የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅና አለአግባብ ለመበልጸግ ያሰቡ አውሮጳውያን በአሜሪካ አካባቢ ያሉትን አገሮች በጥጥና በሸንኮራ አገዳ እያለሙ መጠነሰፊ ሃብት ለማጋበስ በሰላም የሚኖሩ አፍሪካውያንን በግፍ እያጋዙ ዓለማችን እስካሁን ዓይታ የማታውቀውን ዓይነት የባርነት ሥርዓት ለበርካታ ዓመታት አካሂደዋል፡፡ ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ በግፍ የተጋዙት ወገኖች በመንገዳቸው ያሳለፉት መከራና ከዚያም ለማሽን እንኳን የሚሰጠው ዕረፍትና ጥገና እነርሱ ተነፍገው ለመቶዎች ዓመታት ከምንም ጋር የማይወዳደርና የማይነጻጸር ሰቆቃ አሳልፈዋል፡፡ የዚህ መራራ ግፍ ውጤት አሁንም አብዛኛውን የዓለማችንን ክፍል እየናጠው ነው፡፡ በዚህ አስከፊ ዘመን በባርነት ሥር የሚማቅቁት እንደ ንብረት ይቆጠሩ ስለነበር በምርጫ አይሳተፉም ነበር፡፡ ሆኖም ካላቸው ከፍተኛ የህዝብ ብዛት አኳያ ባሪዎችን አስቆጥረው በርካታ የምክርቤት … [Read more...] about የጻድቃን “መፍትሔ ሃሳቦች” – ልመና? ጥገና? ወይስ ህወሃት ቁጥር 2?
Left Column
The Necessity of Cultural Reform: Working with time, not against
In my recent article entitled “The Power of Culture: Why we couldn’t make lasting transformations”, I argued that reforming our culture is critical to experience lasting and sustainable change but, at the same time,very challenging. As promised, in the coming couple of articles, I’d like to propose just a few of the cultural attributes we may consider reforming. Let me begin this journey by suggesting a change that may not draw serious controversies since, compared to my upcoming reform … [Read more...] about The Necessity of Cultural Reform: Working with time, not against
የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ
አቶ ዠ፣ ከ Fast Lane ዩኒቨርስቲ በተልዕኮ በአራት ወራት እድሜ የዶክትሬት ድግሪ የተጫነባቸው የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። በ“ተልዕኮ” ማለት ለ Fast Lane ዩኒቨርሲቲ ደብዳቤ መጻፍና ገንዘብ መላክ ነው ተብሎ ይታማል። ይህን ሃሜት እኔ ጭምጭታ ነው የሰማሁት። ጭምጭምታው ግን ከሁነኛ (አስተማማኝ) ሰው ነው። አቶዠ፣ቀድሞ በደርግ ጊዜ መፈክር ጸሃፊ፣ በኋላም በኢሃዲግ ጊዜ ልማታዊ ጸሃፌ ተውኔት፣ቀድሞ የኢሃዲግ ፍቅር ቤት ሥራ አስቀማጭ፣ ይቅርታ ሥራ አስኪያጅ፣ በዩናይትድ ኔሽንስ የኢትዮጵያ ተወካይ፣ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት በራስ አነሳሽነት ተወዳዳሪ፣ ወዘተርፈ...ወዘተርፈ....ወዘተርፈ....እንዳልኩት የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። ሆኖም ችግር … [Read more...] about የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ
“የኢትዮጵያን ችግር በኢህአዴግ መዋቅሮች ታጥረን መፍታት አንችልም” ጻድቃን ገ/ትንሳኤ
ህወሃት አገር የመገንጠል ዓላማውን አንግቦ የትጥቅ ትግል በጀመረበት ጊዜ ከተጋዳላይነት ተነስተው በአጭር ጊዜ ውስጥ የሌፍተናንት ጄኔራል ማዕረግ ለመጎናጸፍ የበቁት የቀድሞው ኤታማዦር ሹም ጻድቃን ገ/ትንሣዔ “የሃገራችን ፖለቲካዊ ሁኔታና የመፍትሔ ሃሳቦች” በሚል ርዕስ “Horn Affairs” ላይ ለወቅቱ የአገራችን ችግር ይበጃል ያሉትን የመፍትሔ ሃሳብ አቅርበዋል፡፡ እነ ስየ አብርሃን ወደ ወኅኒ የጣለው ህንፍሽፍሽ በተከሰተ ጊዜ የመለስ ወገን ከመሆን ይልቅ ከውህዳኑ እነተወልደ ጋር በመወገናቸው በሳሞራ የተተኩት ጻድቃን አሁን እንደመፍትሔ ያቀረቡትን ሃሳብ አንዳንድ ወገኖች መልካምና የሰከነ አስተሳሰብ በማለት ሊደገፍ እንደሚገባ ሃሳብ ይሰጣሉ፡፡ በህወሃት ግፈኝነት የተማረሩና ህወሃት ካልተወገደ ሰላም አይኖርም የሚሉ ደግሞ የጻድቃንን ሃሳብ “ከዝንብ ማር አይጠበቅም” ብለው በመፈረጅ … [Read more...] about “የኢትዮጵያን ችግር በኢህአዴግ መዋቅሮች ታጥረን መፍታት አንችልም” ጻድቃን ገ/ትንሳኤ
ተጋሩን አትንኩት!
የኢትዮጵያ ፖለቲካ በገባኝ መጠን፡- በአሁኑ ሰዓት ሀገሪቱን የሚመራት ቡድን ራሱን ወደ ገዥ መደብነት ቀይሯል፡፡ በገዥ መደብ ውስጥ የህወሓታዊያን ኃይል ገኖ የወጣ መሆኑ ለክርክር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም፡፡ ይሁንና ገዥ መደቡን "ያጸኑት"’ ሌሎች ኃይሎች እንዳሉ መካድ ያስተዛዝባል፡፡ የፖለቲካ ኃጢያት ትንሽ የለውም፡፡ የምንግዜም የደረጃ ሁለት ተፋላሚዎች የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች፤ የአድርባዮ ኦህዴድ ባለ ስልጣናት፤ ሚዛን አስጠባቂዎች የዲኢህዴን ሰዎች እና የአጋር ድርጅቶች ተቀጥላ ምሁራን (auxiliary elites) አሁን ላይ ወደ ዝግ አምባገነንነት እያዘገመ ላለው ገዥ መደብ ማንአህሎኝ ባይነት የራሳቸዉ የሆነ የማይናቅ ሚና አላቸዉ፡፡ የነዚህ ድርጅቶች ቁንጮ መሪዎች የገዥ መደቡ መሐንዲሶች ናቸው፡፡ ዛሬ ላይ ላለዉ በደልና ጭቆና ዋነኛ ተጠያቂዎችም የገዥዉ መደብ የፖለቲካ … [Read more...] about ተጋሩን አትንኩት!
በጎንደር የተጀመረው አመጽ የአማራው ሕዝብ የሕልውና ትግል ነው !!
ባለፉት 25 አምታት የአማራው ሕዝብ ላይ በትግሬ ወያኔዎች የተፈጸመበት ግፍና መከራ ፤ በአይነት ፤ በመጠንና በይዘት ተሰፍሮና ተነግሮ የማያልቅ ነው። አማራው ኢትዮጵያዊነቱን ማተቡ አድርጎ በመኖሩ ፤ በዘር ማንነቱ ላይ የተከፈተበትን የማያባራ ጦርነት ለመመከት በማንነቱ ዙሪያ ተደራጅቶ ከመታገል ይልቅ ፤ የዘር ፖለቲካ ሃገር ያፈርሳል በሚል ሰፊ አተያይ ፥ ካራ ስለው ጉድጓድ ምሰው ደሙን ሲጠጡና ስጋውን ሲበሉት የቆዩትን ሕገ አራዊት የትግሬ ነጻ አውጪ ወንበዴዎችን ከፍ ሲል በንቀት ፤ ዝቅ ሲል በአላዋቂነትና በችጋራምነት እየታዘበ በጊዜ ሂደት ሲጠግቡ ይሰክናሉ በሚል ክፉኛ ተዘናግቶ በመቆየቱ ራሱንና ሃገሩን መከላከል በማይችልበት ደርጃ ተበታትኖ የተናጥል ጥቃቱን ሲያስተናግድ ቆይቷል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about በጎንደር የተጀመረው አመጽ የአማራው ሕዝብ የሕልውና ትግል ነው !!
በጎንደር ሕዝባዊ አመጽ ለመቀስቀሱ መሠረታዊው ምክንያት ወያኔ በሕዝቡ ላይ ለ25 ዓመታት የፈጸመው ግፍ ነው!
ከሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ የትግሬ ወያኔ በጎንደር ዐማራ ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለው በዘር ላይ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ፣ ከባለፉት 40 ዓመታት ጀምሮ ሲያደርገው የነበረው ጭፍጨፋና ዐማራን ከምድረገጽ የማጥፋት ዓላማው ተከታይ እንደሆነ ወያኔ የተጓዘበት ጉዞና የቆመለት ዓላማ በግልጽ ያሳያል። የጭፍጨፋው አጀማመርና ሂደት እንዲህ ነው፥ ከሃያ የሚበልጡ የወያኔ ልዩ ኃይል ፖሊሶች፣ ሐምሌ መጀመሪያ 2008 ዓም ላይ የትግሬው ገዥና የወያኔ ሊቀመንበር በሆነው ዐባይ ወልዱ ልዩ ትዕዛዝ ጎንደር ከተማ ገብተው የተለያዩ የስለላ ሥራዎችን ሢሠሩ እንዲቆዩ ተደረገ። የአፋኝ ቡድኑ አባሎች ወደ ጎንደር ከተማ እንዲገቡ የተደገበት ስበብ፣ የዐሥራ ሁለተኛ ክፍል የዩንቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን ለመቆጣጠር በሚል ምክንያት እንደሆነና እነርሱም ከሕዝቡ ጋር ባደሩት ግንኙነት ይኸንኑ የ«በሬ ወለደ» ወሬ ሲያዛምቱ … [Read more...] about በጎንደር ሕዝባዊ አመጽ ለመቀስቀሱ መሠረታዊው ምክንያት ወያኔ በሕዝቡ ላይ ለ25 ዓመታት የፈጸመው ግፍ ነው!
ያዲሳባው ሽምቅ ውጊያ!
እንዴት ናችሁ!? ‹‹በዛሬዋ መሐል አዲስ አበባ መኪና ማቆምያ ማግኘት መኪና ከመግዛት ያልተናነሰ መታደልን ይጠይቃል›› በሚል ጦማሬን ልጀምር አስቤ ተውኩት፡፡ ለምን ተውኩት? ጠዋትና ማታ እንደ ፓስታ በተዝለገለገ የታክሲ ሰልፍ እግሩ ሸምበቆ እያከለ ለመጣ አዲስ አበቤ ዐረፍተ ነገሬ ቁጣን ይቀሰቅሳል ብዬ፡፡ የዛሬ አነሳሴ በአዲስ አበባ እየከፋ ስለመጣው የመኪና ማቆምያ ችግር ለመጻፍ ነበር፡፡ ሁለተኛ አንቀጽ ላይ ስደርስ የግዜርን ቁጣና የአንባቢን ተግሳጽ ፈርቼ ተውኩት፡፡ ነገሩ ለተራበ ሕዝብ ‹‹ኬክ የመጋገሪያ ስልቶች›› የሚል አጭር ስልጠና እንደመስጠት ሆኖብኝ ተውኩት፡፡ .እንዳዲሳባ ሕዝብ አንጀት የሚበላ አለ እንዴ? ከተማ ለመኖር በመፈለጉ ብቻ ፀሐይና ብርድ የሚፈራረቅበት አዲሳቤን የመሰለ ምስኪን ሕዝብ አለ? ካለ ንገሩኝ፡፡ ኡዝቤኪስታንም- ታጃኪስታንም ቢኬድ እንዳዲሳባ … [Read more...] about ያዲሳባው ሽምቅ ውጊያ!
የኢትዮጵያ ጉዳይ መጽሔት
መጽሔቱን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። … [Read more...] about የኢትዮጵያ ጉዳይ መጽሔት
Perspectives on the Trilateral Agreement on the Grand Ethiopian Renaissance Dam:
This commentary is our fourth installment on the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD). It is sparked by the news item which was posted on the pro Tigrean People’s Liberation Front (TPLF) website, on July 9, 2016. Citing Sudan Tribune as its source, Aigaforum indicated what the Egyptian Minister of Water Resources and Irrigation, Mohamed Abdel Ati, is reportedly had said. The statement is related to the arrangement about the legal affairs of GERD. The news item states that “…a U.K. based law … [Read more...] about Perspectives on the Trilateral Agreement on the Grand Ethiopian Renaissance Dam:










