ኢትዮጵያ ምጥ ላይ ነች። ከዚህ በፊትም ሁለቴ አርግዛ አዋላጆቿ የሚያደርጉትን ስላላወቁ እናት ብዙ ደም ፈሷት ከሞት አፋፍ ድናለች። የሦስተኛው ምጥ አዋላጅ ኢሕአዴግ ይሳካለት ይሆን? እንዴት እዚህ ደረስን? በዘመናዊ ትምህርትና በምዕራባዊያንና ምስራቃዊያን ፍልስፍናና ርዕዮተ አለም የተቀረፀው የ1960ቹ ትውልድ ኢትዮጵያን እንደሌሎቹ አገሮች የዳበረችና የበለፀገች አገር ለማድረግ ምኞቱና እምነቱ ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ፤ የንጉሱም እድሜ 80ዎቹ ውስጥ ስለነበረ፣ አለምአቀፋዊ ኢኮኖሚያዊ ሂደቶች/የነዳጅ ዋጋ ስለናረና፣ አለምአቀፋዊ ሁለት ግዙፍ የፓለቲካ ጎራዎች ገዝፈው ከመውጣታቸው ጋር ተደምሮ ኢትዮጵያን ከባህላዊ አስተዳደር ወደ ህዝባዊ አስተዳደር ተስፈንጥራ እንደትገባ የሚታገል አብዮታዊ ትግል ተጧጧፈ። አብዮትም ፈነዳ። የተማሪው ንቅናቄ ያስተናገደውና ወደ ውስጡ ያሰረፀው የምስራቃውያን … [Read more...] about የኢትዮጵያ ምጥ
Opinions
የኔ ሃሳብ
ሕዝቤን ልቀቅ!
አሁን በሥልጣን ላይ ያለው የኢትዮጵያ አገዛዝ (የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅት ሕ.ወ.ሃ.ት.) ከ25 ዓመታት በፊት የመንግሥት በትረ ሥልጣንን እንደ ፈረኦን ከጨበጠ ማግሥት አንስቶ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ቀዳሚ ዒላማው በማድረግ የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ተጥሶ መንበሩ ላይ የተቀመጠ ፓትሪያርክ በህይወት እያለ ያለውን ከመንበሩ በማባረርና በማሳደድ በምትኩ ከራሱ ጎሳ መርጦ ፖትሪያርክ አድርጎ ሾመ። ይህ የፖትሪያርክ ሹመት ቀኖናን ቤተ ክርስቲያንን ከመጣስ ባለፈ ፖለቲካዊና ከፖለቲካም የከፋው የዘረኝነት ፖለቲካን (ethnocratic politics) የተከተለ ስለነበር በተቀረው የአገዛዝዙ የዘረኛ መንግሥታዊ መዋቅሮች እንደረደረገው ሁሉ በቤተ ክርስቲያኗ ውስጥም የዘረኝነት መዋቅር እያደገ ሄዶ ለወደፊት ቤተ ክርስቲያኗንም ሆነ አጠቃላይ ሃገሪቱን ለከፋ አደጋ ያጋልጣል በሚል … [Read more...] about ሕዝቤን ልቀቅ!
EPRDF, High time to Act!
Prime Minister Haile Mariam Desalegn in his recent press statement about the current crisis in Ethiopia blamed the regional governors and officials as responsible for exacerbating the problems by not addressing them in time. He said lack of good governance and high rate of unemployment are the major problems that the country is facing now.His party, the prime minister said, came to conclusion that the top officials of the regional states that are facing the strong civil disobedience are … [Read more...] about EPRDF, High time to Act!
የሕወሃት ብጥብጥ እና ሽሽት- ከውስጥ አዋቂ ምንጭ
ሕዝባዊ አመጹ ያመጣውን ቀውስ ተከትሎ በህወሃት ከፍተኛ አመራር ውስጥ ከፍተኛ መበጣበጥ እና የርስ-በርስ ፍጥጫ መከሰቱን ከታመነ የውስጥ አዋቂ ምንጭ መረጃ ደርሶናል። "አመራሩ ክፉኛ ከመከፋፈሉ የተነሳም የርስበርሱ ችግራቸው ላይ ተወጥረዋል" ይላል መረጃው። ቀንደኞቹ የህወሃት አባላት ስርዓቱ እንዳበቃለት ስለተገነዘቡ ንብረት እና ልጆቻቸውን በማሸሽ ላይ ናቸው። ሕዝቡ ሁሉ እንደተፋቸው በግልጽ እየነገራቸው ስለተገነዘቡ፤ የህወሃት የደህንነት አባላት ሕዝቡን ትተው የራሳቸውን ሰራዊት እና ፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሰልሉ ተነግሯቸዋል። "ተጠርጣሪ" የኦህዴድ እና ብአዴን አባላት በነዚህ ሰላዮች ስለተከበቡ በፍርሃት መወጠራቸውን ከራሳቸው አንደበት እየተሰማ ነው። የርስበርስ ውጥረቱ የተከሰተው ወቅታዊ ችግሩን እንዴት እንፍታ በሚለው ሃሳብ ላይ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን በሙሉ በመጥራት … [Read more...] about የሕወሃት ብጥብጥ እና ሽሽት- ከውስጥ አዋቂ ምንጭ
«AmOr!» «አሞር!»
ወደ ዋናው ርዕሴ ከመግባቴ በፊት በቅድሚያ በወያኔ ጥይት በቅርቡ በግፍ ለረገፉት የአገራችን ጀግና ወጣቶች ጥልቅ የሆነ ሀዘኔን እየገለጽኩ፤ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው ፍትህ፤ ዲሞክራሲና ነፃነት ናፋቂው የኢትዮጵያ ህዝብ እግዚአብሔር መጽናናቱን እንዲሰጠው ከልብ እመኛለሁ፡፡ በጉልበት በሚገዙ አምባገነኖች ስር ያለች አገር የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ከጦር ኃይላቸው ባላነሰ ሁኔታ የሚተማመኑበት ስርአታቸውን ይዞ ካቆመው አንዱ ምሰሶ ነው ማለት ይቻላል፡፡ የወያኔንም ስርአት እና ስልጣን ከተሸከሙት ከአምስት ያልበለጡ ምሰሶዎች (the supporting/bearing wall)ውስጥ ይሄ የከፋፍለህ ግዛ ምሰሶ አንዱ ነው፡፡ ሌሎቹ ምሰሶዎች በአጭሩ፦ 1)የጦር ኃይሉ፤ ደህንነቱና ካድሬዎቹ 2)ኤኮኖሚው-ያከማቸው የተዘረፈ ገንዘብ፤ ሀብት ንብረት የኢትዮጵያ መሬት በሙሉ 3)ድርጅቱን ከመነሻው የደገፉትና፤ … [Read more...] about «AmOr!» «አሞር!»
ከትናንት ወዲያ፣ ትናንትና ዛሬ
ዛሬ ላይ ቆሜ ወደኋላ ሳይ የትናንት ወዲያው ይናፍቀኛል፤ ትናንት ወዲያን አይቼዋለሁ፤ አውቀዋለሁ፤ ትናንትንም አይቼዋለሁ፤ አውቀዋለሁ፤ ዛሬንም እያየሁትና እያወቅሁት ነው፤ ከትናንት ወዲያ በጃንሆይ ዘመን የአገዛዙ ነቃፊ ነበርሁ፤ የወደፊቱን የማየት ችሎታ ስለሌለኝ የጃንሆይን አገዛዝ ነቃፊ ነበርሁ፤ በትናንት ወዲያ ላይ በጃንሆይ ዘመን ላይ ቆሜ ዛሬን የማየት ችሎታ ቢኖረኝ የጃንሆይን አገዛዝ ነቃፊ አልሆንም ነበር፤ ትናንትን፣ የደርግን ዘመን ከዛሬው ከወያኔ ዘመን በመሠረቱ እምብዛም የማያለይ በመሆኑ አይናፍቀኝም፤ የዛሬው የወያኔ ዘመን አስመረረኝ፤ ምርር ብሎኛል፤ እንዳልሰደድ ቀዳማዊ ምኒልክ ያለውን ተከታይ ነኝ፤ እንዲህ ብሏል፡-- ‹‹እናቴንና አገሬን እተው ዘንድ አይቻለኝም፤›› እናቴ ‹‹በጡቶቿ አምላኛለችና››፡፡ እናትና አባቴ የኢትዮጵያን ምድር ሆነዋል፤ አባቴ በማይጨው ዘምተው … [Read more...] about ከትናንት ወዲያ፣ ትናንትና ዛሬ
ዓይን እያየ ወደገደል? ምን ይባላል!
በአገዛዙ ወንበር ላይ ተጣብበው የተቀመጡት ሰዎች ሁሉ ብዙ ቢሆኑ ይነጋገሩ ነበር፤ ቢነጋገሩ ሁሉም በየፊናውና በየአቅጣጫው በራሱ ዓይኖች ያየውንና በራሱ ጆሮዎች የሰማውን፣ በራሱ አእምሮ አብሰልስሎ እያቀረበ ክርክር ይፈጠር ነበር፤ ከክርክሩ የሚፈልቀው እሳት ከተለያዩ ሰዎች የሚወረወሩትን ሀሳቦች እያቀለጠ አዲስ መመሪያ ያወጣ ነበር፤ ነገር ግን ተጣብበው የተቀመጡት ተጣብቀው አንድ በመሆናቸው ዓይን የሚያየውና ጆሮ የሚሰማው አንድ ነው፤ አእምሮ ሲጨፈለቅና ሲጣበቅ ሕይወቱን ያጣል፤ ስለዚህም የታየውና የተሰማው ጎዳ ሆኖ ሲቀርብ ውጤቱም ጎዳ በመሆኑ ክርክር የለም፤ ክርክር አለመኖሩ የመካንነት ምልክት ነው፡፡ አገር ተረብሽዋል፤ ሥርዓት ጠፍቷል፤ መደማመጥ ተስኖናል፤ የገነፈለው ስሜት እያቀለጠ ወደሞት ጅረት እየወሰደን እንደሆነ ወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት ገና አልተገነዘቡም፤ የዓለም … [Read more...] about ዓይን እያየ ወደገደል? ምን ይባላል!
ወገናዊ ጥሪ ወገን ለሆነው የትግራይ ህዝብ
ይህን ፅሁፍ ነፃ አስተሳሰብን ከሚያውኩ ግላዊ ባህርያት ነፃ በመሆን ማንበብ ያስፈልጋል። የጎሳ፣ የብሄር ወይም የቋንቋ መለያ አጥር ውስጥ ከቆምን የፅሁፉ አላማም ሆነ ይዘት በውል ላይታየን ይችላል። ቢታየን እንኳን ምናልባት ግምገማችን ሊዛባ ይችላል። ምክንያቱም መልእክቱን ወይም አላማውን የምንገመግመው ከቋንቋችን፣ ከብሄር ማንነታችን ወይም ከትውልድ ቀያችን አንፃር ስለሚሆን ሚዛናችን ወይም ግንዛቤያችን ስህተት ይሆናልና ነው። ሰው መቼም ሲያስብ፣ ሲወስንና እርምጃ ሲወስድ አስተሳሰቡን፣ አወሳሰኑንና እርምጃ አወሳሰዱን በስሜት ሀይል ከሆነ መነሻው፣ መንገዱም ሆነ ግቡ ስህተት መሆኑ አይቀርም። ውጤቱም ጥፋት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበት ቀውስ መነሻው ያስተሳሰብ፣ ያወሳሰንና የድግጊት መነሻችን ነፃ አእምሮ ሳይሆን ስሜት ብቻ ስለነበረ ይመስለኛል። ሰው … [Read more...] about ወገናዊ ጥሪ ወገን ለሆነው የትግራይ ህዝብ
ኦሮሞና አማራ – “ሁለት ዛፎች”!
ኦሮሞ እና አማራ “እሣት እና ጭድ ናቸው” ብላችሁ ክብሪት ለመጫር ለምትቋምጡ የወያኔ ሎሌዎች የሚከተለውን ብትገነዘቡ መልካም ነው፡፡ 1) ኦሮሞ እና አማራ መታየት ያለባቸው እንደ እሳት እና ጭድ ሳይሆን ጎን ለጎን በቅለው ለረጅም ጊዜ አብረው እንዳደጉ ትልልቅ ዛፎች ነው። እነዚህ ዛፎች ለረዥም ጊዜ ተጎራብተው ከመኖራቸውና ከግዙፍነታቸው የተነሳ በመሬት ውስጥ የተሳሰሩት ሥሮቻቸው ምግብ ሊሻሙ ይችላሉ። በአየር ላይ የሚነካኩት ቅርንጫፎቻቸው በንፋስ ጊዜ እርስበእርስ ሊላተሙ ይቻላሉ። ነገር ግን ዛፎቹ ሥር የሰደዱና የተዋሃዱ እንደመሆናቸው መቼም ውሃ አያጡምና፣ እንደ ጭድ ደርቀው በክብሪት እሣት አይቀጣጠሉም። 2) ምናልባት ከሁለቱም ዛፎች ደርቀው የረገፉ ቅጠሎችን እና ጭራሮዎችን ተጠቅማችሁ እሳት መለኮስ ካሰባችሁም ጉዳቱ ለናንተው እንደሚያመዝን እውቁ። የምትለኩሱትን እሳት የንፋስ … [Read more...] about ኦሮሞና አማራ – “ሁለት ዛፎች”!
ECOLOGICAL DEGRADATION, ETHNO-NATIONALISM & POLITICAL CONFLICT IN ETHIOPIA
This article has bearing on the ethno-genesis of the TPLF as an ethno-nationalist movement. Although the alleged "Amara oppression in Tigrai" is projected as the main cause for the emergence of, what has now become, a very virulent Tigrean ethnic nationalism, the underlying problem of ecological degradation in Tigrai which significantly contributed to the ethno-genesis of this movement has been hardly touched upon. It is this salient aspect which I have tried to elucidate in this article. One … [Read more...] about ECOLOGICAL DEGRADATION, ETHNO-NATIONALISM & POLITICAL CONFLICT IN ETHIOPIA










