋሸሽ ተግባር ከየት እንደመነጨ ለምን እንደሚካሄድና እነማን እንደሚፈፅሙት መመልከቱ መልካም ይመስለኛል፡፡ ፕሮፌሠር ፍቅሬ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2008 ዓ.ም ለንባብ ያበቁት የኦሮሞና የአማራ ህዝብ ትክክለኛ የዘር ምንጭ የተሰኘው መፅሐፍ ለገበያ ከዋለ በኋላ በኢትዮጵያውያን ዘንድ እጅግ ተፈላጊ መፅሐፍ በመሆን መነበብ የቻለ ትልቅ መፅሐፍ ነው በዚህም በኢትዮጵያ የመፅሀፍ ታሪክ ውስጥ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ በተደጋጋሚ በመታተም ታሪክ የሰራ መፅሀፍ ነው፡፡ ይህ … [Read more...] about ፕሮፌሠር ፍቅሬን ለቀቅ ቧልትህን ጠበቅ
የካቲት 66 መሪ ኮከቡን ያጣ አብዮት
(የካቲት 66 ሕዝባዊ አብዮት 43ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ) ኢትዮጵያ ሀገራችን ታዳጊ ሀገሮችን በተለይ አፍሪካን እንደ ቅርጫ የተቀራመቱት ቅኝ ገዥዎችና ወራሪዎችን ጥቃት መክታ የግዛት አንድነቷንና ሉዓላዊነቷን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለማንም ባዕዳን ወራሪ ኃይል ሳትደፈርና ሳትገዛ የኖረች የማንነታችንና የክብራችን መግለጫ ናት። ዮሐንስ በመተማ፣ ቴዎድሮስ በመቅደላ፣ ምኒልክ በአድዋ እየተባለ የሚነገርላቸው፣ የሚጻፍላቸው፡ የሚዘፈንላቸው ነገስታቶች በሀገር አንድነትና በኢትዮጵያዊነት ማንነት ወራሪን ያሳፈሩና ዓለምን ያስደነቁ ኢትዮጵያዊነት የክብርና የአንድነት ተምሳሌትነቷን ያስፃፉና ያስተረኩ እስከዛሬም ሆነ ወደፊት ይህ ማንነታቸውን ታሪክ የሚያወሳላቸው ነገስታት ናቸው። በነዚህ ነገስታቶች የአገዛዝ ዘመን የሀገር አንድነትንና የግዛት ነፃነትን በማስከበር ደረጃ በየጊዜው ስማቸው የሚጠራ … [Read more...] about የካቲት 66 መሪ ኮከቡን ያጣ አብዮት
ዕዘኑ ለቀሪ
የመቅደላው ደባ ቋጠሮ የተቀበረው በቂም ጓሮ የምስጢሩ ገመና ለሥልጣኑ ንግሥና ከጠላት ጋር ወግኖ በተቸረው ኃይል መቅኖ መይሳውን አስገድሎ ለመግዛት ተደላድሎ በትረ መንግሥቱን ምራጭ ካሳ የጨበጠበት ድርጊት ጠባሳ ደረስጌን በውቤ ብሎ የቂም ብድሩን ከፍሎ የጎንደሮች መሬት ቁርሾ የበደሉ ዋይታ ሙሾ የግፉ ክፋት ገመና ይደረደራል ገና በበገና በበገና። ያችን የሙታን እናት አጉል ድከሚ ብሏት ያለ ፋይዳ ከንቱ ልፊ ዘርሽንም በዘር አጥፊ ለማለት ይመስላል መለእክቱ ነገረ ሥራው ኩነቱ። ለባለ ቀኑ ድሎት የማይጓደል አቅርቦት ይረጋገጥ ዘንድ ታልሞ የራሱን ኩራዝ አጨልሞ በየመብራቱ ምሰሶ ስር ዘብ መቆሙ ደብረታቦር ምፀቱ ለገብርዬ... ለገልሞ በአግራሞት አስደምሞ የትንብቱ ቅላጼ መዋዕሉ ለካስ ጊዜ ኖሯል ባለድሉ። ለጎንደሮች መከራ ለባለ … [Read more...] about ዕዘኑ ለቀሪ
ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ
የካቲት 13፣ 2009 ደመቀ መኮንን፣ ገዱ አንዳርጋቸውና የጎንደር ከተማ ከንቲባ ተቀባ ተባባል በአንድነት የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችን ባንጋገሩበት ወቅት ገዱ አንዳርጋቸው "መንግሥት የለም" እየተባለ የሚነገረውን የሚያረጋግጥ አስተያየት መስጠቱ ተስማ። እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ከተሰብሳቢው ለደመቀ በርካታ ጥያቄዎች ቀርበውለታል፡፡ ፋና ይፋ ባያደርገውም በውይይቱ የከረሩ ጉዳዮች መነሳታቸው ከአንዳንድ ምንጮች ለመረዳት ተችሏል፡፡ ደመቀ በገለጻው “ጥልቅ ተሃድሶ፤ መልካም አስተዳደር፤ የህዝብ ተሳትፎ፤ ...” በማለት ተሰብሳቢውን ለማሳመን ጥረት ቢያደርግም የተቻለው እንዳልሆነ ፋና ራሱ ከዘገበው ለመረዳት ቻላል፡፡ “... ተሃድሶው አንዱን አመራር ወደ ሌላ ስፍራ ከመቀየር የዘለለ ለውጥ እያመጣ አይደለም” የሚል አስተያየት ከውይይቱ ተሳታፊዎች መነሳቱን የጠቆመው የፋና ዜና ለዚህ ጥያቄ … [Read more...] about ገዱ አንዳርጋቸው “መንግሥት አለመኖሩን” አመነ
ወያኔ እንዲህ እያሰበ መሆኑ ጭምጭምታ ተሰማ፤ ዕውነት ከሆነ ጥቅምና ጉዳቱ ምን ይሆን?
ዛሬ ላለንበት ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና ዐማራ የተሰኘውን ነገድ ከመኖር ወደ አለመኖር ያደረሳቸውን ምክንያት መገንዘብ፣ ለምንፈልገው መፍትሔ ጥርጊያ መንገድ ይከፍትልናል። ከትግራይ ነፃ አውጭ ግንባር (የትግሬ-ወያኔ) የትግል ጉዞ እንደምንረዳው፣ ችግር በገጠመው ቁጥር፣ ዓላማውንና ቆሜለታለሁ የሚለውን ሥርዓት እንደ እባብ ገላ በሌላ በመተካት ጊዜ ይገዛል። ከማኦ ዜ ዱንግ እስከ ኤንቨር ሆጃ፣ ከካርል ማርክስ እስከ ሌኒን፣ ከሂትለር እስከ ደቡብ አፍሪቃ የአፓርታይድ አገዛዝ ያሉትን ርዕዮተ-ዓለሞች ካንዱ ወደ ሌላው ከብርሃን ፍጥነት በፈጠነ ሁኔታ በመቀያየር ኅልውናውን ለማራዘም ይሞክራል። የትግሬ-ወያኔ ላለፉት 25 ዓመታት ያራመደው በዘር ጥላቻ ላይ የተመሠረተ ፖለቲካና አገሪቱንና ሕዝቡን በነገድ ሸንሽኖ ያደረሰው ጥፋት፣ በተለይ ከ2007 እስከ 2009 ዓም ያሉት ዓመታት ሕዝቡ ሊሸከመው … [Read more...] about ወያኔ እንዲህ እያሰበ መሆኑ ጭምጭምታ ተሰማ፤ ዕውነት ከሆነ ጥቅምና ጉዳቱ ምን ይሆን?
የጦር መሳሪያ ዋጋ አሻቀበ፤ ክላሽንኮቭ እስከ 60 ሺህ ብር ይሸጣል፣ መሳሪያ ቁልፍ ሃብት ሆኗል!
ሱዳንና ህወሃት የመሳሪያ ዝውውርን ለመግታት ተስማሙ ትግራይ ክልል ኢትዮጵያን ወክሎ ከሱዳን ጋር ስምምነት አደረገ ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ የተቀሰቀሰዉ አመጽ ማህበራዊ መሰረቱን እያሰፋ በጎንደርና በጎጃም የተለያዩ ዞኖችን፣ ወረዳዎችን፣ የከተማ አስተዳደሮችና የገጠር ከተሞችን ያዳረሰ ህዝባዊ እምቢተኝነት ለመሆን በቅቷል። ይኸው ህዝባዊ እምቢተኝነት በጦር መሳሪያ የታጀበ መሆኑ ደግሞ ከሌሎች የተለየ አድርጎታል። በተለያዩ ማህበራዊ ገጾች፣ የሚዲያ ውጤቶች እንዲሁም "የአማራ ተጋድሎ" በሚል ስያሜ የሚታወቁት ክፍሎች ባቋቋሟቸው መገናኛ መንገዶች በተደጋጋሚ እንደሚገለጸው የሚወድቁ ብቻ ሳይሆን የሚጥሉ የተጋድሎ ሃይሎች እየተበራከቱ ነው። አንዳንዴም የድል ብስራት ያውጃሉ። ትንቅንቁም ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሲያምጽ በምን ያህል መጠን ሊቆጣና ጨቋኙን መደብ … [Read more...] about የጦር መሳሪያ ዋጋ አሻቀበ፤ ክላሽንኮቭ እስከ 60 ሺህ ብር ይሸጣል፣ መሳሪያ ቁልፍ ሃብት ሆኗል!
በአዲስ አበባ ከ45 ሺ በላይ ዕድሜያቸው ከ4-15 ዓመት የሆናቸው ህጻናት አደገኛ ሱሰኛ ሆነዋል
ሱስ አስያዥ ለሆኑ የተለያዩ ነገሮችና እፆች ተጋላጭ የሆኑ ህፃናት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና፤ ጉዳዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አንድ ጥናት አሳሰበ፡፡ “ፊዩቸር ኬር” በተሰኘ ድርጅት የተሰራውና ሰሞኑን ይፋ የተደረገ ጥናት እንዳመለከተው፤ በአሁኑ ወቅት ዕድሜያቸው ለአቅመ አዳም ያልደረሱ በርካታ ህፃናት የተለያዩ ሱሶች ተገዥ እየሆኑ ነው፡፡ እነዚህ ሱሰኛ ህፃናት እስከ እብደት ሊያደርሱ በሚችሉ የአዕምሮ ጤና ችግር ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆን ለተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችም የተጋለጡ ናቸው፡፡ ከሱሰኛ ህፃናቱ መካከል በተለያዩ መንገዶች ራሳቸውን የሚያጠፉ ህፃናት ቁጥርም እየተበራከተ መምጣቱን ጥናቱ አመልክቷል፡፡ እ.ኤ.አ ከ2015 ጀምሮ በተደረገው በዚሁ ጥናት መሰረት፤ በአገሪቱ ያሉ ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ የሚኖሩ ህፃናት እጅግ አደገኛ ለሆኑ ሱሶች ተጋልጠዋል፡፡ በአዲስ አበባ … [Read more...] about በአዲስ አበባ ከ45 ሺ በላይ ዕድሜያቸው ከ4-15 ዓመት የሆናቸው ህጻናት አደገኛ ሱሰኛ ሆነዋል
የአርዮስ ፍሬዎች
“ለሌላ አደገኛ የጦርነት አዋጅ በወገናችን ላይ ታወጀ” በሚል ለተጻፈው መልስ ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ በጎልጉል ድረገጽ ላይ እራሳቸውን ተሃድሶ ብለው በሚጠሩ ነገር ግን እውነተኛ ማንነታቸው ለሰወሩት ወይንም በማንነታቸው ለሚያፍሩት፣ የምንፍቅና አቀንቃኞች መልስ ይሆን ዘንድ ነው። በመምህር ምህረተአብ ላይ ላቀረቡት ትችት ከሞላ ጎደል መልስ ይሆናቸዋል ብዬ አምናለሁ። ጸሃፊው፤ አቤቱታውን ሲያሰማ እንዲህ ይላል፤ ተወልደን ባደግንበት ኦርቶዶክስ በቴ ክርስትያን “የፍቅር ምሳሌ ሊሆኑ በሚችሉ አገልጋዮች ላይ የጦርነት አዋጅ ታወጀብን” ተወልደን ያደግንበት ከማለት፤ ተዘርተን የበቀልንበት ቢል ማንነቱን ይበልጥ ይገልጸዋል ብዬ አምናለሁ። የመወለድና የመዘራት ትርጉሙ ካልገባቸው ለማለት ነው። ሲጀመር ይህች ቤተ ክርስቲያን ባጎረሰች የተነከሰች ለመሆኗ ጸሃፊው እራሱ ይክደዋል ብዬ … [Read more...] about የአርዮስ ፍሬዎች
How do we deal with sociopathic tendencies in our society?
We Ethiopians both in and outside of Ethiopian have been advocating for a change of government there for some time. Well, obviously, we are frustrated not only with the government and its foreign backers but also (equally) with each other for an array of reasons. As a result we are unable to bring about the much needed change for our people and still, being unable to learn from our past wrongful journey, are caught up with inter and intra-ethnic bickering: blaming one another, throwing at each … [Read more...] about How do we deal with sociopathic tendencies in our society?










