SMNE strongly condemns the recent illegal arrest and extradition of Mr. Andargachew Tsige from Yemen to Ethiopia. The Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) strongly condemns the recent illegal arrest and extradition of Mr. Andargachew Tsige from Yemen to Ethiopia. Mr. Andargachew was allegedly picked up at the Yemeni airport in Sana’a while in transit from Dubai to Eritrea. During a layover there, Yemeni security agents, tipped off and accompanied by Ethiopia’s own security agents, … [Read more...] about Solidarity Movement for a New Ethiopia
Left Column
የረመዳን ወግ
ወቅቱ ረመዳን ነው፡፡ እነሆ ለረመዳን የሚሆን (አንድ ወግ) ልጋብዛችሁ፡፡ ኸሊፋው ዑመር ኢብን አል-ኸጣብ ዘወትር እንደሚያደርገው የነዋሪዎቹን ሁኔታ ለመታዘብ በምሽት በመዲና ጎዳዎች ላይ ይንጎራደድ ነበር፡፡ ወደ አንድ ሰፈር ሲደርስ በስካር መንፈስ የሚለፈልፍ ሰው ድምጽ ሰማ፡፡ ወደ ቤቱ ተጠግቶ በመስኮት ቢያይ ሰውዬው የወይን ጠጅ እየጠጣ ዓለሙን ሲቀጭ አገኘው፡፡ ዑመር አላስቻለውም፡፡ በመስኮት ዘሎ ገባና ሰውዬውን “አንተ ምን መስራትህ ነው?… ከሰው ብትደበቅ ከአላህ መሰወር የምትችል መሰለህ?… ወይን ጠጅ ለምንድነው የምትጠጣው?” በማለት ተቆጣው፡፡ ሰውዬው እንግዳውን ትክ ብሎ ቢያይ ዑመር ነው፡፡ በጣም ደነገጠ፡፡ ስካሩ በአንድ ጊዜ ለቀቀው፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ተረጋጋና ዑመርን እንዲህ አለው፡፡ “ኸሊፋው ልክ ነዎት! ወይን ጠጅ መጠጣቴ ሐጢአት ነው፡፡ ይሁንና እኔ አንድ … [Read more...] about የረመዳን ወግ
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፯
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ በተለይ በዚህኛው በርካታዎች በመሳተፋችሁና በግጥም ምላሽ በመስጠት ዝግጅቱን ላሳመራችሁ ሁሉ በድጋሚ ምስጋናችን ይድረሳችሁ - ቀጥሉበት:: የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር ስድስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ መልስ በአፄ ሚኒሊክ - የአገዛዝ ዘመን ኤርትራ በሚገኝ - የስዊድን ሚሽን በኋላም ውጪ ሀገር - ብዙ የተማሩ በዕውቀታቸውም - ለሀገር የሰሩ በሹመት የቆዩ - ሆነው ነጋድራስ ታሪክ ያረሳቸው - እስከዛሬ ድረስ ገብረህይወት ባይከዳኝ - በሚል የጻፋችሁ ስህተት የለውም - ልክ ነው … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፯
የአፍታ እፍታዎች
ያስገረሙኝና ፈገግ ያሰኙኝ የማህበራዊ ሚዲያ ‹‹ጥቅሶች›› 1. ‹‹የድሃ ልጅ ስሙ ሀብታሙ ነው›› 2. ‹‹ሰውና ድፎ በትዕዛዝ እንደፋለን›› 3. ‹‹ቁንጅና ይኑርሽ እንጂ ፀባይ በዱላ ይመጣል›› 4. ‹‹የሴት ልጅ ግርዛትና ሚስድኮል ይቁም›› 5. ‹‹ኡፍ በማለት ትንፋሽ እንጂ ብሶት አይወጣም›› 6. ‹‹ለህይወትህ ዋጋ፣ ለልጆችህ ዳቦ ስጥ!›› ሰፈር ውስጥ የሰማኋቸው አዲሶቹ የሸገር ልጆች ቃላት • ‹‹በጤ›› - በጣም ለማለት • ‹‹በኔ›› - በእናትህ ለማለት • ‹‹እሱ እኮ እምባ ነው›› - የቅርብ ተቆርቋሪ ነው ለማለት • ‹‹ጠበዘዝነው›› - በላነው ለማለት • ‹‹ዘጭ ብያለሁ›› - ጠግቤያለሁ ለማለት • ‹‹ኤም ጢ ›› - መስሚያዬ ጥጥ ነው/ አልሰማህም ለማለት ታክሲ ላይ ያነበብኳቸው፡ 1. ‹‹ሰው ብቻ ነው የምንጭነው፤ በስህተት የገባ ካለ … [Read more...] about የአፍታ እፍታዎች
የአማራ ጉዳይ፤ አለ? ወይስ የለም?
ተናግሬ ነበር ማለት ዋጋ የሌለው የወሬ ማጌጫ ነው፤ እስቲ ፍቀዱልኝና ልጠቀምበት፤ ከወያኔ ዋና ምሁር፣ ከመለስ ጋር ለመጀመሪያና ለመጨረሻ ጊዜ ፊት-ለፊት በቴሌቪዥን በተገኛኘን ጊዜ ‹‹አማራ የሚባል ጎሣ የለም፡›› በማለቴ መለስ ዜናዊና ጭፍሮቹ ብቻ ሳይሆኑ ‹‹አማራ-ነን ባዮች›› በቃልም፣ በጽሑፍም፣ በቴሌፎንም ልክ-ልኬን እየነገሩኝ አንጀታቸውን ቅቤ አጠጥተው ነበር፤ ‹አንዲት ሴት ደውለው እብድና ዘበናይ የልቡን ይናገራል፤› ብለውኛል፤ አንድ ሰው የተናገረው ስሕተት ከሆነ ስሕተቱን በማስረጃ ማጋለጥና የራስን ሀሳብ በማስረጃ መትከል ነው፤ እውቀት የሚዳብረው፣ ሰዎች የሚማሩትና በእድገት ጎዳና የሚጓዙት በተጨባጭ ማስረጃ መነጋገር ሲችሉ ብቻ ነው፤ እኔ አማራ የለም፣ ዜሮ (0) ነው፤ አልሁ፤ አማራ አለ፣ አንድ አለ፤ (1) ነው ያለ ሰው የአንድን ዋጋ ማሳየት አለበት፤ አማራ የለም የሚል … [Read more...] about የአማራ ጉዳይ፤ አለ? ወይስ የለም?
ቅኝ ግዛት!
ምነው በቀደም ለት እንቢልታ ሲነፋ ከበሮ ሲደለቅ፣ ከዘመናት ግዞት ነፃ የወጣንበት፣ ብለህኝ አልነበር አፍሪካ ነፃ ናት? "'አፍሪካ . . . ሀገራችን አፍሪካ የኛ ናት አፍሪካ አፍሪካ. . ." ተብሎ ሲዘመር የጥቁሮች ነፃነት? ታዲያ ዛሬ ለሊት፣. . . የሰማሁት ዋይታ ያዳመጥኩት ጩህት፣ ሲያከብሩ እዳትለኝ የበአሉን ማግስት? ዋሽተህኛል እንዴ . . . ? ትርጉሙን አዛብተህ? . . . ሆኖ እንዳይሆን ብቻ፣ ነፃ መሆን ማለት ካልሆኑ አቻ ላቻ ፣ ለወሬ ማድመቂያ ዳንኪራ መርገጫ፣ ነፃነት ነፃነት እያሉ ማፋጫ፣ ድቤ መደለቂያ በባዶ መንጫጫ ? እኔን ነፃ ያርገኝ. . . በዚች መሬታችን በምንኖርባት፣ የጥቁር ደም አጥንት በግፍ ባለቀባት፣ ነፃነት አግኝቶ ደምቆ `ሚኖርባት ? የሰላምን አየር ተንፍሶ `ሚድርባት ነጭ ነው ወይ ጥቁር . . . … [Read more...] about ቅኝ ግዛት!
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፭” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አምስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ መልስ ለሀገር ለወገን - ውለታ የሰራ ስሙ ለዘለዓለም - ይኖራል ሲጠራ ነገር ግን ታሪኩን - ያረገውን በጎ አንባቢው አለበት - መረዳት ፈልጎ እኛ ለማስታወስ - ይሄንን አድርገን ለማቅረብ ችለናል - መላኩ በያንን እኚህ ስመ ጥሩ - ኢትዮጵያዊ ዶክቶር ሙሉ እድሜአቸውን - ደክመዋል ለሀገር። ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮
የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥፋቱ ምንድን ነው?
ቴዎድሮስ ካሣሁንን በአካል አላውቀውም፤ በዘፈንና በጭፈራ በእውነት ተደሳች መሆን ካቃተኝ ቆይቷል፤ ከ ኅዳር 1967 ጀምሮ ነው የቆረቆረኝ፤ ይህ ሰው እንደሰውና እንደ ኢትዮጲያዊ በየጊዜው የሚደርስበትን ወደ ግፍ የሚጠጋ በደል ስመለከት ያው የለመድነው ምቀኝነት ነው እያልሁ ሳልፈው ቆየሁ፤ ግን በደሉ አላቆም አለ፤ ማንም ሊደርስለት አለመቻሉ ይበልጥ ያሳዝናል፣ በእሱ ላይ ተከታታይ የደረሰበት በደል የሕግ ያለህ የሚያሰኝ ነው፤ በቴዎድሮስ ካሣሁን ላይ በተቀነባበረ መንገድ የሚፈፀመው ማሰቃየት ማንንም ሰው የሚያሳስብ ነው፤ ምክንያቱ ምንድን ነው? በግልጽ የታወቀ ነገር የለም። በቴዎድሮስ ላይ ከባድ ተንኮል ሲፈጸምበት የሰማሁት በመጀመሪያ ዛሬ በስደት ላይ ባለው « አዲስ ነገር» የሚባል ጋዜጣ ላይ ነበር፤ ጋዜጣው ቴዎድሮስ በሙያው ያገኘውን መልካም ስም በሰፊው ጥላሸት ቀብቶት ነበር፤ … [Read more...] about የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥፋቱ ምንድን ነው?
ሕገወጥ ደም ሻጮች የከሰሩበት
ከአንድ ዓመት በፊት አንድ ህመምተኛ ለሚደረግለት ህክምና ደም የሚያስፈልገው ከሆነ፣ ቤተሰብ አሊያም ወዳጅ ዘመድ ምትክ ደም ሰጥቶለትና የሚያስፈልገው የደም አይነት ከደም ባንክ ወጥቶለት ይታከም ነበር፡፡ ይህ አሠራር ግን በርካቶች የሚያስፈልጋቸውን ደም በቀላሉ እንዳያገኙ የሚያደርግ ሆኖ ቆይቷል፡፡ ቤተሰብ አሊያም የታካሚው የቅርብ ወዳጆችም ‹‹ደም ለግሱና ደማችሁ ተተክቶ ለታካሚው ሌላ ደም ይሰጠው›› የሚለውን ሐሳብ ሲሰሙ ሃሳቡን ይሸሻሉ፣ ከልገሳው ያፈገፍጋሉ እንዲሁም ይፈራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ደማቸው ተወስዶ እምብዛም ጥቅም ላይ መዋል የማይችል ግለሰቦች በደላሎች አማካይነት በሽያጭ ደም ይለግሳሉ፡፡ ደም ባንክ የእነዚህን ሰዎች ደም በምትክ ወስዶ ከባንኩ ለታካሚዎች ደም ቢሰጥም፣ በሕገወጥ መንገድ ተሸጦ ገቢ የተደረገው ደም ከሞላ ጎደል ይወገድ እንደነበር ባንኩ … [Read more...] about ሕገወጥ ደም ሻጮች የከሰሩበት
የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ማዕከላዊ ምክር ቤት
በትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ተቃዋሚነት ጎራ የተሰለፉ ኃይሎች በቅድሚያ ትግላቸውን በብሔራዊ ነፃነት ዙሪያ ያድርጉ! እኛ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ማዕከላዊ ምክር ቤት አባላት ከሰኔ ፲፬ - ፲፭ ቀን ፪ሺህ፮ ዓ.ም. (June 21 - 22, 2014) አራተኛ መደበኛ ስብሰባችንን በተሣካ ሁኔታ አካሂደናል። በሁለት ቀናት ጉባኤያችን የሥራ አስፈጻሚ እንዲሁም የቁጥጥርና ፍተሻ ኮሚቴዎች ያቀረቧቸውን የ፮(ስድስት) ወራት የድርጅቱን የሥራ እንቅስቃሴ ሪፖርቶችን አዳምጠን ጠቃሚ ውይይት አድርገናል። ድርጅቱ ያከናወናቸው መልካም ተግባሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ፣ በአፈፃፀም የታዩ ድክመቶች እንዲታረሙ በማስገንዘብ፣ ለድርጅቱ ዓላማ ዳር መድረስ የሚያግዙ የሚከተሉትን አቋሞች ወስደናል። ፩ኛ) የኢትዮጵያውያን ሉዓላዊነት፣ የአገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም መከበር እና የግዛታዊ አንድነት መጠበቅን … [Read more...] about የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ማዕከላዊ ምክር ቤት










