ድሬ ቲዩብ በመባል የሚታወቀው በአማርኛ "ትልቁ" የድህረ ገጽ እና ድህረ ምስል አውታር፣ ሰሞኑን አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፣ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ሁለት ጥያቄ ጠይቆ ነበር። 1ኛው የኢትዮጵያ መሪ (ፕሬዝዳንት) ማን ናቸው? የሚል ሲሆን 2ኛው ደሞ የአሁኑ የአዲስ አበባ ከንቲባ ስማቸው ማን ይባላል? የሚሉ ናቸው ። ሕዝቡም እንደ አቅሙ ትክክለኛውን መልስ ለማግኘት ጥሯል። ሙላቱ አስታጥቄ፣ እንዳለ አድምቄ፣ አሰፉ ደባልቄ፣ ዶቅዶቄ፣ ቦሎቄ፣ አረቄ እና ወዘተ። የጎዳና ተዳዳሪ ልጆች መለስ ነው አዲስ አበባን የቆረቆራት (ወይም ከንቲባዋ መለስ ነው) ሲሉ፣ የጥበቃ ሰራተኞች "ማን ነበር? ይገርማል!" በማለት አለማወቃቸውን አሳውቀዋል። ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ እና ኩማ ደመቅሳም ያሉም አሉ። ይህ እንግዲህ የአዲስ አበባ ከተማ ነው። የኢትዮጵያ ዋና ከተማ። መረጃ … [Read more...] about ሁለት ጥያቄ ብቻ አለን?
Left Column
“የኤርትራ ምሽት” ለስደተኞች ደራስያን
ካንድ አሰርት ዓመታት በላይ አባል ሁኜ የቆየሁበት ኖርዌጂያን ፔን (Norsk PEN/N0rwegian PEN) የሚያከናውናቸው የተለያዩ ተግባራት አሉት፡፡ ከነዚህም አበይት ትግባራቱ መካከል በያገራቱ ያሉ እህት ማህበራትን መታደግና ለስደተኛ ደራስያን የከተሞች የጥገኝነት (By Forfatter) መብትን ማሰጠት ነው፡፡ ሥራቸውም እንዲታተምና ለሕዝብ እንዲደርስ ጥረት ያደርጋል፡፡ በእስር ላይ የሚገኙ የሌሎች አገር ደራስያንንና ጋዜጠኞችን ማሰቢያ ምሽቶችን በየጊዜው ያዘጋጃል፡፡ ከዚህ ቀደም የማሰቢያ ምሽት ከተዘጋጁላቸው ጸሐፍት መካከል እውቁ ጸሐፊ ኢትዮጵያዊው እስክንድር ነጋና ስዊድናዊ/ኤርትራዊው ዳዊት ይስሃቅ ይገኙባቸዋል፡፡ እናም ኖርዌጂያን ፔን ባለፈው ሐሙስ ጥቅምት 25 ቀን "የኤርትራ ምሽት" የተሰኘ የምሽት ፕሮግራም አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ይህ ምሽት ኤርትራ ወስጥ ያለውን የሰብአዊ መብት … [Read more...] about “የኤርትራ ምሽት” ለስደተኞች ደራስያን
ንቧ ድፍት ኣለች
እንደው ባለፈው አመት ህወሓት 40ዋን ስታወጣ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ እንዳደረገች የምታስታውሱት ነው። የዲያስፖራ ቀን በትግራይ ሲከበር 200 ሚሊዮን ብር ወጪ፣ የአርቲስቶች ጉብኝት፣ የከተሞች ቀለሞች መቀባት፣ የዜሮ አምፑል መብራቶች (ህዝቡ ዜሮ አምፑል መንግስት ያለው)፣ የካኪ ልብሶች፣ ድግሶችና ግዢዎች ወጪ ከ2 ቢሊዮን እንዳወጣች በወቅቱ የተገለፀ ነው። በወቅቱ የ38 ሚሊዮን ኩንታል ከክረምት፣ 75 ሚሊዮን ኩንታል ደግሞ ከመስኖ እርሻ እህል ተመረተ ብለው የተተረተሩበት ዓመት ነበር። እያንዳንዷ ካድሬ፣ ልማታዊ ጋዜጠኛ፣ የሊግ፣ የማህበራትና የአንድ ለ አምስት ኔትወርክ መሪ ሁላ አካኪ ዘራፍ እያለች የመለስ ራዕይ ተሳካ እያለች ስታሽካካ ነበር። እውነት እንኳን ድሃ ድህነት የሚል ቃልም ድራሹ የጠፋ አስመስለውት ነበር። ዳሩ ግን ያሁሉ ፕሮፖጋንዳ 4 ወር ሳይቆይ ለአለም ማህበረሰብ … [Read more...] about ንቧ ድፍት ኣለች
ሻምበል ሞገስ ወልደሚካዔል
በግልጽ መታወቅ ያለበት የግለሰቡ ማንነትና ያደረገው አስተዋፅዖ ዓመቱ ፲፱፻፷፫ ነበር። በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ፤ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ነበርኩ። በዚያ ጊዜ ከአራት ኪሎ ወደ ፒያሳ በሚወስደው መንገድ፤ በስተግራ ከነበረው የፋሲካ ሆቴል፤ ከሆቴሉ በስተሰሜን ገባ ብሎ በረባዳው በኩል፤ ተከራይቶ የሚኖር፤ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ነበር። ይህ መምህር አቶ ክብረት ተስፋሁን ይባላል። የሻምበል ሞገስ ወልደሚካዔል የናቱ ታናሽ ወንድም ነው። አራት ሆነን ምሳ ስንበላ፤ ሞገስና እኔ በዩኒቨርሲቲው የምናደርገው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃመወያየት ጀመርን። ለኮንግሬስ ( የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር - አዩተማ University Students Union of Addis Abeba – USUAA - ኡዙዋ) የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን … [Read more...] about ሻምበል ሞገስ ወልደሚካዔል
ደሳለኝ ደበረኝ
የኢቢሲ “ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ” “መንግሥት ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። እነዚህ ከባባድ ኢንቨስተሮች ምርቱን በሞኖፖል ከያዙት፣ ይኸ ነገር በሃገራችን “እየተሰፋፉ የመጡትን መካከለኛ ኢንቨስተሮች” ሊያፈናቅላቸው ይችላል ተብሎ ይሰጋል። ይህንን እንዴት ይመለከቱታል። ¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ትክክል ነው ልማታዊው መንግሥታችን ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። ይህን ነገር እኮ እኛ የፈለሰፍነው አይደለም። ከሌሎች ሃገሮች ተመክሮ (ኮርጀን - ባግባቡ ወይም ባላግባቡ) ወስደን፣ ለምሳሌ ከደቡብ ኮርያ፣ ቬትናምና ቻይና አይተን ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምንሰራበት ምክንያት ኢንቨስተሮች እንዳይቸገሩ ነው። ለምሳሌ መብራት እንዳይቋረጥባቸው። እነሱ ለምን ይቸገሩ? እ? ጨርቁን ቀለም እየቀቡት እያለ መብራት ቢቋረጥ እኮ … [Read more...] about ደሳለኝ ደበረኝ
Me, my country and corruption
Have you seen a movie titled ”me, myself and Irine” or ”me and Marley”? Both are my favorite movies. When I decided to write article about corruption what it does to me and my country. The title concept of these movies clicked to my mind. I borrowed the concept, convinced it will explain the theme of my article. In this article I will try to discuss the harm corruption can cause to an individual that is me and my country. I will also try to shade some light on the issue from the global … [Read more...] about Me, my country and corruption
Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause (GAJEC)
DECLARATION BY THE INTERNATIONAL CONFERENCE ON JUSTICE FOR THE FASCIST ITALIAN WAR CRIMES COMMITTED AGAINST ETHIOPIA IN 1936-41 PREAMBLE 1.1 Taking into consideration the presentations and deliberations at the international conference which was held at the hall of the College of Medicine at Howard University on September 26, 2015; 1.2 Expressing the conference’s warmest appreciation to Howard University for having provided its hall free of charge and for its excellent hospitality as … [Read more...] about Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause (GAJEC)
ሸንጎ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚያገለግለውን አመራር መረጠ
በኦታዋ ካናዳ በተካሄደው ጉባኤ በአውሮፓውያን አቆጣጠር በ2012 የተመሠረተውና የኢትዮጵያ የአንድነት ኃይሎች ትልቁ ስብስብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣ (ሸንጎ) በዛሬው ዕለት ባካሄደው የምክር ቤት ስብሰባ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ድርጅቱን የሚመሩ የሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ አባላትን መርጧል። በዚህም መሰረት ከስራ አስኪያጅ ኮሚቴው አባላት ውስጥ ዶክተር ታዬ ዘገዬን፣ ሊቀመንበር ወይዘሮ ጽጌረዳ ሙሉጌታን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ግደይ ዘርአጽዮንን ዋና ጸሀፊ እና አቶ መሐመድ ጀሚልን ምክትል ዋና ጸሀፊ አድርጎ መርጧል፡፡ የተቀሩት የኮሚቴው አባላት ደግሞ የተለያዩ የተግባር ኮሚቴወችን በኃላፊነት ይመራሉ። ሸንጎው በቅርቡ አጠቃላይ ጉባዔ በማካሄድ ኢትዮጵያችንና ሕዝቧ የሚገኙበትን ሁኔታ በጥልቅ ከመረመረ በኋላ ሀገራችን ከምትገኝበት አስከፊና አደገኛ የግፍ ሥርዓት ተላቃ … [Read more...] about ሸንጎ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት የሚያገለግለውን አመራር መረጠ
በንቁጣጣሽ! ምን ቀጠፈሽ?
ዘመን ፊትሽ ተከምሮ እየታዬ ስራሽ አምሮ እንቁጣጣሽ አንድ ብለሽ አርባ ድረስ እድሜ ቆጥረሽ እንደ ቤቶች የሳቅ ተውኔት እንደ ጨቤ ስካር ህይወት ሞት ራሱን ያሾፍሽበት ለምንድነው? በይ ንገሪኝ እባክሽን አደብቂኝ ባንቺው ቀዬ የተወለድኩ ፊደል በጄ እዛው የያዝኩ መስፍን ሜዳ የተራገጥኩ በጨበጣ ብይ ያስቆጠርኩ ቲቸር ታዬ ያስተማሩኝ ገብሬ ኩርኩም ያቀመሰኝ የሲሚንቶ ጭስ ያወዛኝ ቅዱስ ያሬድ ተሳልሜ ከሽፋ ቤት ተሰይሜ ያቶ ማሞን ኪኒን ቅሜ እዛው ኖሬ እዛው ያደኩ የቃጠሎው ቀን የተረፍኩ እኔ እማውቅሽ የማታውቂኝ የሰፈርሽ አንድ ስው ነኝ ይሄን ሁሉ ዘርዝሬልሽ ጥያቄዬን ስጠይቅሽ ዝም አትይም መቼም ከፍተሽ ፊት ለፊትሽ ተስፋሽ ሞልቶ እየታየ ዝናሽ ጎልቶ እንደጸደይ ባገር ፈክተሽ በህዝብ ፊት ደምቀሽ ታይተሽ በአዲስ አመት በንቁጣጣሽ በ´ለቱ ለት … [Read more...] about በንቁጣጣሽ! ምን ቀጠፈሽ?
ቅጥ ላጣው ሙስና “ተጠያቂ ነኝ” – ህወሃት
ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር - ህወሃት በተለይ በአዲስ አበባ ቅጥ ያጣውን ሙስናና ዘረፋ በተመለከተ በጠራው ስብሰባ አስቀድሞ በመቀሌው "ተጠያቂ ነኝ" በማለት እንዳመነው አሁን ደግሞ ነዋሪው ችግሩን ራሱ እንዳመጣው ራሱ ይፍታው ማለቱ ተነግሮዋል:: የሪፖርተር ዘገባ እነሆ:- * ሙስና በአዲስ አበባ በኔትወርክ ተይዞዋል ሙስና፣ ኪራይ ሰብሳቢነትና የመልካም አስተዳደር እጦት ከወረዳ እስከ ከተማ አስተዳደሩ ድረስ በኔትወርክ የተያያዙ በመሆናቸው ሊፈታቸውም ሆነ ሊያስቆማቸው የሚችለው ድርጅቱ ኢሕአዴግ ብቻ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ለግማሽ ቀን አዘጋጅቶት በነበረው የውይይት መድረክ ላይ ከተለያዩ የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ የሁሉም ክፍላተ ከተሞች፣ … [Read more...] about ቅጥ ላጣው ሙስና “ተጠያቂ ነኝ” – ህወሃት










