የኔልሰን ማንዴላን ሕልፈት በማስመልከት አውስትራሊያ ከሚገኘው ኤቢኤስ ሬዲዮ የአማርኛ አገልግሎት ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል፡፡ መንግሥቱ ለሬዲዮው በሰጡት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፣ በእሳቸው በትረ ሥልጣን ወቅት ማንዴላ የአገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሽልማት ከመጎናፀፈቸውም ባሻገር፣ የአንድ መቶ ሺሕ ዶላር ገንዘብ ተበርክቶለቸዋል፡፡ ይህና ቀሪው ንግግራቸው እንዲህ ቀርቧል፡፡ ‹‹ማንዴላና የተወሰኑ ተከታዮቻቸው ወደ ኢትዮጵያ በስውር መጥተው፣ ወታደራዊ ሥልጠና አግኝተውና እግረ መንገዳቸውን ሞሮኮን ጐብኝተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ማምራታቸውን ተገንዝቤያለሁ፡፡ ‹‹በዚያን ጊዜ አሜሪካኖች በአማካሪነት ኢትዮጵያ ውስጥ ነበሩ፡፡ እስራኤሎችም ነበሩ፡፡ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ግንኙነት የነበራቸው በመሆኑ የማንዴላን ኢትዮጵያ ውስጥ መገኘትና ወታደራዊ ሥልጠና በመከታተል እግር በእግር እየተከታተሉ መረጃ … [Read more...] about “የወደፊቷ ደቡብ አፍሪካ ከማንዴላ ጋር መያያዟን እጠራጠራለሁ” ፕሬዚዳንት መንግሥቱ
Right Column - Primary Sidebar
“ድምጽ አልባው አስዛኝ የወገኖቻችን ለቅሶ በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ግቢ!”
በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ ሁለት የጸጥታ ጥበቃዎችን ጨምሮ ከ13 በላይ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በስሩ እንደሚገኙ የሚነገረለት ይህ የመዝናኛ ማዕከል ከተቆርቆረ ሁለት አስርት አመታትን ቢያስቆጥርም ከቅርብ ግዜ ወዲህ በተለያዩ ሰንካል ምክንያቶች ከትርፋማነት ይልቅ ኪሳራ፤ ከእድገት ይልቅ ወደቀትን እያቀነቀነ አሁን ላለበት ደረጃ መድረሱን የሚናገሩ እማኞች በሰራተኞቹ ላይ እይተፈጸመ ያለው በደል ከመቸውም ጊዜ በላይ እየከፋ መምጣቱን ገልጸዋል። ይህ የኮሚኒቲ ማህበር ካፍቴሪያ ማዕከል ዛሬ ላለበት አሳፍሪ ደረጃ ምክንያት መሆኑ የሚነገረው በተለያዩ ወቅቶች በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ጀርባ ታዝለው ያለችሎታቸው አመራር የሚሆኑ ግለሰቦች ከኮሚኒቲው ካፍቴሪያ ሰራተኞች ጋር በቀረበት ተነጋገረው የካፍቴሪያውን መሰረታዊ ችግር ለመቅረፍ የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ከማህበሩ … [Read more...] about “ድምጽ አልባው አስዛኝ የወገኖቻችን ለቅሶ በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ግቢ!”
ሰማያዊ ፓርቲ በአሜሪካ
ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት …
ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም ሕገ-መንግስቱ የፀደቀበት ቀን ነው፡፡ ይህንንም ተከትሎ በመንግስት አሳሳቢነት እልፍ ሲልም አስገዳጅነት ህዳር 29 በየዓመቱ ከተለያዩ ጎሳ የተወጣጡ ሰዎች ተሰባስበው በመንግሰት ሹማምንቶች ፊት በአደባባይ ከበሮ የሚደለቅበት ቀን ነው፡፡ ይሁን እንጂ የአብዛኛው ኢትዮጵያዊያን መልካም ፍቃድና ተሳትፎ ባልታየበት የፀደቀው ህገ መንግስት በብዙሃን ዘንድ ተቀባይነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ከቃሉ አጠቃቀም ጀምሮ እስከ አከባበሩ ክብረ በዓል አብዛኛዉ ሰው እኔንም ጨምሮ ግድ አይሰጠንም፡፡ ‹‹ይህ ህገ-መንግስቱን የመነዳ ተግባር ነው!!!›› ከገዢው መንግስት ተደጋግሞ የሚሰማ ለመፈረጅ ወይም ለመከሰስ የሚጠቀሙበት ቃል ነው፡፡ አንድ ወዳጄ እንዲህ አለኝ ‹‹ይህ ህገ መንግሰት ዝም ብሎ የተደረደረ ብሎኬት ነው እንዴ የሚናደው?›› በማለት ሲተች … [Read more...] about ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት …
“ታህሳስ 5 ከሰአት በኋላ ለመገደል ፈርሜአለሁ”
ታህሳስ 5 ከሰአት በኋላ ለመገደል ፈርሜአለሁ ገጽ 410 ይላል የስደተኛው ማስታወሻ፤ አቶ ተስፋዬ ገብረአብ "ጓደኛዬ" የሚለው ሆላንዳዊ ስለያዘው የሞት ቀጠሮ ሲያብራራ፤- ለሚቀጥለው … ማስታዉሻ መጽሀፉ ይረዳው ዘንድ ሆላንድ ውስጥ የሞት ቀጠሮ እንዴት እንደሚያዝ ከዚህ በታች አብራራለሁ፤ ከዚያ በፊት ግን ስለ ስደተኛው ማስታወሻ የምለው ከዚህ የሚከተለውን ነው፤ ጫልቱ ብሎ የሰየማትን ተዋናይ እዛው የቡርቃ ዝማታው ላይ ቢከታት ኖር ገጸ ባህርይዋ ከዛ ጋር ይሰምርለት ነበር፡፡ ነገር ግን ከአለቆቹ የደረሰው ትእዛዝ አማራና ኦሮሞን ማፋጀት የኢትዮጵያን ስማ ማጥፋት በመሆኑ የግድ መካተት ነበረባት፤ በጎሳ እምነት የተለከፉ ሰዎች አመለካከታቸው ወደሌላ ሰውነት እንደተሰራጨ ካንሰር ነው፤ ቢነግሩአቸው ቢያስረዷቸው አይጠሩም፤ የተስፋዬ ገብረአብ ተማሪዎች በቀደም ሳውዲ አረቢያን ተቃውሞ ሰልፍ ላይ … [Read more...] about “ታህሳስ 5 ከሰአት በኋላ ለመገደል ፈርሜአለሁ”
አፍሪካዊው ኮከብ
ጀግናው አሸለበ፣ ደከመው ተረታ ሞት አይቀርምና፣ የማታ የማታ፤ ምን ብርቱ ቢሆኑ፣ ሺ መካች ቢሆኑ ሰው አያልፍ አይገደፍ፣ ተዛቹ ተቀኑ፤ አፍሪካ ሆይ መጥኔ፣ አንድ ወልደሽ ላጣሽው ተንግዴ መሸበሽ፣ በማን ትዘከሪው? በማንስ ትጠሪው? ማንዴላ ብረቱ፣ የሮቢን ደሴቱ የዘረኞች ዋግምት፣ የጥቁር ኩራቱ- ተንግዲህ የለህም፣ ታሪክ ነበርክና ታሪክ ነህ ተንግዴ፣ ላትመጣ እንደገና፤ ዓለም አሸርግጂ፣ ቱቢት አስመቺና ደረት እየመታሽ፣ ”ወይ ልጄን...” በዪና፤ አንበሳሽ ቀን ጣለው፣ ይውጣልሽ ሀዘንሽ ሙሾሽን ደርድሪ፣ ማቅ ልበሽ እባክሽ ማንዴ እኮ ነው ሃጁ፣ ሌላው እንዳይመስልሽ፤ ባፍሪካ ሰማይ ላይ፣ የበራው ኮከብ ተወርዋሪ ነበር፣ ዐይንን የሚስብ፤ ባፍሪካ ሰማይ ላይ፣ የነጋው ጀምበር ለወገኑ ነበር፣ ብርሃንና አድባር ለጠላቱ ነበር፣ መራር እንደ ኮሶ ገፍናኝ … [Read more...] about አፍሪካዊው ኮከብ
ላምበሎቼ
በሕይወት እያላችሁ... ላለመዋደድ ተፋቅዳችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ባንዲት ጉድጓድ ታድማችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ምስጥና አፈር ላስማማችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ማንም ምንም ላይለያችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ተቃቅፋችሁ የኋላ ኋላ ኋላ... ላሸለባችሁ... ለናንተ... ላምበሎቼ ለጋሼ ኃይሌ ፊዳ ለጋሼ ብርሃነ መስቀል ረዳ እነሆኝ እላለሁ... ይህን ያገር እዳ፡፡ (በአበራ ለማ) “ጥሎ ማለፍ” ለተባለው የታሪካዊ ልቦለድ መጽሐፌ መታሰቢያ ቋጥሬው የነበረ - 2003 ዓ.ም. … [Read more...] about ላምበሎቼ
ኢትዮጵያን በሙስና ከሚታወቁ የዓለም አገሮች ተርታ ያሰለፈው ሪፖርት ይፋ ሆነ
ትናንት ኅዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም. በመላው ዓለም ይፋ የሆነው የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ተቋም የሙስና አመላካች ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ከሙስና ጽዱነት ተርታ ውጭ ከሆኑና በሙስና ተግባር በከፍተኛ ደረጃ ከሚፈረጁ አገሮች አንዷ ሆና መገኘቷን ይፋ አደረገ፡፡ ሪፖርቱ በሚከተለው የሙስና መለኪያ ሚዛን መሠረት፣ ከሙስና ጽዱ የሚባሉ አገሮች ከዘጠና እስከ መቶ ነጠብ የሚያገኙት ናቸው፡፡ በአንፃሩ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል፣ የሙስና ጎሬ ሆነዋል ተብለው የሚታሰቡ አገሮች ደግሞ ከመለኪያው ከ50 በመቶ በታች የሚያስመዘግቡት ናቸው፡፡ በመንግሥት ተቋሞች ውስጥ ከፍተኛ ሙስና ተንሰራፍቶባቸዋል ተብለው ከተለዩት ውስጥ ኢትዮጵያ 33 ከመቶ የመለኪያውን ነጥብ በማስመዝገብ ከከፍተኛ ሙስኞች ተርታ እንደምትሰለፍ የትራንስፓረንሲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡ ከ177 አገሮች ውስጥ … [Read more...] about ኢትዮጵያን በሙስና ከሚታወቁ የዓለም አገሮች ተርታ ያሰለፈው ሪፖርት ይፋ ሆነ
ETHIOPIANS IN LONDON ECHO THE PLIGHT OF THEIR COMPATRIOTS IN SAUDI ARABIA
London residents of Ethiopia came out again on 2 December 2013 to protest in front of the Saudi Arabian Embassy for the 2nd time in less than 10 days. Although we are aware that some Ethiopians have been transported to Addis Ababa, there are still tens of thousands of Ethiopian immigrants in captivity in that Kingdom, held in subhuman conditions, without food, and sanitary for women. Horrendous news trickling out to the rest of the world through various sources tells gross violation of human … [Read more...] about ETHIOPIANS IN LONDON ECHO THE PLIGHT OF THEIR COMPATRIOTS IN SAUDI ARABIA
አቶ ታምራት ላይኔ እንዳደመጥኳቸው
የቀድሞው የኢትዮጵያ የሽግግር ዘመን ጠቅላይ ሚኒስትር ኋላ ላይ ደግሞ የኢፊድሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ታምራት ላይኔ ከአውስትራሊያዊው የኤስ.ቢ.ኤስ የአማርኛ ራዲዮ ባልደረባ ጋዜጠኛ ካሳሁን ሰቦቃ ጋር ያደረጉትን በሶስት የተከፈለ ሰፊ ቃለመጠይቅ በአንክሮ ተከታተልኩት:: አቶ ታምራት ብዙ ነገሩን፤ ብዙ ደበቁንም:: ከምንም በላይ አቶ ታምራት በረጋ አንደበት ከቁጣ እና ከብስጭት የጸዳ ቃለምልልሳቸውን በዚህ አጋጣሚ ሳላደንቅ አላልፍም:: እርግጥ ነው ቃለመጠይቁ ሰፊ ቢሆንም በደምሳሳው አቶ ታምራት በመለስ ዜናዊ ተታለልኩ የሚል ቃና ያለው መልዕክት እንዳስተላለፉ ነው የተረዳሁት:: ከምንም ነገር በላይ አሁን ከሚከተሉት ሃይማኖት ጋር አያይዘው ቢሆንም ኮሚኒዝም አንደርዮት አለም በፍጹም የስሕተት እና የጥፋት መንገድ አንደነበር በአደባባይ መናገራቸው ለኔ ታላቅ ቁም ነገር ሁኖ … [Read more...] about አቶ ታምራት ላይኔ እንዳደመጥኳቸው










