ታጋይ፣ ከንቲባ፣ መከላከያ ሚ/ር፣ ምክትል ጠ/ሚ/ር፣ አቅም ገንቢ፣ አቅም ተገንቢ … ከዚህ ሁሉ አልፈው አሁን አቅማቸው ተገንብቶ የስፔስ (ሕዋ) ሳይንስ “አቅም ግንባታ” ለመሆን የበቁት ጡረተኛው ተፈራ ዋልዋ “የኢትዮጵያን የሕዋ (ስፔስ) ሳይንስ ሶሳይቲን” ገንብተው በሪፖርተር በኩል ብቅ ብለዋል፡፡ “አቅም ገንቢ ሚ/ር” በነበሩበት ወቅት “ሂድና ከአባዱላ ተማር የአንተ አቅም ግንባታ እንኳን አቅም ሊገነባ ያለውንም ሊያስቀጥል አልቻለም” ተብለው በአቶ መለስ የተገመገሙት አቶ ተፈራ አቅማቸው ተገንብቶ ለስፔስ መድረሱን “ባለራዕዩ መሪ” ሳያዩና ሪፖርተር ላይ ሳያነቡ መሰዋታቸው አቶ ተፈራን እጀ ሰባራ አድርጓቸዋል፡፡ የአላሙዲን “ወዳጅ” ሪፖርተር የአቶ ተፈራን አንደበት ገድቦት ነው እንጂ ተፈራ “ሼኸ፣ ዶ/ር፣ አቅም አስገንቢ … አላሙዲንን” ባነሱበት አንደበታቸው በግል ጄታቸው … [Read more...] about “ተፌ!”
Left Column
ሰማሁ! እናቴ ሰማሁ!
ጠይም ፊትሽ መጥቆሩን፣ ትንፋሽሽ፣ ጥሎሽ መሸሹን፣ የፊትሽ ወዝ ማጠፈፉን አካል ቁመናሽ መርገፉን ሰማሁ እናቴ ሰማሁ፣ አይቻል የለ ችያለሁ። በዝምታ ተውበሽ በሰው ሸክም ተሞሽረሽ በኡኡታ … በዋይታ… መሸኘትሽን ሰማሁት አይቻል የለ ቻል አ’ረኩት የሆንሽውን ሳልጠይቅሽ ሳትነግሪኝ ጎንሽ ሆኜ ሳላዋይሽ ሳታዋይኝ ሞተሽ ቀብርሽ ሳልቆምልሽ ከቀረሁኝ እናቴ ሆይ! ፍረጂልኝ ፍረጂብኝ ምን ላድረገው? ምን ታረጊኝ? ስደት ዶጋ አመድ ያድርግህ! እንደ እናቴ ትንፋሽ ይንሳህ! ምንስ ብትነፍግ ብታሳጣ ካገር ወጪ ብታውጣ የናቴን! የናቴን እንኳን የመጨረሽ ሽኝቷን እንዴት! ከዓይኔ ታርቅ እንዴት! ከእግሬ ትነጥቅ አዎን! ግድየለም! ሞት መቼም ለኛ አዲስ አይደለም ግን! እናትን ያህል ነገር እንዴት ታሳጣኝ ቀብር? ምነው እናቴ አንችስ! ናፍቆትሽን … [Read more...] about ሰማሁ! እናቴ ሰማሁ!
ከምርጫ ’97 “የተማረው” ኢህአዴግና የሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫን በተመለከተ ከሰሞኑ ለመነሻ ያህል የቀረበ ነው በሚል ረቂቅ የጊዜ ሰሌዳ ለፓርቲዎቹ ለማስተዋወቅ ሞክሮ ነበር፡፡ ይህን የጊዜ ሰሌዳና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችን በተመለከተ ከፓርቲዎቹ ጋር ለመምከር በሶስት ዋና ዋና ከተሞች (አዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀዋሳ) ፓርቲዎቹን ከፋፍሎ ለውይይት ጠርቶ የነበረ ቢሆንም ጥቂት የማይባሉ ፓርቲዎች መድረኩን ጥለው መውጣታቸው የሚታወስ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ የምርጫ ጊዜውን በተመለከተ ከመነጋገራችን በፊት በርካታ ልንነጋገርባቸውና ሊስተካከሉ የሚገቡና በደብዳቤ ለምርጫ ቦርድ የገለጽናቸው ጉዳዮች ስላለሉ ለእነዚያ ጉዳዮች ቅድሚያ መሰጠት ይገባዋል ከሚል መነሻ ነበር፡፡ ምንም እንኳ ቦርዱ የዝሆን ጆሮ ይስጠኝ እንዳለ የቀጠለ ቢሆንም፡፡ ያም ሆነ ይህ ምርጫ ቦርድ ለውይይት ያቀረበው ረቂቅ የምርጫ ጊዜ … [Read more...] about ከምርጫ ’97 “የተማረው” ኢህአዴግና የሚጠበቀው ሀገራዊ ምርጫ
እርሳስና ላጲስ
እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡ እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ ውሸት … [Read more...] about እርሳስና ላጲስ
የጅዳው ት/ቤታችን እንደ አረቡ አብዮት ከድጡ ወደ ማጡ!
የጅዳ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህርት ቤት በተወሳሰበ የአሰራር፣ አመራር ሂደት ውስጥ በማለፍም ቢሆን የመማር ማስተማር ሒደቱን ከጀመረ ሁለት ወር ደፍኗል። በሁለት ወራት ልጆቻችን ተምረው ተመለሱ ብሎ ለጠየቀ ምላሹ ቆሽት ያሳርራል። በእስካሁኑ የትምህርት ቅበላ ባለው ከስድስት ያላነሰ ክፍለ ጊዜ የሚማሩት ከሁለትና ሶስት ክፍለ ጊዜ ሲሆን አልፎ አልፎ አራት ክፍለ ጊዜ ብቻ ተምረው ይመለሳሉ። ይህን እውነታ ልጆቹን እንደማዋያ ጥሎ ዘወር የሚለው ባይተዋር ወላጅ ከልጆቹ ይሰማዋል። የልጆቹን ደብተር አገላብጦ የሚመለከት የእኔ ቢጤ ብስጩ አባት ደግሞ ከልጆቹ ከመስማት አልፎ በማስረጃ ደብተሩን ሲያገላብጥ የሚታዘበው እውነታ ነው። በአንዳንድ ክፍሎች ዘመናዊውን ትምህርት ትምህርት የሚያሰኙት የእንግሊዝኛና የሒሳብን ጨምሮ ከፍ ሲል የኬሚስትሪ፣ የፊዚክስ፣ የባዮሎጂና የኮምፒውተር ትምህርቶች … [Read more...] about የጅዳው ት/ቤታችን እንደ አረቡ አብዮት ከድጡ ወደ ማጡ!
ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ
ምርጫ ቦርድ በጊዜ ሰሌዳ ላይ ለመወያየት በጊዮን ሆቴል የጠራውን ስብሰባ “ጥያቄዎቻችን የሚመልስ አይደለም” በሚል የሰማያዊ ፓርቲ ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ በተጨማሪም የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (መኢዴፓ) እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ተወካዮች ስብሰባውን ረግጠው ወጥተዋል፡፡ ፓርቲዎቹ በትናንትናው ዕለት ከምርጫ 2007 ዓ.ም በፊት ውይይት ሊደረግባቸውና ሊፈቱ ይገባል ያሏቸውን ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ ያስገቡ ቢሆንም በዛሬው ስብሰባ በደብዳቤ ካሳወቋቸው ችግሮች ይልቅ የጊዜ ሰሌዳ ቅድሚያ የተሰጠው በመሆኑ የምርጫ ምህዳሩን ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም ብለው ስብሰባውን ረግጠው መውጣታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ስብሰባውን ረግጠው ከወጡት መካከል የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ (ኢብአፓ) ዋና … [Read more...] about ሰማያዊ፣ መኢዴፓና ኢብአፓ የምርጫ ቦርድን ስብሰባ ረግጠው ወጡ
የዝናብ ሀሳቦች
ዝናብ መች ይከፋል ቢዘንብ ምን አለ መብረቅ ባያስከትል እያጉረመረመ መዝነቡንስ ይዝነብ ማበስበሱን ቢተው ቀን የጣለ አይደል ሌት የሚያዳልጠው። ★★★ ሌቱን ሲዘንብ አድሮ ቀኑን ብራ ዋለ ለምን ይወቅሱታል ሰው መስራት ከቻለ ሲጥልም አይጣል ነው ዶፉ ከወረደ ማን አለብኝ ያለው ገደሉም ተናደ። ★★★ ዝናቡ ከመጣ "አህያ ማይችለው" በጊዜ 'ንጠለል ከወረደ አንዴ ነው እዲህ ከሚፎክር መጣሁ ቀረሁ እያለ ወርዶ ቢያሳርፈን እሱም እፎይ ባለ። ተጻፈ 8/5/2014 … [Read more...] about የዝናብ ሀሳቦች
Obang addresses Civil Society Policy Forum at the IMF and World Bank meeting
Address by Obang Metho, Executive Director of the SMNE, to the Civil Society Policy Forum at 2014 Annual Meetings of the International Monetary Fund (IMF) and the World Bank Group (WBG), Washington, DC Thank you for inviting me to share in this panel discussion on “The Role of World Bank Indicators in Agricultural Development.” Today’s discussion is very relevant in that the World Bank is investing billions of dollars into agribusiness. Various new tools have been designed to measure and … [Read more...] about Obang addresses Civil Society Policy Forum at the IMF and World Bank meeting
“መጪው ምርጫ ይቅርብን”
ጥላ መጽሔት 11ኛ ዕትም “መጪው ምርጫ ይቅርብን” በሚል ርዕስ እና ከዚህ በታች ያሉትን ጦማሮችና ሌሎችን አካትታ ወጥታለች፡፡ ከቢን ላደን ግድያ በስተጀርባ ኢትዮጵያ በጋዜጠኞች በስደትም አንደኛ? የወያኔ ፍትሃዊ ምርጫ! መሬት ቆርሶ ... የአገር ስሜት ሳይኖረው ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ የመጽሔቷን የሽፋን ገጽ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ … [Read more...] about “መጪው ምርጫ ይቅርብን”
መጠነኛ ማስተካከያ ለሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ከአዘጋጆቹ፡ ከጥቂት ቀናት በፊት ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው “ማተብ እናስወልቃለን? ሴኩላሪዝምስ ምንድን ነው?” በሚል ርዕስ ለጻፉት ሥርዓት ጠብቆ ምላሽ የሚሰጡ ተቀብለን እናትማለን ባልነው መሠረት ኢብኑ ሙነወር “መጠነኛ ማስተካከያ ለሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው” በሚል ርዕስ ጨዋነት በተሞላበት አጻጻፍ የላኩልንን ምላሽ ከዚህ በታች አትመናል፤ ምስጋናችንንም እናቀርብላቸዋለን፡፡ ሌላ አዲስ አጀንዳ እስካልመጣ ድረስ በዚሁ ይህንን ውይይት የቋጨን በመሆኑ ምላሽ ጽሁፎችን የማንቀበል መሆናችንን እንገልጻለን፡፡ ጉዳዩን መቀጠል የሚፈልጉ ከጸሐፊዎቹ ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋውና ኢብኑ ሙነወር ጋር በኢሜይል ወይም በፌስቡክ ወይም በሌላ በሚያመቻቸው መንገድ በመገናኘት ሃሳባቸውን መላክ ይችላሉ፡፡ በቅርቡ በሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ መንግስት ለአመራሮቹ በሰጠው ስልጠና ላይ … [Read more...] about መጠነኛ ማስተካከያ ለሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው










