በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ አንምሳደር ዘነበ ከበደ የሚመሩ የመንግስት ሹማምንቶች ጅዳ ከተማ ውስጥ መሽገዋል ያሏቸው 80 ሺህ ኢትዮጵያውያን እጃቸውን በሰላም ካልሰጡ የመንፉሃው አይነት እልቂት እንደሚጠብቃቸው ሲያሙዋርቱ! ሪያድ በኢትዮጵያው አንምሳደር መሃመድ ሃሰን የሚመራው ቡድን የሚያሰማው «ጅብ ከሄድ ውሻ ጮህ ጥሪ» ድብቅ አጀንዳ ያለው መሆኑ ተገለጸ ! ከ9 ሚሊዮን በላይ የተለያዩ የውጭ ሃገር ዜጎች በጥገኝ ነት እንደሚኖሩባት የምትታወቀው ሳውዲ አረቢያ በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ ሃገር ዜጎች የመኖሪያ ፈቃዶቻቸውን እንዲያስተካከሉ የተሰጠ የ 7 ወር የግዜ ገደብ መጠናቀቅን ተከትሎ የሳውዲ ጸጥታ ሃይሎች ከ 3 መቶ ሺህ በማይበልጡ ኢትዮጵያውያኑ ላይ ብቻ ባነጣጠረው እርምጃ እስካሁን ቁጥሩ በወል ለማይታወቅ ወገናችን አሰቃቂ ህልፈተ ህይወት ስቃይ እና መከራ ምክንያት መሆኑ … [Read more...] about በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያኑ ላይ ያነጣጠረው ዘመቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል!
Left Column
Explaining the Ethiopian outmigration: Incentives or Constraints?
In both theory and practice, pull and push factors drive migrants out of their own countries of origin. The factors are complex but they are in general categorized as: (a) demand-pull factors, represented by better economic opportunities and jobs in the host (new) country; (b) supply-push factors, represented by the lack of economic opportunities, jobs, and economic downturns, political oppressions, abuses of human rights by home country governments, religious intolerance (constraints), war, … [Read more...] about Explaining the Ethiopian outmigration: Incentives or Constraints?
COLONIALIZM Vs FREDDOM IN HISTORY OF ETHIOPIA
In my point of view the history of Ethiopia, colonialism and fighting for freedom and unity have long relation in the nation’s history .Literal definition of colonialism is exploitation by a stronger country of weaker one or the use of the weaker country's resources to strengthen and enrich the stronger country. In addition to this, policy and practice of a power in extending control over weaker peoples or areas is also categorized as colonialism. I just wanted to mention some of these leaders … [Read more...] about COLONIALIZM Vs FREDDOM IN HISTORY OF ETHIOPIA
አይ አበሻ! አበሻና ልመና፦ አንድ
በዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፤ ለአበሻ፣ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው፤ እንዲያውም ከልመና ውጭ የሆነ ኢትዮጵያዊ ኑሮ የለም ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፤ ስለዚህም ልመና ባህላዊ ጥበብ ሆኖአል፤ አንዳንድ አላዋቂዎች፣ አንዳንድ አዋቂዎችም አንዳንዴ እየተሳሳቱ ልመናን እንደነውር ይገልጹታል፤ ልመና ነውር አይደለም፤ ለጨዋ ልጆችማ አንዳንድ አጥንትን የሚያበላሽ ሥራ ከመሥራት ለምኖ መብላት ክብር ነው፤ ይህ ባህላዊ ጥበብ ያልገባቸው የድሬ ዳዋ ለማኞች ብቻ ናቸው፤ እጃቸውን እየዘረጉ ‹‹እስቲ አሥር ብር ስጠኝ!›› ይላሉ! በጫት ሞቅ ሲላቸው መቶ ብር ይጠይቃሉ፤ የድሬ ዳዋ ልመና መሆኑ ነው! የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ቄሶቹ ምንም ይስበኩ በተግባር እንደሚታየው ጽድቅ የሚገኘው በልመና ነው እንጂ … [Read more...] about አይ አበሻ! አበሻና ልመና፦ አንድ
አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለምኒሊክና ስለኢትዮጵያ
የአጼ ምኒሊክን መቶኛ የሙት አመት መከበር ምክንያት በማድረግ በ DW ሬድዮ በተደረገው ጥያቄና መልስ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፣ ዶ/ር ሓይሌ ላሬቦና ዶ/ር ሹመት ሲሳይ (የታሪክ ተመራማሪዎች) ቃለ መጠይቅ ተደርጎ በሚሰጠው መልስ ላይ ስለ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተናገሩት ላይ አስተያየቴን አቀርባለሁ። አንባቢያንን ቃለመጠይቁን ቢያዳምጡ ጥሩ ነው ባይ ነኝ፤ ሁለቱ የታሪክ ምሁራን ትምህርታዊ ትንተና ይሰጣሉና፡፡ ውሸት ሲደጋገም እውነት ሊመስል ይችላል፤ በተለይም የአገራችንን የኢትዮጵያን ታሪክ ለማያውቁ እውነታው ምን እንደሚመስል መረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ። አቶ ቡልቻ ኦሮሞ ከባሌ እየተስፋፋ ሲመጣ ልብነ ድንግል እንዳይስፋፋ አቆሙት ይላሉ፡፡ ለምን ይህን ምሳሌ እንዳቀረቡም ግልጽ አይደለም ለሳቸው ትንታኔ የማይመች በመሆኑ፤ ለዛውም በአጼ ልብነ ድንግልና በኦሮሞች መሀከል ስለነበረው ግኑኝነት … [Read more...] about አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለምኒሊክና ስለኢትዮጵያ
የጋምቤላ ክልል በህንድና በሳዑዲ ኩባንያዎች ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠየቀ
የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ሦስት የውጭ አገር ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር ታይቶባቸዋል፣ የፕሮጀክት አፈጻጸማቸውም ደካማ ነው በሚል የፌዴራል መንግሥት ዕርምጃ እንዲወስድ ጠየቀ፡፡ የክልሉ መንግሥት በቅርቡ ለግብርና ሚኒስቴር፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በጻፈው ደብዳቤ የህንድ ኩባንያዎች የሆኑትን ካሩቱሪንና ቬርደንታ ሃርቨስት፣ እንዲሁም የሼክ መሐመድ አል አሙዲ ኩባንያ የሆነው ሳዑዲ ስታር የእርምትና የማስተካከያ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ጠይቋል፡፡ በጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ጋትሉዋክ ቱት ኮት ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው፣ የክልሉ መንግሥት በነዋሪዎች አስተያየት ላይ ተመርኩዞ የራሱን ግምገማ አካሂዷል፡፡ ክልሉ ባካሄደው ግምገማ በተለይ እነዚህ ሦስት የውጭ አገር ኩባንያዎች ከፍተኛ ችግር እንደታየባቸውና የፕሮጀክት አፈጻጸማቸውም ደካማ መሆኑን … [Read more...] about የጋምቤላ ክልል በህንድና በሳዑዲ ኩባንያዎች ላይ ዕርምጃ እንዲወሰድ ጠየቀ
የነፃነት አባት
ታ ሪኩ ገናና፤ ስራው የለው አቻ ላ ሰበበት ጉዳይ፤ የሌለው ፍራቻ ቁ ጣን ቂም በቀልን፤ ያጠፋ ጥላቻ ማ ንዴላ ታላቁ፤ የነፃነት ጮራ ን ጥረ መብረቅ ሆኖ፤ አፍሪካን ያስጠራ ዴ ሞክራሲ እንዲያብብ፤ ተስፋውን ሰንቆ ላ ሰበው አላማ፤ ቆሞ ነበር ታጥቆ የ ህይወት ዘመኑ፤ ቢሆንም መራራ ነ ፃነት አላብሷል፤ ስሙን የሚያስጠራ ፃ ድቅ የሆነ ሰው፤ እያለ በሕይወት ነ ውና ተግባሩ፤ መልካም ነገር መስራት ት ዕዛዙን ፈጽሟል፤ በእድሜው ዘመናት ዓ ለም መቆያ ናት፤ ተቀባይ እንግዳ ባ ህሪዋ መራር፤ ወሳጅ በሞት እዳ ት ልቅ ትንሽ ሳትል፤ ድንገት የምትከዳ ና ልን አይባልም፤ ማንዴላም ተመለስ ቸ ሩ ፈጣሪያችን፤ የታላቁን ሰው ነፍስ ው ለታ ይክፈላት፤ ወደሱ ስትደርስ … [Read more...] about የነፃነት አባት
ማንዴላን በተመለከት ለግማሽ ዓመታት የተደበቅ ምስጢር
ኔልሰን ማንዴላ የደቡብ አፍሪካ የፀረ-አፓርታይድ (የዘር-መድሎ) ተዋጊ አርበኛ መሆናቸው ይታወቃል። በደቡብ አፍሪካ ዘረኛ መንግስት ለእስር የተዳረጉት ኢትዮጵያ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና ወስደው እንደተመለሱ ነበር። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ 1962 ዓም ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ኢትዮጵያ ፓስፖርት በመስጠት አጋርነቷን የገለፀች ብቸኛ ሀገር ነበረች። ከዘመናት በኃላ ማንዴላ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ወቅት የግድያ ሙከራ ሴራ ተደርጎ እንደነበር ሚስጥሩን ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ ይዘው የቆዩ በቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ ዘመን የኢትዮጵያ ፖሊስ መኮንን ዛሬ ጥቅምት 15/2006 ዓም ለመጀመርያ ጊዜ በሸገር ራድዮ የዜና እወጃ ላይ ገልፀዋል። ሻምበል ጉታ ዲንቃ በንጉሡ ዘመን የፖሊስ መኮንን ነበሩ። ማንዴላን በከፍተኛ ሚስጥር እንዲጠብቁ ኃላፊነት ከተሰጣቸው ጄኔራል ታደሰ(የማንዴላ አሰልጣኝ … [Read more...] about ማንዴላን በተመለከት ለግማሽ ዓመታት የተደበቅ ምስጢር
በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)
ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡ የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡ ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ? ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ? ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው … [Read more...] about በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)
አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤ ሁለት
አበሻ ድግስ ይወዳል፤ ድግስ የሚወደው መብላትና ማብላት ስለሚወድ ነው፤ ለመብላት የአበሻ ምክንያቱ ብዙ ነው፤ ልጅ ተወለደ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ክርስትና ተነሣ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ አገባ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ሞተ ብሎ መብላት ነው፤ አበሻ ሰው ቀብሮ ሲመለስ በንፍሮ ይጀምርና ቀስ በቀስ ወደሌላው ይተላለፋል። ሃይማኖትም ቢሆን ለመብላት ካልሆነ የነፍሱ ጉዳይማ በጣም ሩቅ ነው፤ ሕያዋን ለነገሥታት፣ ሙታን ለካህናት ይገብራሉ፤ በሚለው መመሪያ መሠረት ግብር መቀበል ያለ ነው፤ ክርስቶስ ተወለደ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ተጠመቀ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ሞተና ተቀበረ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ተነሣ መብላት ነው፤ ማርያም አረገች መብላት ነው። ማኅበርም የሚጠጣው (የሚበላው ለማለት ነው፤) ለመብላት ነው፤ አምላክ በተለያዩ ስሞቹ፣ ቅድስት ማርያም በተለያዩ ስሞችዋ፣ መላእክት፣ ቅዱሳን፣ … [Read more...] about አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤ ሁለት










