• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልዑል በሉዓላዊ መንግስት ይሰለጥናል!

September 15, 2016 11:36 pm by Editor Leave a Comment

‶…ልዑሉ በሰዎች መንግስት ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን እንዳለውና እነዚህንም መንግስታት ለወደደው እንደሚሰጥ እስክታውቅ ድረስ…″ ዳን.4፡32

ሉዓላዊ መንግስት (sovereign nation) በሌሎች ቅኝ ግዛት ወይም ባርነት ስር ያልወደቀ ራስ-ገዝና ነጻ መንግስት ሲሆን የሃገሪቱ የአመራር አካላት እንደመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካላት ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ የህዝቡም ሰላምና የሁለንተና እድገት በሃገሪቱ አመራር አካላት ብቃትና ቅንነት ይወሰናል፡፡ ሉዓላዊነት ሌሎች አካላት በአንድ ሃገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ (meddle) ዋስትና እንደሚሰጥ በማሰብ አንዳንድ መንግስታት በማንአለብኝነት ከእግዚአብሔርም ከሰውም የሚያነካካ እርምጃ ሲወስዱ ይስተዋላሉ፡፡

ከነዚህም አንዱ ለትምህርታችን በቅዱሱ መጽሀፍ በስፋት የተተረከልን የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነጾር ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔር ባርያዬ/አገልጋዬ እያለ ደጋግሞ የሚጠራውና ስኬትን ያበዛለት ንጉስ የዙፋኑንና የስኬቱን ምንጭ ዘንግቶ በብዙ ትዕቢትና ነውር ሲመላለስ የምድር ነገስታት ገዢ ከሆነው ከልዑል (the most high) እግዚአብሔር ዘንድ ፍርድ ወጣ—‶መንግስት ከአንተ ዘንድ አለፈች″ (ዳን.4፡31)፡፡ እንደጥፋቱም ጥልቀት አስተማሪ የሆነ ተጨማሪ ቅጣት ተበየነበት—‶ለሰባት ዘመን እንደአውሬ በዱር ተሰድደህ ትኖራለህ″ (ዳን.4፡32)፡፡ ንጉሱን ለዚህ ሁሉ ቅሌት ያበቃው ከላይ በርዕሱ እንደተጠቀሰው ልዑል እግዚአብሔር በሰዎች መንግስት ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን እንዳለውና ሹም ሽርም በእጁ እንደሆነ አለማወቁ ነበር፡፡

ልዑል በሉዓላዊ መንግስት እንዲሰለጥን የሃገሬ መሪዎች ያውቁ ይሆን?

መሰልጠን ማለት ያገባኛል በሚልና በባለቤትነት መንፈስ በሃይልና ስልጣን በሰዎችና አሰራራቸው ላይ ጣልቃ መግባት ማለት ነው፡፡ እውነት ነው የአፍሪካ ህብረትም ሆነ የተባበሩት መንግስታት በሉዐላዊ መንግስት አመራርና አሰራር በቀጥታ መሰልጠን አይችሉም፡፡ ነገር ግን ልዑል እግዚአብሔር የኢህአዲግን መንግስት ጨምሮ በሁሉ ይሰለጥናል፡፡ ‶ከፍ ካለው በላይ ከፍ ያለ ይመለከታልና″ (መክ.5፡8) ልዑል በሰው ልብ የታሰበውን፣ በጓዳና በአደባባይ የሚደረገውን ያውቃል፡፡ እርሱን ፈርተን ህዝቡንም አክብረን በመልካም ብናስተዳድር ስልጣናችን ይጸናል/ይረዝማል፤ መተካታችንም በክብር ይሆናል፡፡

እንደባቢሎኑ ንጉስ እግዚአብሔርን ባለመፍራትና ሰውንም ባለማፈር በምንወስዳቸው እርምጃዎች ልዑሉ ሊንቀን፣ መንግስትን ሊነጥቀን፣ በግል ሊቆነጥጠን፣ ለወደድነው ሳይሆን ለወደደውም ስልጣኑን ሊሰጥ ይችላል፡፡ በተለይም እንደኢትዮጵያ ባሉ በጸሎት የሚበረቱ የእምነት ሰዎች ባሉበት ሃገር የልዑል ጣልቃ ገብነት ይፈጥናል፡፡

በገዛ ስልጣኑ መንግስትን ከደርግ ነጥቆ በሃገራችን የሾማችሁ የኢህአዲግ አመራር አካላት እያደገ ከመጣው የማንአለብኝነት አካሄድ ተመልሳችሁ በህዝቡና በእግዚአብሔር ፊት ቅንነት ያለበትን እርምጃ እንድትወስዱ አበረታታለሁ/እጸልይማለሁ፡፡ ናቡከደነጾር ተጸጽቶ ከክፉ ስራው በተመለሰ ጊዜ መንግስቱን እንደመለሰለት/እንዳጸናለት ምናልባትም ሽንገላ የሌለበትን የተሃድሶ እርምጃችሁን አይቶ ልዑል ህዝቡን ዳግም ሊያስገዛላችሁና የስልጣን ዘመናችሁንም ሊያረዝም ይችላል፡፡ በልበ-ደንዳናነት በአመጽ ብንጸና ግን ያሰማራነው ጦር እንኳን እግዚአብሔርን የህዝቡንም እንቅስቃሴ ሊያስቆም አይችልምና ለዘር ማንዘር የሚተርፍ ጠባሳ ትታችሁ እንዳታልፉ በጌታ ፍቅር አሳስባለሁ፡፡

በዚህ አጋጣሚ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች እንደባለአደራ ነብያቶችንና ሊቃውንቱን አማክራችሁ የእግዚአብሔርን ሃሳብና የህዝቡ/መንግስት ምላሽ ምን ሊሆን እንዲገባ ምክር እንድትሰጡ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡

‶እግዚአብሔር ሆይ መድኃኒትህን እጠብቃለሁ″ ዘፍ.49፡18
ዶ/ር ሳምሶን—ከሃገር ቤት


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule