• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የማን ተጋድሎ ነው…?”

August 16, 2016 12:15 am by Editor Leave a Comment

ወያኔ ኢትዮጵያን እያፈራረሰና ህዝቡን ‘ርስ በርስ እያባላ ያለው ብቻውን አይደለም። የሀገሪቱ ጠላቶች፣ ሆድ-አደሮች፣ መሀል-ሰፋሪዎች፣ ግብዞችና የመሳሰሉ ሁሉ አጋጣሚውን ይጠቀማሉ። ሲጠቀሙም ኖረዋል። ወያኔና ግብረ–አበሮቻቸው እኮ ኢትዮጵያን የማፈርስረሱን መረሀ-ግብር የተቀበሉት  ከምዕራቡና  ከዐረቡ ዓለም ነው። መርሳት የሌለብን ወያኔ ከዚህ ደረጃ  እንዲደርስ የኛ አስተዋ’ጾ መሆኑን መቀበል አለብን። ማርቲን ሉተር ይመስለኛል፤ “ካልተጎነበስክላቸው  እነሱ  ከአንተ  ጀርባ  ላይ  አይወጡም!” ያለው። ቁምነገሩ ካለፈው መማር መቻላችን ላይ ነው።

በርግጥ  አሁን  ብዙሀኑ  የወያኔን  “አሪወሳዊነት”  ከማንኛውም  ግዜ  በበለጠ  የተረዳበትና  የ40 ዓመት የከፈፍለህ የቤት  ስራ “ፉርሽ” የሆነበት ነው። ይሁን  እንጂ  ብዙ  ድህረ-ገጾች፣  ዜና – ዘጋቢዎች፣ ዘፋኞች፣  ሰላማዊ ሰልፎኞች፣ የፓለቲካ ተንታኞች፣ መግለጫዎችና የመሳሰሉት በሚያሳዝንና በሚያሳፈር ሁኔታ ከወያኔ የጎሳ ወጥመድ ያለመላቀቃችን፤ “አንድ ‘ርምጃ  ወደፊት፣  አንድ ‘ርምጃ ደግሞ  ወደ  ኋላ” መሆኑ  በግዜ  ሊታሰብበትና ሊታረም የሚገባ ጉዳይ ነው። እናም  የምንናገረውንና  የምንጽፈውን  በጥንቃቄ መመርመርና፤ ወያኔ  የማይቆፍረው  ጉድጎዳ፣ የማያፈሰው  ደም እንደሌለ ከምንግዜውም  የበለጠ አሁን  መረዳት  ያስፈልጋል።

  • “የአማራ ተጋድሎ!….. የኦሮሞ ተጋድሎ!….. የመሳሰሉ ዜናዎችና  መፈክሮች   የሚያመለክቱት አሁንም   ደም እንደጎርፍ  እየፈሰሰና ምድራዊን ስቃይ እየተቀብለን፣ ወያኔ ካሰመረልን የጎሰኝነት  ስሜት  ያለመውጣታችን የሚያመለከት ነው። ለምንድን ነው “የኢትዮጵያኖች ተጋድሎ!” የማንለው?…..እድግመዋለሁ፤ “የኢትዮጵያዊኖች ተጋድሎ!”። አማሮች እንዲህ… አድረጉ… ኦሮሞዎች እንዲህ ሆኑ… አደረጉ…. ወዘተ…. እያልን፤ በአንድ  አካባቢ  አንድ  ወጥ  ህዝብ   እንዳለ  አድርገን  ማቅረባችንና  መዘገባችን  ይቁም። በተለይም ኢሳት (ቲቪና  ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ህዝብን ዓይና ጆሮ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ ጉዳይ ግን ቢያስብበት መልካም ነው እላለሁ።

በዚች ሰዓት ጋምቤላዎች  የከፍሉት መሰዋ’ትነና  እየከፈሉት  ያለው  ተጋድሎ፣  የኦጋዴኖችና  አንዲሁም  በተለያየ ግዜ በተለያዩ የሀገሪቱ  ግዛቶች  ከወያኔ ጋር የሚተናናቁት ሁሉ የኢትዮጵያኖች ያውም  የዚህ ኢትዮጵያዊ ትውልድ ተጋድሎ እንጅ የማን ሊባል  ይችላል? ካላያማ ከወያኔ በምን ተለየን? የተጀመረውን የጸረ-ወያኔ  የጎሳ ከፋፍለህ  ግዛው እንዴት ነው  የምናከሽፈው? “የዚያ  ጎሳ  ተጋድሎ!.. የዚህ ጎሳ ተጋድሎ!….” እያልን  እንዴት  አድርገን  ነው  ትግሉን ለህዝባዊ ፣ ለሁሉም  ኢትዮጵያዊ  ድል  የምናበቃው?

  • ሌላው የስሞኑን ህዝባዊ አመጽ ያቀጣጠለው የወልቃይት ጉዳይ  ነው። የወልቃይት ጥያቄ የሁሉም  ኢትዮጵያዊ ጥያቄና  ትግል  ነው። ኢትዮጵያዊ  ዜጋ  ነኝ  የሚል ሁሉ ይመለከተዋል። ይሁን እንጂ “ወልቃይት አማራ!…” የሚለው አባባል፣ መፈክርና ቀረርቶ የወያኔ የጎሳ ስራ መስራቱን ነው የሚያመለክተው። “ወልቃይት …  የጎንደር አንዱ ግማድ ነው፤ ለዚህም የህይወት መሰዋትነት ብቻ አይደልም፤ የዘር ማጥፋት ወንጀል እየተፈጸመበት ያለ ህዝብ ነው። ያ ማለት ደግሞ “ወልቃይት – ጎንደር፤ ጎንደር – ኢትዮጵያ  ነው።” ይህም ማለት “ኢትዮጵያ ከሌለች – ወልቃይት – ጎንደር የለም”። ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚስማመው “በኢትዮጵያዊያን ተጋድሎ!….” ነው። ትግሉ የሁሉም ኢትዮጵያዊ  መሆኑ  በዚህ ሰዓት መዘንጋት  የሌለበት ጉዳይ ነው። ለመሆኑ የሌላው ኢትዮጵያዊ ተጋድሎና መሰዋትነት የት ሊጣል ነው? የአብሮነት ትግል ባላማካሄዳችን አይደልም ወይ፤ ወያኔና  ሆድ-አደሮቹ ሀገራችን የግላቸው እቃ አድርገው ህዝብን እንደቅጠል የሚያረግፉት።
  • ወያኔ ለኢትዮጵያ ጎሳዎች ብሎ   የጫነብን  ሰንደቅ –ዓላማ፤  በየተኛውም  ኢትዮጵያዊ ተቀባይነት  አለመኖሩ ብቻ  አይደለም፤ ነባሩ ሰንደቅ – ዓላማ የኢትዮጵያ ህዝብ የአንድነትና   የተጋድሎ  መግለጫ   መሆኑን እያስመሰከረ  ነው።  ስለዚህም  በህዝባዊ  አመጽ   ወቅት  የቡድን  ወይም  የድርጅት  ሰንደቅ  ዓላማ  ይዘን መውጣታችን ይከፋፍለናል እንጅ  አንድ  አያደርገንም። በርግጥ  በአንዳንድ  የደቡብ  ክፍል  የወያኔ ካድሪዎች የአንዳንድ ድርጅቶችን “ሰንደቅ  ዓላማ” ይዘው  በመውጣት  ህዝብን  ለመምታትና  ለመከፋፈል  እየተጠቅሙብት  ቢሆንም፤ እኛ ግን አንድነታችን  በተግባር  እናስመስክር። እየተከፈለ  ያለው  የህይወት መሰዋትነት  ነው።
  • ሰሞኑን  ከተቀሰቀሰው ህዝባዊ አመጽ ጋር  አንዳንድ  ዘፋኞች  ከትግሉ  ጋር  በተያያዘ   ነጠላ ”የቅሰቀሳና የውዳሴ”  ዜማ ለቀዋል፡:  በተለይም ስለ  “ወልቃይት-ጎንደር፣ …….ስለ ኦሮሚያ፣….  ወዘተ።  ይሁን  እንጂ  በ’ኔ እይታ ዜማዎቹ  በደንብ  የታሰበባቸው አይደሉም። “ኢትዮጵያዊ”  አንድምታ  የላቸውም። ተጋድሎውና ህዝባዊ  አመጹ የመላው  ኢትዮጵያዊ በመሆኑ  ዜማዎቹም  የሁሉንም  ኢትዮጵያዊያን አንድነትና  ጅግንነትን የሚያወድሱና የሚቀሰቅሱ   መሆን  ሲገባቸው  በአካባቢያቸው  ተወስነዋል።   የወያኔች  በጎሳ  ላይ  በተመሰረተ የጥላቻና  የግብዝነት  ከበሮ -ድለቃ ፤ የምን ያህል የወርዱና  የዘቀጡ ኅሊና ያልፈጠረባቸው መሆናቸውን የሚያመለክት ሆኖ ሳለ፤ የ’ነሱን  ፈለግ  መከተሉ “በአንድ  አፍ  ሁለት  ምላስ  …” ይሆንብናል። “ወልቃይት ብረሳሽ፣ ቀኜን ይርሳኝ!..!” ከማለት “ኢትዮጵያ … ብረሳሽ፣ ቀኜን  ይርሳኝ!” ብሎ ቢያንጎራጉር፤ ለአንድነታችንና ለትግላችን የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ነው። ለወያኔም  የራስ  ምታት  ነው።  ኢትዮጵያ እንዳትኖርና  እንድትፈራርስ እኮ ነው  ወልቃይትና ሌሎችም አካባቢዎች  ለወያኔ  የተከለሉትና  ለሱዳን  እጅ መንሻ የሚቀርቡት። እናም በተቻለ መጠን የትግል ዜማችን የሁላችንም ሀገር ልናደርጋት መሰዋ’ት  ለምንከፍልላት  ኢትዮጵያችንና  ህዝባችን  ይሁን።

ያለፉትም ሆነ አሁን ያሉት “ጅግኖቻችን” የከፈሉት መሰዋትነትና እየከፈሉ ያሉት ለኢትዮጵጵያና ለኢትዮጵያዊያን ነው። ታዲያ እነዚህን የክብር የኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ወደ መንደርተኛነት ማውረድ ምን ይሉታል?። ቢቻል በዚህ ሰዓት ዘፋኞች  በህብረት ለሁሉም ኢትዮጵያዊ  የሚሆን  በተለያዩ የሀገሪቱ ቋንቋዎች ዜማ ቢለቁ ለትግሉም ሆነ ለአንድነታችን የበኩላቸውን አስተዋ’ጾ ያደርጋሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ በተለይም ባህር-ማዶ የምትገኙት እንደ አለምፀሀይ  ወዳጆና  ታማኝ  በየነ ያላችሁ፤ የጥበብ ሰዎችን እንደተለመደው  ብታሰተባብሩ ”ለቀባሬው ማርዳት” ባይሆንብኝም  መለዕክቴ  ይድረሳችሁ።

ፊልጶስ / ነሀሴ 2008 / E-mail: philiposmw@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule