• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓይን እያየ ወደገደል? ምን ይባላል!

August 29, 2016 04:47 am by Editor 2 Comments

በአገዛዙ ወንበር ላይ ተጣብበው የተቀመጡት ሰዎች ሁሉ ብዙ ቢሆኑ ይነጋገሩ ነበር፤ ቢነጋገሩ ሁሉም በየፊናውና በየአቅጣጫው በራሱ ዓይኖች ያየውንና በራሱ ጆሮዎች የሰማውን፣ በራሱ አእምሮ አብሰልስሎ እያቀረበ ክርክር ይፈጠር ነበር፤ ከክርክሩ የሚፈልቀው እሳት ከተለያዩ ሰዎች የሚወረወሩትን ሀሳቦች እያቀለጠ አዲስ መመሪያ ያወጣ ነበር፤ ነገር ግን ተጣብበው የተቀመጡት ተጣብቀው አንድ በመሆናቸው ዓይን የሚያየውና ጆሮ የሚሰማው አንድ ነው፤ አእምሮ ሲጨፈለቅና ሲጣበቅ ሕይወቱን ያጣል፤ ስለዚህም የታየውና የተሰማው ጎዳ ሆኖ ሲቀርብ ውጤቱም ጎዳ በመሆኑ ክርክር የለም፤ ክርክር አለመኖሩ የመካንነት ምልክት ነው፡፡

አገር ተረብሽዋል፤ ሥርዓት ጠፍቷል፤ መደማመጥ ተስኖናል፤ የገነፈለው ስሜት እያቀለጠ ወደሞት ጅረት እየወሰደን እንደሆነ ወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት ገና አልተገነዘቡም፤ የዓለም ሕዝብ በሙሉ ተገንዝቦታል፤ በወንበሩ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡት በሚገነዘቡበት ጊዜ የሞት ጅረት አጥለቅልቆናል፤ መድኅን የሚመጣው ከሞት በፊት ነው፤ የዱሮ አዝማሪ እንዳለችው፡–

አንጀቴ ተቆርጦ ከሆዴ ከወጣ፣
እንግዲህ ሀኪሙ ምን ሊቀጥል መጣ!

ሳምሶን ‹‹ውጽዒ ነፍስየ ምስለ ነፍሶሙ፤›› ብሎ ምሰሶውን ገፍቶ እንደጣለው ዛሬም በወንበሩ ላይ የተጣበቁት ምሰሶውን ገፍቶ የመጣልና የሦስት ሺህ ዓመታት የኢትዮጵያን ታሪክ ለማፈራረስ ጉልበቱ እንዳላቸው ያምኑ ይሆናል፤ ‹‹ውጽዒ ነፍስየ ምስለ ነፍሶሙ›› ለማለትና ውጤቱንም ለመቀበል ከቆረጡ ያለምንም ጥርጥር በቂ ጉልበት አላቸው፤ ነገር ግን ይህ ጉልበት የተባረከና የተቀደሰ አይደለም፤ ዝናብ እንደሚወርድበት ክምር ጨው ነው፤ ዝናቡ ከጉልበት ቁጥጥር ውጭ ነው፤ በዚያ ላይ አንድ የሁሉም አገር ታሪክ ያረጋገጠው እውነት አለ፤ አሸናፊ ይጠናከራል፤ ተሸናፊ ይዳከማል፤ ሕዝብ ተሸናፊ ሆኖም አያውቅ፡፡

በዚያ ላይ ወደእምነት ደረጃ ከፍ ስንል ኃያል እምኃያላን የሆነ አምላክ አለ፤ በጉልበታቸው የሚታበዩትን ይታገሳቸዋል እንጂ ለመጨረሻ ድል አያበቃቸውም፤ የደካሞቹንም ስቃይና መከራ የሚያበዛው የድል አክሊል አዘጋጅቶላቸው ይሆናል፤ ጉልበተኞች ከዕብሪታቸው ሲጸዱና የእግዚአብሔርን ኃያልነት ሲቀበሉ በነሱ ላይ ድልን ለተጎናጸፉት ያስተምራሉ፤ የጉልበተኛ ሥርዓት ወድቆ የሕግ ሥርዓት ይተከላል፤ አሸናፊም ተሸናፊም በሕግ ጥላ ስር ይተዳደራሉ፡፡

አሸናፊም ተሸናፊም አንድ ዋና ነገር ቦግ ብሎ እንዲታያቸው እመኛለሁ፤ ትግላቸውም ሆነ ውጤቱ የግል አይደለም፤ ከመሀከላቸው የአምባ-ገነንነት ዝንባሌ ያላቸው ሰዎች ቀስ በቀስ ትግሉን የግል እያደረጉ ሄደው በመጨረሻ ድሉንም የግል ያደርጉታል፤ ሌላ ቀርቶ ቤተ-ሰቦቻቸውንም ይረሳሉ፤ አሸናፊም ሆነ ተሸናፊ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ የብዙ ሰዎችን ትብብርና ከባድ መስዋእትነትን የከፈሉ ሰዎችን የያዘ ነው፤ እነዚህ በብዙ መንገድ ብዙ ዓይነት መስዋእት የከፈሉ ሰዎች ለሚቀጥሉት ትውልዶች የሚያወርሱት ብዙ ነገር አለ፤ ራሳቸውን ሀብታም ማድረጋቸውንና ሰዎችን እንደፈለጉ ሲቆርጡና ሲፈልጡ መኖራቸውን ማንም እንደውርስ አይቀበላቸውም፤ ዘመን አልፎበታል፤ ታሪክም አይሆንም፤ የተጋድሎ ታሪካቸው፣ ለነጻነት፣ ለእኩልነትና ለአገር ባለቤትነት የሚያበቃና ለተከታይ ትውልዶች ሁሉ አርአያ የሚሆን ታሪክ በኩራት የሚተላለፍ ይሆናል፡፡

በቀል፣ ጭካኔና በስሜት መገዛት ውሎ አድሮ ያጋልጣል፤ የሀብታሙ (አያሌው)ና የተመስገን (ደሳለኝ) ተገቢውን ህክምና ማጣትና መሰቃየት በምድርም በሰማይም ያስቀጣል፤ ይህንን ባህል አድርገን እንዳንቀጥል እሰጋለሁ፤ አእምሮአችንን ጡንቻ ብቻ ስናደርገው የማሰብ ሥራውን ያቆማል፤ ጠላት ለሚባለው ሰው የተመኙለት ገደል ላይ ዓይኖችን ተክሎ መራመድ ራስን ወደዚያ ገደል ማስገባት ነው፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ነሐሴ 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Wondefraw says

    August 30, 2016 08:23 am at 8:23 am

    Long life for u it sensible writing now they should think in different mind.

    Reply
  2. Naji says

    September 1, 2016 01:37 am at 1:37 am

    Wishing you good health,many more years with strength and energy, you are truly and educator and national figure. You are absolutely correct when you said that those who are in leadership positions are guided and manipulated by a single mind attached to a single brain. If there had been honest dialogue and consensus all the messes we are seeing right now would not have happened. Greed, when it becomes boundless it damages the brain and cripples the senses. I guess greed like leprosy diseases kill the senses. I watch, I see, I hear what is going on in every corner of the country. I am sorry, I can not find any other explanations and believe that is coming from sensible entity, thinking rational being.
    I am sorry, I am angry, sad and upset I do not what tell those arrogant, senseless, immoral, hateful bunch of groups.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule