• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቃ! በለን አምላክ (say us enough! O’ God)

December 8, 2013 10:07 pm by Editor 1 Comment

ያ የምትወደው ፤ ያ የምታሞካሸው

ልጆቸና ሕዝቤ ፤ እያልክ ያከበርከው

መከራ አፈናቅሎት ፤ ከሀገሩ ከቀየው

ከአሕዛብ ደጅ ወድቆ ፤ ግፍ ሰቆቃ ቆላው፡፡

የጭንቅን ልክ ዓየ ፤ ሞት በዓይነት ቆጠረ

የሰቆቃን ጣራ ፤ ከፍ ብሎ በረረ

ሞትን ተላመደ ፤ ንቆም ተዳፈረ

በእሱ እየተበላ ፤ በእሱ ላይ ፎከረ

የአውሮችን አውሬነት ፤ ተበልቶ አጋለጠ

ድብቁን አወጣ ፤ ነፍሱን ለሀቅ ሰጠ፡፡

   ምን ዓይነት ፍጥረቶች ፤ ምን ዓይነት ጉዲራ

   እውን ሰዎች ናቸው ? የሆኑ የእጅህ ሥራ ?

   ወይስ ሰይጤ እንዳለው ፤ እኔ ነኝ ፈጣሪ

   ይሆኑ ይሆን የሱ ፤ የዚያ እርኩስ መሠሪ

   በሁለ ነገሩ ፤ እሱን አስመስሎ

   እንደራሱ አድርጎ ፤ ፈጥሯቸው አንቦልቡሎ ?

   ወይስ ከነገዱ ፤ ከሆኑት እንደሱ

   ሥጋ ለብሰው መጡ ? ሰው መስለው ሊያረክሱ

   ሕዝብህን በመቅጣት ፤ አንተን ለመበቀል

   ልጆች እንዳይኖሩህ ፤ ከርስትህ በመንቀል

   ካልሆነ እንዴት ታዲያ ፤ ሰው ሆነው የአዳም ዘር

   ሰብአዊ ሕሊና ፤ እንዴት አጡ ፍቅር ?

   ጥቂት ሐዘኔታ ፤ ሩኅሩኅ መሆን ገር

   እውን ከዚህ እርጉም ዘር ፤ ከእኩያን ልቡና

   ጽድቅ ይወጣል ብሎ ፤ ሰው ያምናል ሊቀና ?

   ካልሆነ የዋህ ጅል ፤ ዕውቀት የገደፈ

   በሥጋዊ ጥቅም ፤ ልቡ የተነደፈ

   የዝሙት ጥማቱን ፤ ሊያረካ የወደደ

   ያማሩትን ሁሉ ፤ መርጦ እያጠመደ

   በሴት ለመጫወት ፤ በአንድ ቤት አጉሮ

   አንጋግቶ ለመንዳት ፤ በእንስሳ ተፈጥሮ

   ሴት ሰው እንዳልሆነች ፤ እንደ እቃው ቆጥሮ

   የእሱ መጠቀሚያ ፤ ሆና የሱ ቋጠሮ

   የራሷን ፍላጎት ፤ አሳጥቶ ቀብሮ

   እሷም ልክ እንደሱ ፤ ሰው መሆኗ ቀርቶ

   እንደ ሰውነቷም ፤ እኩል መብቷን ነስቶ

   ጨቁኖ ለመግዛት ፤ ለመርገጥ አፍኖ

   የሚሻ ማስበርገግ ፤ እንደ ባሪያ አባክኖ

   ጾም ሳይልም ፍስክ ፤ ለመክተት ጮማ እርጎ

   በቅቤ እንቁላሉ ፤ ለመውዛት መግምጎ

   ገደብ ሳይኖርበት ፤ ለመድለብ ጠራርጎ

   ይሄን ይሄን ምቾት ፤ ኃጢአት ነው ሳይባል

   ማግኘት የፈለገ ፤ ራሱን የሚያታል

   ይሄ ዓይነት ተላላ ፤ አዎ እሱ ይሆናል ፡፡

   ታዲያ እሱ ምን ያርገው ፤ ከአውሬ ቢሆን አቻ

   ሆድ እንዲህ ሲሞላ ፤ ሲፈረጥም ጡንቻ

   ባዶ መሆኑ አይቀር ፤ ጭንቅላት ተራቁቶ

   ለማሰብ ተስኖት ፤ ሰብአዊነት አጥቶ

   ከእጁ የወደቁትን ፤ ከወልደ ሳጥናኤል

   በእስር ቤት አጉሮ ፤ በምድር ላይ ሲዖል

   ሕፃናት አልቀሩ ፤ አሮጊት ሕሙማን

   ሴቷ አልቀረች ወንዱ ፤ ደፍረው አረከሱን

   ብረት እያጋሉ ፤ በአፈ ማኅጸኗ

   በወንዱም ፊንጢጣ ፤ ወዮ ወዮ ቀኗ

   በዘይት መላጡ ፤ በፎቅ መወርወሩ

   የሰው ልጅ እንደ በግ ፤ በሰይፍ መመተሩ

   በረሀብና ጥም ፤ ሲሰቃይ በጠኔ

   ተሰዶ መግባቱ ፤ ሆኖበት ኩነኔ

   ብልቱን ሲቆርጡት ፤ ሲያስጓራው ሰቆቃ

   የስቃዩን ጩኸት ፤ የጣሩን ድምፅ ሲቃ

   መስማት የሚናፍቁ ፤ ሁሌ እንደ ሙዚቃ

   እያዩ የሚያሽካኩ ፤ እንደ አዝናኝ ድለቃ

   ስንቱ ጉድ ተነግሮ ፤ ቢወራ አያበቃ፡፡

ታዲያ እነዚህን ፤ ጭካኔ የተሞሉ

ግእዛነ አእምሮ ፤ ሕሊና አልባ ሁሉ

ትንሽ ከርኅራኄ ፤ ቅንጣት ያልታደሉ

ግብረ-ገብነትን ፤ ጽድቅን የሚጠሉ

እንዴት ብየ ልመን ፤ ሰዎች ናቸው ሲሉ

ሰብአዊ መለያ ፤ ሳይዙ ቢምሉ

ከቶ እንዴት ይሆናል ፤ ነው ሌባ ለአመሉ

ውስጥ የሌላቸውን ፤ እንዲያው ሲያስመስሉ

ግን ሰውን ነው ጌታን ? ማንን ያታልላሉ?

   ራሔል ስታለቅስ ፤ ጩኸት ስታሰማ

   የሰቆቃ እንባዋን ፤ ያየኸው ከራማ

   ምን ነው ጨከንክብን ፤ ፍጹም ድምፅህ ጠፋ

   የረድኤት ክንድህ ፤ ርቆን ቀን ከፋ

   ሽ ራሔሎች ጮኸው ፤ ደም እያመነጩ

   ከዓይን ወደሰማይ ፤ ቀድተው እየረጩ

   አምላከ አበዊነ ፤ እግዚአብሔር አዶናይ

   በእውነት የለህማ ! አንተ በዚህ ሰማይ

   እያሉ አልጮሁም ? በሰቆቃ እንባ ?

   የገባኸውስ ቃል ? ሆነ እንዴ ቁብ አልባ ?

   የሰጠኸን ኪዳን ፤ ምን በላው የት ገባ ?

   አንተም ደሞ እንደሰው ፤ ቃልህን ታጥፋለህ ?

   ወይንስ ወዴት ሔድክ ፤ ምን በላህ ምን ዋጠህ ?

   እንደምን ያለ እንቅልፍ ፤ ያዘና ወሰደህ ?

   ማን ቀርቦ ይቀስቅስህ ፤ ማን ጎትጉቶ ያንቃህ ?

   አቅም አልባ ሆነናል ፤ ጽድቅ ርቋል ከኛ

   አንተኑ ለማንቃት ፤ እንድትሆነን ዳኛ

አንቂልና እመ አምላክ ፤ ቀስቅሽው ልጅሽን

የእናትነት ቁጣሽ ፤ ቶሎ ያሥነሣልን

ንቃሕ እግዚኦን ደግመሽ ፤ ለምንት ትነውም

በእግዚኦ ኩነኔከ ፤ እንዲሰጠን ሰላም

ስለ ዐሥራትነት ፤ ስላለሽ ቃል ኪዳን

ብለሽ አሳስቢልን ፤ ከልጅሽ አማልጅን

ፍረድ በይው ታደግ ፤ ሕዝቤን ከመከራ

በቀልህን ተበቀል ፤ ደማቸውን አጥራ

በይልን ጩሂልን ፤ አታስተኝ አደራ

ይሄው እንላለን ፤ እግዚኦ ቀን አብራ

ማረን ይቅር በለን ፤ ፍቅርህን አድሰው

ምንድን ነው ያስጨከነህ ? አንልም ለምን ነው ?

በደል ኃጢአታችንን ፤ በደንብ ስለምናውቀው

እንዳስተማርክ ሁሉ ፤ በቃልህ እንዳልከው

የምወደውን ነው ፤ እኔ የምቀጣው

አባቱ የማይቀጣው ፤ ልጅ የሆነ ማነው ?

ያለ ቅጣት ብትኖር ፤ ዲቃላ ነህ እንጅ

ከአብራክ የተከፈልክ ፤ አይደለህም ልጅ

ቅጣቱ ለጊዜው ፤ ደስ አያሰኝህም

ዳሩ ግን በኋላ ፤ ፍሬውን የሰላም

ያፈራላቹሀል ፤ ጽድቅን የዘለዓለም

ብለኸናልና ፤ ይሁን  እንዳንተ ፈቃድ

ግን ደሞ በቃ በል ፤ ምሕረትህን አውርድ

አፈፍ አርገህ አንሣን ፤ እግዚኦ ማረን ወልድ

መከራ የምታውቀው ፤ አንተ የኛ ዘመድ

ከዚህስ በኋላ ፤ ሌላ ዓይነት መከራ

ደሞ ሌላ ፍዳ ፤ ሌላ ሕይዎት መራራ

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

የሚሸከም ጉልበት ፤ የሚችል ትክሻ

የሚያስተናግድ ቅስም ፤ ስቃይ መታገሻ

ጨርሶ የለንም ፤ ደቂቃም ማማሻ

በዚሁ ይብቃ በለን ፤ ይሁን መጨረሻ

ትንሣኤያችንን አውጅ ፤ ይምጣ የኛ ድርሻ፡፡

ኅዳር 2006 ዓ.ም.

amsalugkidan@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. alem woldel says

    January 15, 2014 12:53 am at 12:53 am

    Amen! !!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule