• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይድረስ ለብአዴን አባላት

September 5, 2016 07:47 am by Editor Leave a Comment

ወያኔዎች “ሕዝቡን አረጋጉ፤ ሰላም ፍጠሩ” ወዘተ. እያሉ ቁም ስቅላችሁን እያበሏችሁ እንደሆነ እንረዳለን፡፡ እናንተም እኛም አሳምረን እንደምናውቀው ግን የሕዝባችን ሰላም ያደፈረሰው ራሱ ወሮበላው የወያኔ ቡድን ነው፡፡ በሕዝባችን ላይ የዘር ማጥፋት ጦርነት አውጆ ንጹሐንን የሚፈጀው፣ እንቡጥ ሕጻናትን የሚጨርሰው፣ በሺሕዎች የሚቆጠሩ የአማራ ወጣቶችን በየእስር ቤቱ አጉሮ ዘግናኝ ቶርቼር የሚፈጽመው፣ በርካታ ንጹሐን አማሮችን ከረሸነ በኋላ የወልቃይት ጠገዴን ጉዳይ ሁለቱ ክልሎች ተወያይተው ይፈቱታል እያለ በደማችን ላይ የሚቀልደው፣ የሰላም ጉባኤ እያለ እየሰበሰበ በብሶት የሚናገሩትን ወገኖቻችንን እየነጠለ የሚያስረው ወዘተ ወዘተ ራሱ ነብሰ ገዳዩ ወያኔ እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ሕዝባችን ሰላም ወዳድ ነው፡፡ የሰላም ጠንቅ፣ የሽብርና የሁከት አባት ወያኔ ነው፡፡ ስለሆነም ሰላም እንዲሰፍን ከተፈለገ መፍትሔው በጣም አጭርና ግልጽ ነው፡፡

ሰላም እንዲሰፍን ካስፈለገ መብታቸውን ስለጠየቁ ብቻ በየአካባቢው የታሰሩትና እንደተለመደው ወያኔ እጅግ ዘረኛ በሆነ መንገድ ቶርቼር የሚፈጽምባቸው ልጆቻችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፈታት ይኖርባቸዋል፡፡ ሰላም እንዲሰፍን ካስፈለገ በግፍ የተወሰደው የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት መሬት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መመለስ ይኖርበታል፡፡ ሰላም እንዲሰፍን ካስፈለገ ወያኔ ከሕዝባችን ጫንቃ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲወገድና ሕዝባችን በወያኔ ምስለኔዎች ሳይሆን በልጆቹ እንዲመራ ያስፈልጋል፡፡ ሰላም እንዲሰፍን ካስፈለገ የአማራ ሕዝብ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚገባውን ሥልጣን ማግኘት ይኖርበታል፡፡ ከዚህ ውጪ ያለው ሁሉ ተራ የወያኔ ማዘናጊያና የክህደት መንገድ ነው፡፡ ወሮበላው ቡድንና የዚህ ቡድን ተላላኪ የሆነው ኃይለማርያም ደሳለኝ የወልቃይት ኮሚቴዎች ለትግራይ ክልል ያቀረቡት ጥያቄ የለም ሲሉ በአገርና በሕዝብ ላይ ክህደት መፈጸማቸው ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን የወልቃይትን ጉዳይ ሁለቱ ክልሎችና ድርጅቶች ተወያይተው ይፈቱታል የሚባለው ባዶ ማዘናጊያ እንጂ ከዚህ ነብሰ ገዳይ ቡደን የሚገኝ መልካም ነገር የለም፡፡

የወያኔ መንገድ የሰላም መንገድ አይደለም፤ ሆኖም አያውቅም፡፡ ወያኔ የልጆቻችን ገዳይ የሆነ ደመኛችን እንጂ የሰላም አጋራችን አይደለም፡፡ ከዚህ ወሮበላ የጥፋት ኃይል ጋር ሰላምም ኅብረትም የለንም፤ አይኖረንም፡፡ ጠላቶቻችን የፈለገውን ያህል ቢያደቡም፣ የፈለገውን ያህል ልጆቻችን ቢያስሩና ቢገድሉም፣ የፈለገውን ያህል የዘር ማጥፋት እርምጃ ቢወስዱም፣ ከዚህ በኋላ ወደኋላ መመለስ ብሎ ነገር አይኖርም!! የአባቶቹን የአይበገሬነትና የጽናት መንፈስ የወረሰ ደም መላሽ ትውልድ ተፈጥሯልና በወያኔ ነብሰ ገዳይ ጦር የተፈጁት እንቡጥ ሕጻናት ደምም በከንቱ ፈሶ አይቀርም!!

ሕዝባችን አጋዚ የተባለው ነብሰ ገዳይ ጦር ግድያ ሳያንበረክከው በያለበት የሚዋደቀው፣ በወያኔ አገዛዝ ሲደርስበት የቆየው ይህ ነው የማይባል በደል አንገፍግፎት መሆኑን እናንተም እኛም አሳምረን እናውቃለን፡፡ የትግሉ አደራጅና መሪ (ወሮባለው ወያኔና የዚህ ነብሰ ገዳይ ቡድን ተላላኪ የሆነው ኃይለማርያም ደሳለኝ እንደሚለው የተወሰኑ ጽንፈኛ ዲያስፖራዎች ሳይሆኑ) ራሱ ሕዝቡ መሆኑንም በሚገባ እናውቃለን፡፡ ከዚህ ሐቅ በመነሳት የትግሉን መሠረታዊ ጥያቄ ስትደግፉ እንደቆያችሁ እንገነዘባለን፡፡ በዚህ ይበልጥ ሊጠናከር በሚገባው መልካም እርምጃችሁም የብዙዎችን አድናቆት አትርፋችኋል፤ ብዙዎቻችን ኮርተንባችኋል፡፡ አሁንም በዚህ ሕዝባዊ አቋማችሁ እንድትቀጥሉ ያስፈልጋል፡፡ ከዚህ አቋማችሁ እንድታፈገፍጉ ብዙ ግፊት እንደሚደረግባችሁ ብንገነዘብም፣ የወያኔ መንገድ የጥፋት መንገድ መሆኑን ከእናንተ በላይ የሚያውቀው የለምና የጥፋቱን መንገድ እንደማትመርጡ ደግሞ ባለሙሉ ተስፋ ነን፡፡

ሕዝባችን ሰላም ወዳድ ነው፡፡ ሕዝባችን ከየትኛውም ሕዝብ ጋር ጠብ የለውም፡፡ በነብሰ ገዳዩ የወያኔ ቡድን ፊታውራሪነት በየቦታው ሲዘመትበት ኖረ እንጂ የአማራ ሕዝብ በየትኛውም ሕዝብ ላይ አልዘመተም፤ አይዘምትም፡፡ ሐቁ ይህ ሆኖ ሳለ ነብሰ ገዳዩ የወያኔ ቡድን አማራ ክልል በሚኖሩ ትግሬዎች ላይ ጥቃት ተፈጽሟል እያለ መሠረተ ቢስ አሉባልታ እያወራና እናንተም ይህንን በሬ ወለደ እንድታስተጋቡ ብዙ ግፊት እያደረገባችሁ እንደሚገኝ እናውቃለን፡፡ ሆኖም ይህንን የወያኔ የጥፋት ወጥመድ በሚያስደንቅ ሐቀኝነትና ቁርጠኝነት ሳትቀበሉት በመቅረታችሁ ደግሞ ብዙዎች ኮርተውባችኋል፡፡ ይህ ትልቅ ከፍታ ነው፡፡ ከዚህ የሕዝብ ልጅነት ወደባንዳነት መውረድ የታሪክ አተላ መሆን ነውና በጀመራችሁት መንገድ እንድትገፉ ያስፈልጋል፡፡

ባንዳነት የአማራ ሕዝብ ዕሴት አይደለም፡፡ ሕዝባችን የሚታወቀው በአርበኝነቱ ነው፡፡ ሆኖም ሁልጊዜም ከውስጣችን ሆነው የሚያስጠቁን ባንዳዎችንና ምንደኞችን ደግሞ አጥተን አናውቅም፡፡ ትናንትና አባቶቻችን ሲያስጠቋቸው የነበሩት እነዚህ እንክርዳዶችና የታሪክ አተላዎች ናቸው፡፡ ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታትም ቢሆን ሕዝባችን በመሠረተው አገሩ ባይተዋር ሆኖ ሲፈናቀል የኖረው፣ ልጆቹ በግፈኛው ወሮበላ ቡድን ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩና ሲገደሉ የከረሙት በእነኝህ ምንደኞች አማካይነት መሆኑን እናንተም እኛም አሳምረን እናውቃለን፡፡ ስለሆነም የሕዝብ ልጅ የሆናችሁት የብአዴን አባላት እነዚህ ምንደኞችና የወያኔ ተላላኪዎች ለራሳችሁም እንደማይተኙላችሁ አውቃችሁ፣ ከሕዝቡ ጋር ሆናችሁ ልትመነጥሯቸው ይገባል፡፡ 40 ሚሊዮን ጀግና ሕዝብ ከኋላችሁ እያለ የምትፈሩበት ምንም ዓይነት ምክንያት የለም፡፡ ከሕዝባችሁ ጋር በማበራችሁ የሚመጣባችሁ መከራ እንኳ ቢኖር ለሕዝባችሁ ስትሉ የምትከፍሉት መከራ በታሪክ ፊት የማይሞት ስም ያስገኝላችኋል እንጂ ተጋድሏችሁ እንዲሁ ከንቱ ሆኖ አይቀርም፡፡ ከንቱዎች ለፍርፋሪ ሲሉ የሕዝባችን ግንባር ቀደም ጠላት ከሆነው የወያኔ ቡድን ጋር ኅብረት የመሠረቱት ምንደኞች ናቸው፡፡

እንግዲህ ብአዴንና የብአዴን አባላት በታሪካችሁ አግኝታችሁት የማታውቁት ዕድል ከፊታችሁ ተደቅኗል፡፡ ምርጫው የራሳችሁ ነው፡፡ ወይ እንደአቡነ ጴጥሮስ፣ አበበ አረጋይ፣ በላይ ዘለቀ፣ ኃይለማርያም ማሞ፣ አሞራው ውብነህ፣ ሙሉዓለም አበበ፣ ጄኔራል ተፈራ ማሞ፣ ኮ/ል ደመቀ … ከሕዝብ ጋር ቆማችሁ፣ በሕዝብ ላይ የመጣውን መከራ አብራችሁ ትታገሉና ደማቅ ታሪክ ትጽፋላችሁ፤ አልያም ደግሞ እንደ አቡነ አብርሐም፣ መላኩ ተፈራ፣ ታምራት ላይኔ፣ ካሳ ተክለብርሃን፣ ዓለምነው መኮንንና ሌሎች የለየላቸው ባንዳዎችና ጸረ ሕዝቦች ሕዝባችሁን ታስጨርሱና በታሪክ ትቢያነት ትመዘገባላችሁ፡፡ የሰላም ኮንፈረንስ እያላችሁ በምታካሒዱት ስብሰባ እንደምትረዱት የአማራ ሕዝብ ፍላጎት አርበኝነቱን እንድትመርጡ፣ መከራውንም ደስታውንም ከሕዝባችሁ ጋር እንድትጋሩ ነውና የሕዝቡን አደራ ተቀበሉ፡፡ (ምንጭ: Muluken Tesfaw)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule