• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እርሳስና ላጲስ

October 21, 2014 05:51 am by Editor 3 Comments

እርሳስ በጓደኛው፤ በብዕር እስክሪፕቶ

ባለው ገደብ የለሽ፤ ነጻነቱ ቀንቶ

እንዳሻው ቢናገር፤ የልቡን አውጥቶ

እንዲህ አልክ ብሎ፤ ያለውን አጥፍቶ

የሚያስወግድበት፤ በላጲስ አንሥቶ

ስለማይከላ፤ ሲናገር አፍ ከፍቶ ፡፡

እሱ ግን ዘለዓለም፤ በላጲሱ ጠፍቶ

መኖሩ አስመርሮት፤ በእጅጉ ተከፍቶ

እኔስ ለምን እንዴት? ማለት ጀመረና

ጠየቀ አፋጠጠ፤ ተሰማው ፍነና

ነጻነቱን ሊያውጅ፤ ተነሣ ይሄ ጀግና

ከእንግዲህ በኋላ፤ አለ ቆፍጠን ብሎ

የነበረውን ፍርሐት፤ ከልቡላይ ነቅሎ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ አለ አንሥቶ ክንዱን

ባናቴ ያለው ላጲስ፤ ገደብ የለሽ ሥልጣን

አብቅቷል ብያለሁ፤ ይሰማ አዋጀ

የሚጸና ይሆናል፤ በትውልድ ልጅ ልጀ

ከዚህች ቀን በኋላ፤ ማንም ያላወቀ

በእውቀት ያለበቃ፤ ከንቱ ያልጠነቀቀ

ዐሥሬ እየጻፈ፤ እየለቀለቀ

ዐሥሬ የሚያጠፋ፤ መሀይም የወደቀ

ውሸት የሚደጋግም፤ በላጲስ እየፋቀ

በእጁ አይይዘኝም፤ አለቀ ደቀቀ

ከቶም አይገዛኝም፤ ብሎ አስታወቀ ፡፡

ከእንግዲህ ወዲህ፤ መብቴን ተገፍፌ

አልኖርም ብያለሁ፤ እያለ መዳፌ

እኔም እንደ ብዕር፤ ያሻኝን ብል ጽፌ

ወይም ተናግሬ፤ በዓለም ሕግ ታቅፌ

ያ የተናገርኩት፤ የጻፍኩት ቃል ርኡስ

ይቀመጣል እንጅ፤ እዛው ሳይደመሰስ

ማንም አይፍቀውም፤ እያነሣ ላጲስ

ይሄው አውጃለሁ፤ ይሁን እንደ ቃል ቅዱስ፡፡

ከእንግዲህ በኋላ፤ በዚህ አዋጅ ሥሩ

ስሕተት እንኳን ቢሆን፤ የጻፍኩት ቃል ዘሩ

ይቀመጣል እንጂ፤ ልክ እንደ ብዕሩ

ሠረዝ ተደርጎበት፤ ሳይጠፋ ነገሩ

ለታሪክ ለትምህርት፤ ጠቀምጦ በክብሩ

ከእንግዲህ ወዲህ፤ የማንም ምን ውላጅ

ከቶም አይፍቀኝም፤ እኔን በላጲስ ፈንጅ፡፡

መስከረም 2007ዓ.ም.

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    October 21, 2014 10:05 am at 10:05 am

    **************************
    አርሳስ…
    እርሳስ በእስክሪብቶ ሁልግዜ ተዛብቶ
    እኔ እየጠፋሁኝ አንተ አትጠፋ ከቶ?
    እስክሪብቶ…
    አንተማ ሞኝ ነህ አጥፊህን በራስህ ተሸክመህ
    ለእግር ሸንካይ በመቅረጫ ተሸራርፈህ
    እኔማ ቀለሜ ላይፈስ ታፍኜ ከላይም ከታችም
    የሚፃፍ ሞልቶ አንድም ዘጋቢና ፀሐፊ አልተገኘም።
    ላጲስ…
    እኔ የሰማሁት የዓሳ ሽታ ከራስ ነው
    የእርሳስ ላይ ጭንቅላትን አጥፊ ማነው ያለው
    እርሳስማ አጠፋኝ ሲል ስሜን አጠፋው
    እስኪሪብቶ ተሳለቀብኝ እንደማላጠፋው
    የተፃፈን ቀበኛ የሚፅፍን የሚያጠፋው ማነው!?
    በለው!

    Reply
  2. Amsalu Gebrekidan says

    October 23, 2014 10:03 pm at 10:03 pm

    ይሄንን ግጥም ብዙ ሰው እንዳልገባው ሳይ አዘንኩ፡፡ ለነገሩ እንኳን ቅኔያዊው ይቅርና የትውልዱ በቋንቋው ራሱን ሐሳቡን የመግለጽ ችሎታ እጅግ ከመድከሙ የተነሣ የቋንቋው ጥራት አሽቆልቁሎ ተራ ንግግር እንኳን በአግባቡ መግለጽ የምንቸገር ትውልድ እየሆንን ከመሆኑ የተነሣ ቅኔ ለምን አልገባህም ብሎ ማለት ምጸት ነው የሚሆነው፡፡

    ይሄውላቹህ እርሳሱ የሚወክለው ሐሳቡን በነጻነት የመግለጽ መብቶቹን አጥቶ ተረግጦ የሚኖረውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይወክላል፡፡ ላጲሱ ደግኖ ገደብ የለሽ ሥልጣን ይዘው የሚረግጡትን ግፈኛ ገዥዎቹን ይወክላል፡፡ እስክሪፕቶና ብዕሩ ደግሞ በነጻነት ሐሳቡን የመግለጽ መብት ያለውን የምዕራቡን ዓለም ሕዝብ ይወክላል፡፡ አሁንስ?

    Reply
    • ሳባ says

      November 7, 2014 01:32 pm at 1:32 pm

      አመሰግናለሁ አምሳለው ግን አኔ ገና ሳነበው ቅኔ መሆኑ ገብቶኝ ነበር. ልንገርህ አኔ ethiopia ውስጥ አደለም ያደኩት ግን የላፕሱና የርሳሱ ቅኔ ስለገባኝና አንተ ደግሞ sure ስላደርክልኝ አመሰግናለሁ.

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule