“መዝሙሩማ” መዝሙር ነው - የኅብረ-ዜማ ውጤት፣ ሕዝብን ያስተሳሰረ - የአንድነት ሰንሰለት፤ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ - ከደቡብ እስከ ሰሜን... ተዳርሶ በድንገት፣ በቅብብሎሽ ያስተጋባ - የነጻነት አዝማች ልደት! ደራሲውም ሕዝብ ነው - መሳሪያውም ባህላዊ፣ ዘረኞችን እሚያሸማቅቅ፣ ግፈኞችን እሚያርበደብድ... ኃያል ድምፅ ምትሃታዊ! “መዝሙሩማ” መዝሙር ነው - የብሩህ ዘመን ብስራት፣ በደም ቀለም የተጻፈ! - እሚዘመር በሕዝብ አንደበት! (ስማ! አቶ “ጌታቸው”!) . . . ከእንግዲህማ አትልፋ - ዘመንህን በከንቱ አትጨርስ፣ ክፋት ፕሮፓጋንዳህን - እሳት ባገር ከመለኮስ፣ ይልቁንስ ጠጋ በል -“ሕዝበ-መዝሙሩን” በደንብ አጥና፣ ያንተም መፃዒ ዕድል - በሕዝብ ድል እንዲቃና! እንጂማ!... መዝሙሩማ ኀብረ-መዝሙር … [Read more...] about “መዝሙሩማ…”!
Left Column
“የማን ተጋድሎ ነው…?”
ወያኔ ኢትዮጵያን እያፈራረሰና ህዝቡን ‘ርስ በርስ እያባላ ያለው ብቻውን አይደለም። የሀገሪቱ ጠላቶች፣ ሆድ-አደሮች፣ መሀል-ሰፋሪዎች፣ ግብዞችና የመሳሰሉ ሁሉ አጋጣሚውን ይጠቀማሉ። ሲጠቀሙም ኖረዋል። ወያኔና ግብረ–አበሮቻቸው እኮ ኢትዮጵያን የማፈርስረሱን መረሀ-ግብር የተቀበሉት ከምዕራቡና ከዐረቡ ዓለም ነው። መርሳት የሌለብን ወያኔ ከዚህ ደረጃ እንዲደርስ የኛ አስተዋ’ጾ መሆኑን መቀበል አለብን። ማርቲን ሉተር ይመስለኛል፤ "ካልተጎነበስክላቸው እነሱ ከአንተ ጀርባ ላይ አይወጡም!" ያለው። ቁምነገሩ ካለፈው መማር መቻላችን ላይ ነው። በርግጥ አሁን ብዙሀኑ የወያኔን “አሪወሳዊነት” ከማንኛውም ግዜ በበለጠ የተረዳበትና የ40 ዓመት የከፈፍለህ የቤት ስራ "ፉርሽ" የሆነበት ነው። ይሁን እንጂ ብዙ ድህረ-ገጾች፣ ዜና – ዘጋቢዎች፣ ዘፋኞች፣ ሰላማዊ … [Read more...] about “የማን ተጋድሎ ነው…?”
The Untold Plight of the Amhara People
The massive civil uprising in Ethiopia last week has captivated the attention of the world. Needless to say the world is now well aware of the protest by the Oromo ethnic group, the so called Oromo Protest, that has been going on for the last nine months. The second largest ethnic group, the Amhara, joined the uprising last week. The magnitude and consistency of the uprising in Amhara is quite a surprise and uncommon for many non-Ethiopians, including the mainstream media. It has however been … [Read more...] about The Untold Plight of the Amhara People
የዋዜማ አቋም እና ጥሪ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ
“የዋዜማ አቋም እና ጥሪ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ” በሚል ርዕስ የዋዜማ ሬዲዮ ይፋ ያደረገውን መግለጫ የጎልጉል ኤዲቶሪያል ቡድን ተወያይቶበታል፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተቋቋመበት ዓላማና ከሚከተለው የአስተሳሰብ መስመር አንጻር የዋዜማ መልዕክት አብሮት የሚሄድ በመሆኑ የቀረበውን ወቅታዊ ጥሪ ከነሙሉ ዓላማ ከዚህ በታች አትመናል፤ በቀጣይ ለሚደረጉ ሥራዎችም እንደ ሚዲያ የሚጠበቅብንን ሁሉ ለመፈጸም ፈቃደኞች መሆናችንን እና ሌሎችም በተመሳሳይ ተግባር ላይ ያላቸውን ትብብር እንዲያሳዩ በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡ ኢትዮጵያ አሁን የደረሰችበት ፖለቲካዊ ቀውስ ከወትሮው በተለየ አስጊና አስከፊ አደጋን ያረገዘ ሆኖ ይታያል። የፖለቲካ ቀውሱን “የመልካም አስተዳደር እጦት፣ የዴሞክራሲ አለመዳበር” እያሉ መግለጽ ከፊታችን የተደቀነውን አደጋ አቅልሎና የተለመደ … [Read more...] about የዋዜማ አቋም እና ጥሪ በወቅታዊው የኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ
ከትህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን ይውረድ የሽግግር መንግስት ይቋቋም
በአጠቃላይ ለ25 ዓመታት ሙሉ ህዝባችንን አፍኖ ሲገዛ የቆየና፣ ለ40 ዓመታት ሰላማዊ ዜጎችን እየረሸኑ አገራችንን እየዘረፉ የቆዩ ባለስልጣኖች ያሉበት ህወሓት/አህአዴግ በተለይ በዚህ ዓመት በኦሮሞና በአማራ ህዝባችን ላይ ጦርነት ከፍቷል። የአገዛዙን የግድያ ወንጀሎች እናወግዛለን፤ የህዝቡን ተቃውሞ እንደግፋለን። ስለዚህ በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲገነባ፣ የህዝባችን አንድነት እንዲጠናከርና የአገራችን ሉኣላዊነት እንዲከበር᎓- 1. ህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን መወገድ አለበት 2. በኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ሲቪክ ማህበሮችና ብቃት ባላቸው ግለሰቦች የሽግግር መንግስት መቋቋም አለበት። ከዚህ በላይ የተጠቀሱትን ዓላማዎች ለማሳካት የሚከተለውን ጥሪ እያቀረብን ፣ እኛም ከህዝባችን ጐን ተሰልፈን ለትግሉ መሳካት የአቅማችንን እንደምናበረክት ቃል እንገባለን። 1. ሁሉም … [Read more...] about ከትህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን ይውረድ የሽግግር መንግስት ይቋቋም
ቅኝ ተገዥነቱን ያወቀ ሕዝብ በከፊል ነፃ ነው!
የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሬ ወያኔ ቅኝ ተገዥ ከሆነ ድፍን 25 ዓመት ሆነው። በእነዚህ ረጅም ዓመታት፣ የተማሩትም ሆነ ያልተማሩት ዜጎች፣ በቅኝ ተገዥነት መያዛቸውን ያወቁትም ሆነ ለማወቅ የጣሩት በጣም ጥቂቶች ናቸው። እነዚህ በቅኝ ተገዥነት ተይዘናል ያሉት የጥቂቶቹ ድምፅ፣ በብዙኃኑ፣ ከሁሉም በላይ በጎሣ ፖለቲከኞቹ ድምፅ ተውጦ፣ ወያኔ፣ ያላንዳች ሀግ ባይ፣ ሩብ ምዕተ ዓመታት የአገሪቱን ብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት በእጅጉ የጎዱ ሥራዎችን እንዲሠራ ሠፊ ዕድል ሰጠው። በመሆኑም የኢትዮጵያዊነት አያያዥ ማገርና ወራጅ፣ መሠረትና ጭምጭም የነበሩትን፣ የኢትዮጵያዊነት ዕሴቶቻችን ከሥራቸው ነቀላቸው። ሕዝቡን በነገድ ከፋፍሎ እሣትና ጭድ አደረጋቸው። የኢትዮጵያ ነገዶች ሙጫ በመሆን ከሌሎች ነገዶችና ጎሣዎች ጋር ሰምና ፈትል ሆኖ፣ ኢትዮጵያዊነትን ሲገነባ የኖረውን የዐማራ ነገድ፣ በዘር ጠላትነት … [Read more...] about ቅኝ ተገዥነቱን ያወቀ ሕዝብ በከፊል ነፃ ነው!
ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!
ይድረስ ለእኛ-ከእኛ! - ከላይ ልጀምር ካ’ናቱ፣ በብረት ኃይል ተከቦ - ከተኮፈሰው በከንቱ፣ ይድረስልኝማ ለወያኔ - ለጊዜያዊው ባለጉልበቱ፤ … “ለሕዝባዊነት መጣሁ” ብሎ - ሕዝብን በጥይት መቁላት የለምና፣ አቆልቁለህ እየውማ - የምትሄድበትን ጎዳና! የጭካኔ መጠንህ ጫፍ ደረሰ - የውሸት ቋትህ ሞላ፣ የ’እውቀት‘ ገደብህ አበቃ - ከእንግዲህ ላይኖርህ የቀረ ‘መላ’፣ ከወደቁ ወዲያ መንፈራገጥ.. እንዳይሆን ለመላላጥ፣ ሳሩንም ላለመጋጥ.. መሬቱንም ላለመናጥ…፣ ከአውሬነት ባህል ተላቆ - ሰውነትን ይሻልና፣ ይድረስ! ይድረስ! እልሃለሁ፤ ይድረስ! እንደገና፤ ዛሬ እንኳን እንደማመጥ - ይቅርብህማ ወንድሜ፣ በግፍ ተሞልተህ ጉዞ - ላይሆንህ መልካም ዕድሜ፣ “አበቅቴ ውሉን ሳይስት” - የአመሻሽ ጀንበር ሳትጠልቅብህ፣ ቆም ብለህ ማሰብ ጀምር - እንደ “ጆቤ”ህ፣ እንደ … [Read more...] about ይድረስ ለእኛ—ከእኛ!
ለመፍትሔው መፍትሔ
በሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ተንሳይ የመፍትሔ ሀሳቦች ምላሽ ለ፡ ሌ/ጄ ፃድቃን ገ/ተንሳይ “የሃገራችን ፖለቲካ ሁኔታና የመፍትሔ ሀሳቦች” ጽሁፍ እነሆ 17 ዓመት በበረሃ 25 ዓመት በመንግሥት ሥልጣን የተቆናጠጠው ወያኔ ዛሬ የሥልጣን ዘመኑ ማብቂያው የመጨረሻው መጀመሪያ ላይ ደርሷል። በትግሉ ላይ ነበርን ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ አመራር እርከን ላይ ነበርን የሚሉ የወያኔ ባለሥልጣን፤ የድርጅታቸውን 17 ዓመት የትግል ጉዞ አብረው ፕሮግራም ሲነድፉ፣ ፖሊሲ ሲያወጡ፣ የትግራይ ነፃ አውጪ ብለው በዘር ሲደራጁ፣ የዐማራ የበላይነት ሰፍኗል ብለው አማራ ላይ ሲያነጣጥሩ፣ የብሔር/ብሔረሰቦች መብት እስከመገንጠል ብለው የዘር ፖለቲካ ሲያራምዱ፣ ኤርትራ በኢትዮጵያ ቅኝ ተይዛለች ብለው ከሻቢያ ጋር ለኤርትራ ነፃነት ሲታገሉና ሲያታግሉ የነበሩ ዋናው የድርጅቱ አመራር ባልደረባ ዛሬ የወያኔ ወንበር እንዳበቃለት … [Read more...] about ለመፍትሔው መፍትሔ
አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)
‹‹ጥበበኛ በጥበብ እግር ይመላለሳል›› (ጠቢብ የሐውር በእግር ጥበብ) እንዲሉ፣ አባተ መኩሪያ ከግማሽ ምታመት በዘለለ በኢትዮጵያ ቴአትር ሕዋ ውስጥ በጥበብ ለጥበብ ኖሯል፡፡ ለቴአትር እስትንፋሱ ነበርም ይሉታል፡፡ በርሱ ጥበብ ያለፉት ሁሉ፡፡ በጥበብ የባተው አዘጋጅ፣ የውዝዋዜ አሠልጣኝ (ኬሪዮግራፈር)፣ ጸሐፌ ተውኔት፣ የፊልም አዘጋጅ የነበረው አባተ መኩሪያ በአገሪቱ የቴአትር ታሪክ ውስጥ ስማቸው በግዘፍ ከሚነሱትና አሻራቸውን ካሳረፉ በኩሮች አንዱ ነበር፡፡ በተለይ በተውኔት አዘጋጅነት ስመ ጥር ለመሆኑ ዘመን ተሻጋሪ ተውኔቶችን ወጥ እና ትርጉሞች በማዘጋጀቱ ይጠቀሳል፡፡ ከታዋቂ ሥራዎቹ መካከል ሀሁ በስድስት ወር (1966) አቡጊዳ ቀይሶ (1971)፣ መልእክተ ወዛደር (1971)፣ የመንታ እናት (1971)፣ መቅድም (1972)፣ ጋሞ (1973)፣ አሉላ አባነጋ (1979) ይጠቀሳሉ፡፡ … [Read more...] about አባተ መኩሪያ “ተንቀሳቃሹ ቴአትር ቤት” (1932 – 2008)
ለኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጥብቅና!
ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን በግሌ አላውቀውም፤ ነገር ግን እስከሚበቃኝ ድረስ አውቀዋለሁ። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እኔን አያውቀኝም፤ ነገርግን እኔና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ጠበቆቹ እንዳለን ያውቃል። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጎንደር ውስጥ አንገረብ እስርቤት ባሁኗሰዓት - ምሽት፣ ረቡዕ ሐምሌ ፳፯ ቀን ፳፻፰ ዓመተ ምህረት - ለጊዜው አለ። እዚያ እንዲቆይ ያደረገው ወገኑ ነው። ሁላችንም እንደምናውቀው፤ በእስርቤት ያለ ግለሰብ፤ በትክክል ይሁን በድፍረት በመታሰሩ ብቻ፤ ጠበቃ ያስፈልገዋል። እናም ጠበቃው ነኝ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ለኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጥብቅና!










