• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ንቧ ድፍት ኣለች

November 5, 2015 11:36 am by Editor 1 Comment

እንደው ባለፈው አመት ህወሓት 40ዋን ስታወጣ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ እንዳደረገች የምታስታውሱት ነው።

የዲያስፖራ ቀን በትግራይ ሲከበር 200 ሚሊዮን ብር ወጪ፣ የአርቲስቶች ጉብኝት፣ የከተሞች ቀለሞች መቀባት፣ የዜሮ አምፑል መብራቶች (ህዝቡ ዜሮ አምፑል መንግስት ያለው)፣ የካኪ ልብሶች፣ ድግሶችና ግዢዎች ወጪ ከ2 ቢሊዮን እንዳወጣች በወቅቱ የተገለፀ ነው።

በወቅቱ የ38 ሚሊዮን ኩንታል ከክረምት፣ 75 ሚሊዮን ኩንታል ደግሞ ከመስኖ እርሻ እህል ተመረተ ብለው የተተረተሩበት ዓመት ነበር።

እያንዳንዷ ካድሬ፣ ልማታዊ ጋዜጠኛ፣ የሊግ፣ የማህበራትና የአንድ ለ አምስት ኔትወርክ መሪ ሁላ አካኪ ዘራፍ እያለች የመለስ ራዕይ ተሳካ እያለች ስታሽካካ ነበር።

እውነት እንኳን ድሃ ድህነት የሚል ቃልም ድራሹ የጠፋ አስመስለውት ነበር። ዳሩ ግን ያሁሉ ፕሮፖጋንዳ 4 ወር ሳይቆይ ለአለም ማህበረሰብ በድርቅ ለተጠቃ ህዝብ እርዳታ በመለመን አስደነገጡን።

የየካቲት 11 በዓልና ያጋጠመው ድርቅ ኢህአዴግ ልክ እንደ ሃይለስላሴና ደርግ ስርዓቶች የህዝብ ስቃይ፣ ርሃብ፣ ሞት የማይሰማው ግኡዝ መንግስት መሆኑ ያጋለጡበት አጋጣሚ ፈጥሮ አልፏል።

1) የጃንሆይ ልደትና የ67 ድርቅ

2) የደርግ ኢሠፖአኮ ልደትና የ77 ድርቅ

3) ህወሓት ልደት የየካቲት 11ና ድርቅ 2007/8 በተመሳሳይ ምድብ ያጋልጣቸዋል።

ህወሓት ከ30 ዓመት በፊት ያኔ የሽምቅ ተዋጊ በነበረችበት ግዜ ራስዋ ወደ ማሌሊት ስታሸጋግር ለትግራይ ህዝብ እንድታከፋፍል የተሰጣት እርዳታ 95% ለመመስረቻ በአል ድግስና ለጦር መሳርያ መግዣ እንዳዋለችው BBC እንደዘገበው የአሁኑ የእርዳታ እህል “ለአባይ ግድብ፣ መጋዘን ሞላ” እየተባለ እየተሸጠ እንዳለ እየተነገረ ነው። ህወሓት በበረኻም በቤተ መንግስትም ሁና የህዝብ እርዳታ የመቀማት ልማዷ እንዳልተወች ነው።

ህወሓት ለአርባዋ ብዙ ሽርጉድ ብላለች። ከዝግጅቱ ትልቅ ንብ ቀርፀው ተሽከርካሪ ነገር ሰርተው በቲዮታ መኪና እየጎተቱ በማዞር የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ አንዱ ነበር።

ታድያ ንቧ የጉዞዋን ግማሽ ከሄደች በኋላ ንግድ ባንክ አለፍ ብላ ሑመራ ሆቴል አጠገብ እኔ ወደ ነበርኩበት ስትደርስ ንቧ በአፍ ጢሟ ድፍት አለች።

ንቧ ፊትለፊቴ ድፍት ስትል እኔን የሚል አንድም ሰው አልነበረም። አንዷ ተለቅ ያሉ ሴትዮ “እንዴ ምን ነክቷት ነው አሁን በአፍጢሟ የተደፋችው …?” ይላሉ። ሌላኛዋ ደግሞ “አታዮ ክንደየን ዳ ኖአኻ ትኾኖ” (እናንተዬ እንዴት አባትዋ ታክላለች) ሲሉ ነበር።

ጨዋታው ሲያዳምጥ የነበረው ወጣት “እቺስ አውራዋ ሙሰኛዋ ናት። እንዲህ የወፈረችው ሙስና በልታ በልታ መሆን አለባት” ሲል ቀለደባት።

ንቧ ፊትለፊቴ መጥታ ድፍት አለችና ተጎትታ ወደጎን ተወሰደች።be e

በመኪና የመጣችው ንቢቱ ሰው ድሃ ይሁን ሃብታም ሲሞት በሶስት ሜትር አቡጀዲድ እንደሚገነዝ ጋሪ ላይ ወጥታ ተገንዛ ተጭና ሄደች። እኔም ወደ ጋሪዋ ሲጭንዋት አገዝኳቸው። ምክንያቱም በባህላችን ሬሳ ሲሸኝ የማታውቀው ቢሆን’ኳ ተሸክመህ መሸኘት ግዴታ ነው።

ቦታው ላይ የአውራምባ ታይምስ አዘጋጅ ዳዊት ከበደ ነበረና ድፍት ያለችው ንብ ፎቶ ሲያነሳ ነበረ።

የንቧ ፊት ለፊቴ መጥታ በአፍ ጢሟ ድፍት ማለት ግን አይገርምም…?

ነፃነታችን በእጃችን ነው።

IT IS SO…!!!!

(ምንጭ: ፎቶና ጽሁፍ ከAmdom Gebreslasie ፌስቡክ ገጽ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 9, 2015 08:35 pm at 8:35 pm

    “ንብ ከተደፋች ከእግርህ ሥር
    ልታቆም ነወይ መቅሰሟን ልትበላ ሳር
    ሁሉ መረረ ጠፋ የማር አንጀራ በሀገር
    ከተደፉ ይቅር በላቸው አትጨክን ማር”
    በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule