• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደሳለኝ ደበረኝ

November 1, 2015 04:59 pm by Editor Leave a Comment

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ” “መንግሥት ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። እነዚህ ከባባድ ኢንቨስተሮች ምርቱን በሞኖፖል ከያዙት፣ ይኸ ነገር በሃገራችን “እየተሰፋፉ የመጡትን መካከለኛ ኢንቨስተሮች” ሊያፈናቅላቸው ይችላል ተብሎ ይሰጋል። ይህንን እንዴት ይመለከቱታል።

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ትክክል ነው ልማታዊው መንግሥታችን ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። ይህን ነገር እኮ እኛ የፈለሰፍነው አይደለም። ከሌሎች ሃገሮች ተመክሮ (ኮርጀን – ባግባቡ ወይም ባላግባቡ) ወስደን፣ ለምሳሌ ከደቡብ ኮርያ፣ ቬትናምና ቻይና አይተን ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምንሰራበት ምክንያት ኢንቨስተሮች እንዳይቸገሩ ነው። ለምሳሌ መብራት እንዳይቋረጥባቸው። እነሱ ለምን ይቸገሩ? እ? ጨርቁን ቀለም እየቀቡት እያለ መብራት ቢቋረጥ እኮ በቃ ያ ሁሉ ጨርቅ ተበላሸ ማለት ነው። ባለም ገበያ ላይ እኮ ተወዳድረው ነው የሚሸጡት…እ!” (ይሄ የመጨረሻው አረፍተ ነገር ቃል በቃል የተወሰደ ነው [1] ከ 4ኛው ደቂቃ ጀምሮ።

እንግዲህ የትልልቅ ኢንቨስተሮች መብዛት አነሥተኛ ኢንቨስተሮችን ያፈናቅላል አያፈናቅልም ለሚለው ጥያቄ መልሱን አልሰማሁም። ዎልማርት አንድ ቦታ ሲከፈት ያካባቢውን ትንንሽ ነጋዴዎች እንደሚያፈናቅለው ማለት ነው። ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ነው መልሱ። እኔ ደግሞ ይህንን መልስ ሰምቼ ደሳለኝ ደበረኝ። (ወፍጮ ቤቶችና ሱቆች እየፈረሱ መሬት ለሌሎች እየተፈለገ እያለ ማለት ነው።)

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ሶቨሪን ቦንድ የሚባለው ነገርስ ለሃገራችን ትልቅ ጫና ይሆናል የሚባለውስ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እሱማ ምንም ችግር የሌለበት ብድር ማለት እኮ ነው።ከቻይናና ከወርልድ ባንክ ስትበደሪ ጣጣ አለው። ለምሳሌ ለምን እንደምትፈልጊው፣ ምን ፕሮጄክት ላይ ማዋል እንደምትፈልጊ በዝርዝር ጽፈሽ፣ ፈርመሽ ነው የምትቀበይው። ሶቨሪን ቦንድ ግን በቃ ብር ሥጡኝ ብለሽ መበደር ነው። በሶስት ቀናት የሚገኝ ብድር ነው። ለፈለግሽው ጉዳይ ማዋል ትችያለሽ። እኛ ግን ዝም ብለን ልንበላው አይደለም የምንበደረው … ለሜጋ ፕሮጄክቶች እንዲሆን ነው”

“በሶስት ቀን የሚገኝ ብድር?” … እንዴ ከማን ነው የምትበደሩት? ከማፍያ? “ዝም ብለን ልንበላው አይደለም? ሜጋ ፕሮጄክቶች? ለምሳሌ የብአዴን 35ኛ አመት ማክበሪያ ሜጋ ፕሮጄክት … እየጨፈረን፣ ዝም ሳንል የምንበላው?” ብለን እንጠራጠር የሚል ሃሳብ ውል ባይልብኝም የደሳለኝ መልስ ግን ደበረኝ።

የኢቢሲ “ጋዜጠኛ” “ግብጽ በአባይ ግድብ የተነሳ በጣም ከማሥጋቷ የተነሳ መሳሪያ እያጠራቀመች ነው ይባላል። ይህንን እንዴት ያዩያል?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ግብጽ ከፈለገች ሃገሩን በሙሉ መሳሪያ ታድርግ። የሚዋጋው መሳሪያ አይደለም አስተሳሰብ ነው”

ደሳለኝ አሳቀኝ። የሚዋጋው አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚባል አስተሳሰብ ነው?

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “መንግሥትዎ ዲሞክራቲክ ነው?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ያለጥርጥር።”

ደሳለኝ አሳቀኝ። ጥርሴ እስኪነቃነቅ።

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “የእርስዎ መንግሥት የሚኮራበትና ሁሌም የሚለው ሃገርዎ እንዴት እያደገች እንዳለች ነው። አነጋጋሪው ጉዳይ ግን የእድገቱ ተጠቃሚዎች በአንድ እጅ ላይ ባሉ ጣቶች ብቻ የሚቆጠሩ ብቻ ናቸው መባሉ ነው። ምን ይመልሳሉ ለዚህ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ጥያቄሽ ጠለቅ ያለ ምርመራና ጥናት የጎደለው ነው። በሃገራችን ከ70 ሚሊዮን ገበሬዎች መሃከል ከድህነት መሥመር በታች ያሉት 15 በመቶ ብቻ ናቸው። ሌላው ሃብታም ነው።”

ማርቲን ዴኒስ ከአልጃዚራ “ሃብት በሃብት ከሆናችሁ ታዲያ እልፍ አእላፍ ኢትዮጵያውያን ለምን ይሰደዳሉ?”

¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “እንዴ? አልጃዚራ ስለ ስደተኞች ዶክሜንተሪ ሲሰራ አንድም ኢትዮጵያዊ አላሳየም እኮ! ይህ በመሆኑ በጣም ነው ደሳለኝ።” [2] ከ10:47 ደቂቃ ጀምሮ ያዳምጡ።

ደሳለኝ ደሳለኝ አለ። እኔን ግን ደሳለኝ ደበረኝ።

ማብራሪያ ¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ ላልኩበት ምክንያት።

ባለፈው ሰሞን አንድ ደሳለኝን የሚያሞግስ ጽሁፍ አነበብኩ። እኚህ ሰውዬ ደሳለኝ ሥልጣን የሚጋሩት ኒዎ ሊበራሎች እንደሚናገሩት አሻንጉሊት ሆነው ሳይሆን በሃገራችን ሥልጣን የመጋራት ልምድ ኢህአዲግ በማስለመዱና በማስፈሩ ነው ብለው ይደመደማሉ። ከሌሎች ሶስት ሰዎች ጋር ሥልጣን ከተጋሩ ደሳለኝ እንግዲህ ¼ኛ ጠ/ሚ ናቸው። በጫወታችን ላይ የሚያስቀኝ ነገር በጠፋበት ዘመን እኝህ ሰውዬ ይህንን ጽፈው ስላሳቁኝ ባለውለታዬ ናቸው።።

[1] https://www.youtube.com/watch?v=pOSDvm4weOM

[2] https://www.youtube.com/watch?v=VwimUr2C7mY

***********

ጌቱ ኃይሉ አማዞን (amazon.com) ላይ በመሸጥ ያለው ጸሃዮቹ (tsehayochu) የተባለው መጽሃፍ ደራሲ ነው።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule