• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የረመዳን ወግ

July 7, 2014 11:10 pm by Editor 5 Comments

ወቅቱ ረመዳን ነው፡፡ እነሆ ለረመዳን የሚሆን (አንድ ወግ) ልጋብዛችሁ፡፡

ኸሊፋው ዑመር ኢብን አል-ኸጣብ ዘወትር እንደሚያደርገው የነዋሪዎቹን ሁኔታ ለመታዘብ በምሽት በመዲና ጎዳዎች ላይ ይንጎራደድ ነበር፡፡ ወደ አንድ ሰፈር ሲደርስ በስካር መንፈስ የሚለፈልፍ ሰው ድምጽ ሰማ፡፡ ወደ ቤቱ ተጠግቶ በመስኮት ቢያይ ሰውዬው የወይን ጠጅ እየጠጣ ዓለሙን ሲቀጭ አገኘው፡፡ ዑመር አላስቻለውም፡፡ በመስኮት ዘሎ ገባና ሰውዬውን “አንተ ምን መስራትህ ነው?… ከሰው ብትደበቅ ከአላህ መሰወር የምትችል መሰለህ?… ወይን ጠጅ ለምንድነው የምትጠጣው?” በማለት ተቆጣው፡፡

ሰውዬው እንግዳውን ትክ ብሎ ቢያይ ዑመር ነው፡፡ በጣም ደነገጠ፡፡ ስካሩ በአንድ ጊዜ ለቀቀው፡፡ ከትንሽ ቆይታ በኋላ ተረጋጋና ዑመርን እንዲህ አለው፡፡

“ኸሊፋው ልክ ነዎት! ወይን ጠጅ መጠጣቴ ሐጢአት ነው፡፡ ይሁንና እኔ አንድ ጥፋት ብቻ ነው የሰራሁት፡፡ እርስዎ ግን በዚህች ቅጽበት ሶስት ጥፋቶችን ሰርተዋል”፡፡

ዑመር ሰውዬውን እየተመለከተ “ጥፋቶቼ ምን ምን ናቸው?” አለው፡፡

ሰውዬውም እንዲህ ዘረዘረለት፡፡ “አንደኛ አላህ የሌሎችን ነውር አትከታተሉ ብሏል፡፡ እርስዎ ግን ይህንን ቃል ጥሰው እኔ በድብቅ የምሰራውን አይተዋል፡፡ ሁለተኛ አላህ ወደ ሌሎች ሰዎች ቤት ስትገቡ የባለቤቶቹን ፈቃድ ጠይቁ ብሏል፡፡ እርስዎ ግን ያለኔ ፈቃድ ነው ወደ ቤቴ የገቡት፡፡ ሶስተኛ አላህ ወደቤት ስትገቡ በበር ግቡ ነው ያለው፡፡ እርስዎ ግን በመስኮት ነው የገቡት”፡፡

ዑመር ጥፋቱን አንድ በአንድ አመነ፡፡ እናም “ለጥፋቴ ማበሻ ምን ይሻላል ትላለህ ታዲያ?” በማለት ጠየቀው፡፡

ሰውዬውም “ለሁለታችንም ጥፋቶች ማበሻ የሚሆን መድኒት አላህ ተናግሯል፡፡ ይኸውም የጓዶቻችሁን ነውር ደብቁ የሚለው ነው፡፡ እኔም እርስዎ የሰሩትን ጥፋት ለማንም አልናገርም፡፡ እርስዎም የኔን ስካር ለማንም አይንገሩብኝ፡፡ ከአሁን ወዲያ ላልጠጣ በአላህ ስም ቃሌን እሰጣለሁ” አላቸው፡፡

ዑመር በሰካራሙ ሰውዬ ብልሃት በጣም ተንደቆ ወደ ቤቱ ተመለሰ፡፡ ሰውዬው ሞቶ ይህንን ታሪክ ለተከታዮቹ ከማጫወቱ በፊት ለማንም ተናግሮት አያውቅም፡፡

የሰውን ነውር በመከታተል ሱስ የተለከፋችሁ ሰዎች ሆይ! እባካችሁ ተመከሩ፡፡ የሌላውን ነውር እከታተላሁ ብላችሁ ለራሳችሁ ኩንታል ሙሉ ሐጢአት እንዳትፈጽሙ፡፡

የሰውን ነውር ያያችሁ ሰዎች ሆይ! የጓዶቻችሁን ነውር አታውሩ! የባልንጀራችሁን ነውር ከደበቃችሁለት አላህ እናንተንም ከመጥፎው ሁሉ ይሰውራችኋል፡፡

—–

አፈንዲ ሙተቂ
ሰኔ 21/2005
ሀረር- ምስራቅ ኢትዮጵያ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. መስፍን says

    July 9, 2014 02:27 am at 2:27 am

    አፈንዲ ምን አይነት ፍልስፍና ለታስተምር እንደሆነ አልገባኝም ፣ ወሸታሙን ቀጣፊ ባለማለታችን ፣ባንዳውን አገሩን ለጥቅም የሸጠውን
    ባለማጋለጣችን ፣ ከጣሊያንና አሁን ደግሞ በእኛ እደሜ ያየነው ከሰማሌ ጋር በመሆን አገሩን የወጋውን ባለማሳወቃችን ህዝብ እንዲያቀው በለማደረጋችን ፣ይህው አሁን አገራችን የባንዶች መጫወቻ ሆናለች ።ማለት ያለብን በውሸት ሥም አለማጥፋት ፣የሰራን ማመስገን፣እህ ምንተባለ ብሎ ጠይቆ ያለተረጋገጠ ወሬ መንዛት፣መጥፎ መሆን መስበክ እንጂ እንዴት ነውር ይደበቅ በለህ ምሳሌ ታቀርባለህ? የህው እነታምራት
    ላይኔ የሰሩት ተረስቶ የጨበጨብላቸዋል ፣እነ ሰዬ? ! አንዳርጋቸውም የሄው በኤርትራ እርዳታ ነፃ ያወጣናል ብሎ አዳሜ ቴያትር የሰራል! ይህ ሁሉ ነውረኛን በመደበቃችን ነው ።

    Reply
    • shimon says

      July 11, 2014 10:17 am at 10:17 am

      “ረጅም እድሜ!

      Reply
  2. anwar says

    July 9, 2014 04:15 pm at 4:15 pm

    Mesfene I agree the lesson from the story is for people who are close to you or someone you know not to embarrass them in public basically don’t go around and be fault finder .but for the people you mentioned above of course we have to use all our means to fight them dictators and those who support them will never give you your rights .you have to take it. tnx by the way afendy good story I didn’t mean any harm

    Reply
  3. Amenen Gudaye says

    July 11, 2014 03:06 am at 3:06 am

    Mr Afendy if you have another please.

    Reply
  4. ቶቶ says

    August 10, 2014 02:48 pm at 2:48 pm

    እነደው ለመሆኑ ይሄን ታሪክ ከየት ይሆን ያገኙት ውድ ጸሃፊዬ? ነው ወይስ እስላም እንዲህ የሚራራ ነው ብለው ሊሉን ፈልገው ይሆን? ለመሆኑ በእስልምና መጠጥ፡ መጠጣት ከ8-14 ድረስ የሚሆን ግርፋት እንደሚያመጣ ሃዲቱ የተለያዩ ኡለማዎች እንደሚናገሩ ረስተውት ይሆን? ለማንኛውም እስላም ምን እንደሆነ የኢራቁ እስላማዊ እስቴት (ISIL) በተግባር እያሳየን ስለሆነ የእርሶ እስልምና እንደው የጥጥ ከረሜላውን አይነት መሰለ። ነው ወይንስ ከሰሞኑ በሊባኖስ እና በተለያዩ የመካከለኛው ምስራቅ ያሉ አረብ አገራት በሮመዳን ጾም ጊዜ ምግብ ሲበሉ እንዳይታዩ (እስላም ያልሆኑትን) እንደውም ( Saudi warns non-Muslims on Ramadan fasting /http://www.upi.com/Business_News/Security-Industry/2005/10/01/Saudi-warns-non-Muslims-on-Ramadan-fasting/UPI-67841128194966/?rel=78121373377801) እንደው ቀልዶትን ቢያቆሙ ብዬ ነው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule