• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከትናንት ወዲያ፣ ትናንትና ዛሬ

August 29, 2016 09:21 am by Editor Leave a Comment

ዛሬ ላይ ቆሜ ወደኋላ ሳይ የትናንት ወዲያው ይናፍቀኛል፤ ትናንት ወዲያን አይቼዋለሁ፤ አውቀዋለሁ፤ ትናንትንም አይቼዋለሁ፤ አውቀዋለሁ፤ ዛሬንም እያየሁትና እያወቅሁት ነው፤ ከትናንት ወዲያ በጃንሆይ ዘመን የአገዛዙ ነቃፊ ነበርሁ፤ የወደፊቱን የማየት ችሎታ ስለሌለኝ የጃንሆይን አገዛዝ ነቃፊ ነበርሁ፤ በትናንት ወዲያ ላይ በጃንሆይ ዘመን ላይ ቆሜ ዛሬን የማየት ችሎታ ቢኖረኝ የጃንሆይን አገዛዝ ነቃፊ አልሆንም ነበር፤ ትናንትን፣ የደርግን ዘመን ከዛሬው ከወያኔ ዘመን በመሠረቱ እምብዛም የማያለይ በመሆኑ አይናፍቀኝም፤ የዛሬው የወያኔ ዘመን አስመረረኝ፤ ምርር ብሎኛል፤ እንዳልሰደድ ቀዳማዊ ምኒልክ ያለውን ተከታይ ነኝ፤ እንዲህ ብሏል፡–

‹‹እናቴንና አገሬን እተው ዘንድ አይቻለኝም፤›› እናቴ ‹‹በጡቶቿ አምላኛለችና››፡፡

እናትና አባቴ የኢትዮጵያን ምድር ሆነዋል፤ አባቴ በማይጨው ዘምተው በጥይት ቆስለዋል፤ የመርዙንም ጋዝ በትንሹ ሳንባቸውን ሳይጠብሰው አልቀረም፤ ይቺን እናትና አባቴ አፈር የሆኑላትን አገር ትቼ መሰደዱ ስለማይሆንልኝ እየመረረኝ የመድኃኔ ዓለምን ምሕረት እጠብቃለሁ፡፡

torture123ለምን የጃንሆይ ዘመን ይናፍቅሃል? ለሚለኝ የምሰጠው መልስ የሚከተለው ነው፤ በጃንሆይ ዘመን ኢትዮጵያ የታሪክ ክብርዋ ርዝራዥ ነበረ፤ ስለዚህ የኢትዮጵያ ሕዝብ ራሱን ችሎ በነጻነት የኖረ፣ በተደጋጋሚ የመጡበትን የተለያዩ ወራሪዎች እያሳፈረ የመለሰ ቆራጥ፣ ጀግናና ኩሩ ሕዝብ መሆኑን ዓለም በሙሉ አምኖ የተቀበለው ጉዳይ ነበር፤ በዘመኑም ከተባበሩት መንግሥታት ጦር ጋር ኮሪያ የዘመተው የኢትዮጵያ ጦር ከአሥራ ሰባት አገሮች አንዱ ቢሆንም አንድም ምርኮኛ፣ አንድም ሬሳ በጠላት እጅ ሳያስገባ የተመለሰ ብቸኛ ጦር ነበር፤ ያኮራል፡፡

ከኢትዮጵያ ለመውጣት ቪዛ ማገኘት ቀላል ነበር፤ በዚያን ጊዜ ምን ዓይነት ኢትዮጵያዊ ነው ለመሰደድ የሚያስብ? አሜሪካ በየዓመቱ የሚመድበውን የኢትዮጵያን የስደት ድርሻ የሚጠቀሙበት ጥቂቶች ግሪኮችና አርመኖች ነበሩ፤ አርባ ሺህ ግድም ጦር ይዛ የምትፈራ፣ ደሀ ሕዝብ አቅፋ የምትኮራና የምትከበር፣ ጮሃ ሳትናገር የምትሰማ አገር ነበረች፤ እምነት የሚጣልበት የጨዋ ሕዝብ አገር ነበረች፤ ይህ ነው የናፈቀኝ! police12

ዛሬ በየጋዜጣው ላይ የማነበውና የማየው ፎቶግራፍ አሳፈረኝ! ውርደቱ አንገፈገፈኝ! ከሁሉም ይበልጥ ደግሞ ምንም ማድረግ አለመቻሌ፣ ኢምንትነቴ ያንገበግበኛል፤ አንድ ወጣት በባቡር መንገድ ላይ ወድቆ አምስትና ስድስት ፖሊሶች እየተሻሙ በዱላ ሲደበድቡት፣ በጫማቸው ቦታ ሳይመርጡ ሲረግጡት እነዚህ ከኛው የተወለዱ፣ በእኛው ባህልና እምነት ያደጉ፣ ለሕዝብ ደኅንነት የተሰማሩ ናቸው ወይ? የሚፈጽሙት ግፍ ጀግንነት ይመስላቸው ይሆን ወይ? ልጆች ያላቸው ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው እነዚህን የግፍ ምስሎች በጋዜጣም ሆነ በቲቪ ሲያዩ እንደሚያማቸው ይገነዘባሉ ወይ?

በሚያዝያ 30/1997 በሚልዮን የሚቆጠር ሕዝብ በጨዋነት ወጥቶ በጨዋነት ተበተነ፤ ለምን አይቀጥልም? እስከመቼ ተፈራርተን እንኖራለን? በሠለጠነ መንገድ መነጋገር አልቻልንም፤ በሰላማዊ ትግል መነጋገር አልቻልንም፤ በግድ ወደሕገ አራዊት መግባት አለብን?

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ነሐሴ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule