A CALL TO THE PEOPLE OF ETHIOPIA: What will we leave to the next generation—a gift or a curse? This question is critically important; however, it is equally important to know whether or not our—or someone else’s—individual or collective efforts, will produce the desired outcome. These are key questions to ask ourselves today as we face the many warning signs that signal the growing instability in Ethiopia. Change appears to be inevitable, but what kind of change do we want and how can we get … [Read more...] about WHAT WILL WE LEAVE TO THE NEXT GENERATION — A GIFT OR A CURSE?
Right Column - Primary Sidebar
የታሪክ እርማት በየገፁ
በቅርቡ "የትምህርት ሚኒስቴር" 400 ተማሪዎች በፈተና ቅጾች ላይ ኢትዮጵያውያን አይደለንም ብለው ሞሉ የሚል መረጃ አወጣ ሲባል ሰምቼ ቆሽቴ አርሮ ነበር። የተናደድኩበት ምክንያት የመንግስት የ26 አመት የጸረ-ኢትዮጵያዊነት ፖሊሲ አፈጻጸም ይህን የመሰለ ውጤት እንዴት ሊያመጣ ቻለ በሚል ሳይሆን እንዴት ዛሬ ስርአቱ በሞት አፋፍ ላይ ቆሞ እንኳን የሩብ አመት ድካሙ ከንቱ መሆኑን አይገባውም ብዬ ነበር። እንጂ ኢትዮጵያን የማትመስል ኢትዮጵያን ለመፍጠር ሌት ተቀን ያለመታከት ሲዘራ የኖረው የጎሳ መርዝ 400 የተበላሹ እጽዋትን አበቀለ ቢሉኝ እንኳን ጉዳታችን ከዚህ በላይ አልሆነ ብዬ በእፎይታ እተነፍስ ይሆናል እንጂ ብዙም አላዝንም። መንግስት ግን ላመታት ስራው ከንቱነት ዋቢ የሆነውን መረጃ ዛሬም ሳያፍር እንደመልካም ዜና ማወጁ ያስገረመኝ መሆኑን ግን መሸሸግ አልችልም። የዛሬ ርእሴ ግን … [Read more...] about የታሪክ እርማት በየገፁ
«ባልበላው ጭሬ አፈሰዋለሁ!»
«ባልበላው፣ ጭሬ አፈሰዋለሁ!» ይህ አባባል እኔ ካልተጠቀምኩበት፣ ሌሎች እንዳይጠቀሙበት አደረገዋለሁ፤ ለእኔ ካልሆነ፣ ለማንም እንዲሆን አልሻም፤ የእኔ መገልገያ ካልሆነ፣ ሌሎች ሊገለገሉበት እንዳይችሉ አበላሸዋለሁ፣አፈርሰዋለሁ፣ብለው ለሚያስቡ የጥፋት ሰዎች ዕይታ፣ በዶሮዋ ተመስሎ የተነገረ የብልሆች ዕውነት የማስጨበጫ ዘዴ ነው። አዎ ! ይህን አባባል በሌላ አባባልም አበው ይገልጹታል። «እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል» ሲሉ። እነዚህ አባባሎች እኔ ወይም እኛ ካልተጠቀምንበት፣ ለእኛ ካልሆነ ሌሎች ሊጠቀሙበት አይገባም ብለው የሚያስቡ ሰዎች የሕይዎት መርሕር እንደሆነ አባባሎቹ ያስረዳሉ። የትግሬ-ወያኔ አስተሳሰብና አጠቃላይ ዓላማ በነዚህ አባባሎች የተቃኘ ነው። የወያኔው ዘር የማይመራት ኢትዮጵያ መኖር የለባትም፣ እኛ ያልነው ካልሆነ፣ኢትዮጵያ መበታተን አለባት ብለው በማመን፣ ባለፉት ፳፯ … [Read more...] about «ባልበላው ጭሬ አፈሰዋለሁ!»
“ወይዘሪት ስሜን” የደባርቅ ቆንጆ
በደባርቅ ወረዳ በተደረገ የቁንጅና ውድድር የደብር ቀበሌ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሪት አልማዝ ተስፋ ማርያም "ወይዘሪት ስሜን" በመሆን አሸንፋለች። (ምንጭ: Addisgazetta) … [Read more...] about “ወይዘሪት ስሜን” የደባርቅ ቆንጆ
ሽሽት እና አባዱላ ገመዳ
ከሰሜን እና ከበስተ-ምስራቅ አቅጣጫ እየነፈሰ ያለው አውሎንፋስ መርከብዋን እያናጋት ይገኛል። ጫፍ ላይ ጉብ ያሉትን አስተናጋጆች እያንጠባጠበ የሚገፋው ሃይል እየበረታ መጥቶ፣ አሁን ከካፒቴኑ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ይመስላል። ይህ ሁላችንንም የሚያስማማን መራራ ሃቅ ነው። ችግሩ እዚህ ላይ አይደለም። ግን ... እየሰመጠ ካለው ከዚህ መርከብ ለማምለጥ የተገኘችውን ቀዳዳ እየተጠቀሙ የሚሾልኩትን ሁሉ "ጀግና" ብለን ለመጥራት እንደምን ይዳዳን? ራስን ማዳን እና ሃገርን ማዳን፤ በሰማይና በምድር መሃከል ያለ ርቀትን ያህል የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ዘንግተነው ከሆነ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህ ስራዓት "በስብሷል" ብሎ ከተናገረ 10 አመታት አልፈውታል። ከ 26 ዓመታት በኋላ ደግሞ እነሆ ህወሃት ከርፍቶ መርገፍ ጀመረ። ችግሮቹ ግን እጅግ እየተባባሱ እንጂ እየተሻሻሉ አልመጡም። ይህ ስርዓት ዛሬ … [Read more...] about ሽሽት እና አባዱላ ገመዳ
የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ፣ ተግዳሮቶቹና የመፍትሄ ኣሳብ
የሰው ልጅ ማህበራዊና ግላዊ ተፈጥሮ ስላለው ለማህበራዊ ኑሮውና ለግላዊ ኑሮው የተለያዩ ጠገጎችን እያበጀ ይኖራል። እነዚህ የሚሰራቸው ጠገጎች ለግል ህይወቱም ሆነ ለማህበራዊ ህይወቱ ወሳኝ ናቸው። ሰው የዚህን ዓለም ኑሮውን ለመግፋት ከሚያስችሉት መሳሪያዎች ኣንዱ እነዚህ ጠገጎቹ ናቸው። የሰው ልጅ በህይወቱ የሚፈጥራቸው እነዚህ ጠገጎች ሃይማኖታዊ ወይም ባህላዊ ወይም ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ትርፍ ያስገኙለታል። ታዲያ ይህ የሰው ልጅ በዓለም ላይ ከሚፈጥራቸው ጠገጎች መሃል ከፍተኛውና ጠንካራው ሃገር የሚባለው ጠገጉ ነው። በርግጥ ከዚህ ኣልፎ ዛሬ ጊዜ ሌላ ከፍ ያለ የጋራ የዓለም ጠገግ ህዝቦች ኣበጅተው ስያሜውን ደግሞ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ብለውታል። ነገር ግን የሰው ልጅ ከቀን ተቀን ህይወቱ ጋር በጣም የተሳሰረው ጠገግ አገር ሲሆን ለዚህ ጠገግ የተለያዩ ስምምነቶችን ኣስፍሮ በዚህ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ፣ ተግዳሮቶቹና የመፍትሄ ኣሳብ
የአምባሳደር ኸርማን ኮኸን ምክርና የኢትዮጵያ ጥቅም
የኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠል በተደረገበት ጊዜ ታላቅ ሚና ከነበራቸው ባለስልጣኖች አንዱ አምባሳደር ኸርማን ኮኸን እንደነበሩ ይታወቃል። በምእራቡ አለም ደግሞ የቀድሞ ባለስልጣኖች ከጡረታ በዄላም ቢሆን ቁልፍ ሚና ሲጫዎቱ ይስተዋላል። በመሆኑም፤ አርሳቸው በዚሀ ጉዳይ ላይ ህሳበ ሲስንዘሩ ትኩርት መሰጠቱ አስፈላጊነቱን የጎላ ያደርገዋል።ከዚህ በመነሳት ስሞኑን አምባሳደር ኮኸን ይዘውልን ብቅ ያሉትን ጉዳይ አንዳንድ ገጽታዎች በዚህ ጽሁፍ ውስጥ እመረምራለሁ። አምባሳደር ኸርማን ኮኸን በኤርትራ (ሻቢያ) ላይ የተባበሩት መንግስታት የጣለው ማእቀብ ሊነሳ ይገባዋል ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ አሁን በተባበሩት መንግስታት ውስጥ ያላትን ቦታ ተጠቅማ እንዲያውም ስለማእቀቡ መነሳት በግንባር ቀደምትነት ዋናዋ ጠያቂ መሆን አለባት ሲሉ እንደተናገሩ አፍሪካን ኒውስ የተሰኘው ድረ ገጽ ላይ … [Read more...] about የአምባሳደር ኸርማን ኮኸን ምክርና የኢትዮጵያ ጥቅም
ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]
የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]፤ 2009ዓ.ም፤ አ/አ፤ አታሚ አልተገለጸም፤ 10ዶላር፣ 100 ገጽ የማለዳ ድባብ፣ ለ በዕውቀቱ ሥዩም አራተኛ የግጥም ሥራው ነው። መጽሐፉ ሦስት ክፍሎች አሉት፤ “ግጥምና የዘመን መንፈስ” [ገጽ 5-9]። ግጥሞች [ገጽ 17-91]። “ጉደኛ ስንኞች” እና “ሙሾና ባለቅኔ” [ገጽ 93-100]። መድብሉ፣ ቀድሞ ካስነበባቸው ላይ አዳዲሶች ተጨምረውበት የተዘጋጀ ነው [ገጽ 9]። የትኞቹ አዳዲሶች እንደሆኑ አልተገለጸም። ግጥም ከስድ ንባብ ይልቅ የግል እይታዎችን፣ ማህበራዊ ትረካዎችን ለመቋጠርና ለማስታወስ ይረዳል። ቅኝቱና አወራረዱ ለጆሮና ለዐይን ይጥማል። ግጥም ማህበራዊ እሴት አለው፤ በሥልጣን ለሚባልጉ እርምት ለመስጠት [“ይድረስ ለጥም ሚኒስትር”፣ ቁ.71]፣ የሕይወትን አጭርነት ለማሳሰብ፣ ከሚታየው ውጭ የላቀ ተስፋ እንዳለ ለማወጅ፣ የግለሰብ … [Read more...] about ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]
ድንበር: “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል”
ስለኢትዮጵያ ድንበር መፍረስ፤ መገሰስና መጠገን በተደረጉበት ዘመናት ሁሉ የነበረች አሁንም ታፍና በመታዘብ ላይ ያለች፤ ወደፊትም የምትኖር ይህች ጥንታዊት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፤ አሁን ህዝቧ ስለሚነጋገርበት ስለ ድንበር ምን ትላለች? የሚለውን ለመዳሰስ ይህችን ጦማር ሳዘጋጅ በውስጧ የተሸከመቻቸውን ሀሳቦች በተጻፉባቸው ቋንቋዎች እንዳሉ አቅርቤያቸዋለሁ። ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚሰነዘረውን አፈና ለመከላከል የጠቀስኳቸውን ሀሳቦች በተጻፉባቸው ቋንቋዎች እንዳሉ በማቅረቤ (ግእዙን ግን ትርጉሜዋለሁ) ይቅርታ በመጠየቅ ያጎደልኩትን እየሞላችሁ፤ የተሳሳትኩትን እያረማችሁ ታነቧት ዘንድ በታላቅ ትህትና አቀረብኩላችሁ። መግቢያ “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል” በሚል ርእስ ይህች ጦማር የፈለቀችበት ዘመን፤ ኢትዮጵያን ከጎረቤት አገር የሚያዋስኗት ድንበሮችና፤ በውስጥም ዜጎቿ … [Read more...] about ድንበር: “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል”
‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ
"አከ’ሲ" አለ ያገሬ ሰው፣ ከሰሞኑ ‘አጃኢብ’ ያሰኘውን የአዜብ መስፍን ወሬ ሲሰማ። አዜብ ልምድ ያላት ውሸታም እንጂ ልምድ ያላት ኮሜዲያን አትመስልም ነበር። ከሚሚ ስብሃቱ ጋር በያዝነው ሳምንት የተወኑት ድራማ ግን ጦሽ አርጎ ያስቃል። መቼም ጥርስ እንጂ ልብ አይስቅ። ፈንድሻም'ኮ ልቧ እየተቃጠለ ነው ፊትዋ ሚፈካው። ሴትየዋ አይኗን ሳይሆን ቅንድቧን በጨው አጥባ "ምንም የለኝም ግን ይወረስ" ነው የምትለው። መለስ የባንክ ደብተር ይቅርና መንጃ ፈቃድ እንኳ የለውም ስትል የቀለደችበት ወቅት ሩቅ አይደለም። እርግጥ ነው አዜብ በራስዋ ስም እንኳን ሕንጻ፣ ሲም ካርድም ሊኖራት አይችልም። ጥሩ ጋዜጠኛ አልገጠማትም እንጂ፣ ቢገጥማት፣ "እመኑኝ ልጃገረድ ነኝ!" ብላ እያለቀሰችም ቢሆን ለማሳመን ትሞክር ነበር። ልጆቼን እየተበደርኩ ነው የማስተምረው ብላ በተናገረች ሰሞን ኤ.ቢ.ሲ … [Read more...] about ‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ








![ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/10/dibab-191x300.png)

