"ለኦሮሞ ህዝብ በሙሉ የተላለፈ የሃዘን ቀን ጥሪ" የሚለውን ጥሪ ካተምን በሁዋላ ይህንን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተብሎ የተላለፈውን መረጃ ስላገኘን ከዚህ በታች ደብዳቤውን አቅርበናል። ስለተፈጠረው ሁሉ ይቅርታ እንጠይቃለን፣ አስተያየት ለሰጣችሁን ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ። (የደብዳቤው ፎቶ ምንጭ ኢሣት) ለኦሮሞ ህዝብ በሙሉ የተላለፈ የሃዘን ቀን ጥሪ (ከበቀለ ገርባና ቂሊንጦ እስርቤት ከሚገኙት ሌሎች የፖለቲካና የህሊና እስረኞች…ነሃሴ፤2008) በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ፣ የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄ አንግበው በሰላም የወጡ በርካታ ዜጎች ከነዚ የህዝብ መብቶች ተቃርኖ በጉልበት እየገዛ ባለው የኢህአዴግ የጭቆና አገዛዝ ስርዓት (tyrannical regime) ተተኪ አልባ ህይወታቸውን አጥተዋል፤ እያጡም ነው። "የዲሞክራሲ ስርዓት ተገንብቷል፣ የዜጎች ህገ-መንግስታዊ መብት ተከብሯል" እያለ … [Read more...] about ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተላለፈ ብሔራዊ የሃዘን ጥሪ
Opinions
“የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት
የመረጃ መረቡ ከሃገር ቤት በሚሰማው የህዝብ እንቢተኝነት አመጽ ተጨናንቆ እኛንም አጨናንቆን ከርሟል። በዚህ የመረጃ ቅብብሎሽ መካከል ወደ ምሥራቅ ሳውዲ ለስራ ጉዳይ አቅንቸ ነበር። ርያድ፤ ደማም፡ ጁቤል፤ ሃፍር አልበጠንን ለአንድ ሳምንት ሳካልል ከሃገር ቤት ከሚሰማው መረጃ እኩል በሳውዲ ዙሪያ ያሉ በርካታ ወገኖቸ የተለያዩ መረጃዎች በስልክ አድርሰውኛል። በተዘዋዎርኩባቸው ከተሞች ያገኘኋቸው ኢትዮጵያውያን ወገኖቸም የሚያመውን የስደት ህመም ሳይደምቁ አጫውተውኛል። ሁሉም አሳሳቢ ናቸው፣ ሁሉም ቢያንስ መፍትሔ ይሻሉና ዝም የማይባለውን የወገንን ድረሱልኝ ጥሪ አሳውቃችኋላሁ! ዛሬም በተለያዩ የሳውዲ ከተሞች የተበተኑ ችግር የገጠማቸው ዜጎች መብት አስከባሪ አጥተው ሲንከራተቱ፣ ሲንገላቱና የድረሱልኝ ጥሪ እያሰሙ ነው! በአንጻሩ አዲስ ኮንትራት ውል ከሳውዲ አረቢያ ጋር ለመስማማት ደጋግሞ … [Read more...] about “የዛፍ ላይ እንቅልፍ!” ስደት
የሰሜን ምዕራብ ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ ነገ…
* ኢህአዴግ የቁልቁለት ጉዞውን ተያይዞታል * ከገዳዮች ቁጥር በላይ ለመሞት የተዘጋጀዉ ህዝብ ይበልጣል እንደ መግቢያ የኢትዮጵያን ነገረ-ፖለቲካ በቅርበት የሚከታተሉ የአገር ውስጥና የምዕራቡ አለም ምሁራን የድህረ-መለስ ኢህአዴግ ፖለቲካዊ ማሻሻያዎችን ያደርጋል ብለው በተስፋ ቢጠብቁም ከታሰበው በተቃራኒ መንገድ ሲጓዝ እየታየ ነው። ተራማጅ የፖለቲካ ሀሳብ ያረጠበት ድርጅት አፈናና ግድያ መገለጫው ሆኗል። የአገዛዙን ምሰሶ ለማጥበቅ ሲባል ህገ-መንግስታዊ ድጋፍ የሌላቸውን የፖለቲካ ሹመቶች በመንግስታዊ መዋቅር ከመሰግሰግ ጀምሮ በፓርቲና በመንግስት መካከል ፍጹም ልዩነት የለሽ አሰራሮችን አጠንክሮ መጓዝን መፍትሄ አድርጎ ይዞታል። በአራት ነጥብ ግትር አቋም የታጠረው ኢህአዴግ፤ የፖለቲካ ተቋማት የፖለቲካ ብዝሃነትን እንዲያስተናግዱ ምቹ መደላድል ከመፍጠር ይልቅ የአንድ ፓርቲ ፍጹም … [Read more...] about የሰሜን ምዕራብ ፖለቲካ እና የኢትዮጵያ ነገ…
ህወሃት በሕዝብ ላይ የደገሰው በዶ/ር ደብረጽዮን አንደበት
ባለፈው ሳምንት ጌታቸው ረዳ ከአልጃዚራ ቴሌቭዥን ጋዜጠኛ ጋር ተጋፍጦ ነበር። አንድ ጥያቄ ቀረበለት። "በራሳችሁ የምትተማማኑ ከሆነ ለምን የተባበሩት መንግስታት ታዛቢዎች እንዳይገቡ ከለከላችሁ?" ሚኒስትር ጌታቸውም። "የተባበሩት መንግስታት አያስፈልገንም። እኛው ራሳችን ከህዝቡ ጋር እንነጋገራለን።" ሲል ነበር የድፍረት መልስ የሰጠው። ይህ የትእቢት መልስ ለጋዜጠኛዋ እንግዳ አይሆንም፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ግልጽ ነበር። እነሆ ከህዝብ ጋር ንግግር መጀመራቸውን እያሳዩን ነው። እንደ ፋሺሽት ጣልያን በከባድ መሳርያ ሕዝብን ለመደብደብ ቆርጠው መነሳታቸውን ተመልከቱ። በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማእረግ ሃገሪቱን የጠቆጣጠሩት ዶ/ር ደብረጽዮን በዛሬው እለት በፌስቡክ ገጻቸው ላይ አንድ የጦር አዋጅ አስነብበውናል። በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የታወጀ ጦርነት። የጦርነት መግለጫው … [Read more...] about ህወሃት በሕዝብ ላይ የደገሰው በዶ/ር ደብረጽዮን አንደበት
The TPLF on retreat
* (Woyane - the cornered Beast.) This time it looks like we have found the formula to start building a harmonious Ethiopia. The Tigrai Woyane Liberation Front that refused to grow up is on retreat mode. The Forces arrayed against the gangster organization are now speaking in one voice. Will TPLF elite wave the white flag without further bloodshed is in everyone's mind. The question is not easy to answer. From experience, the most corrupt and ethnic based regimes come out bloodied if lucky; but … [Read more...] about The TPLF on retreat
ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!
* ከዚህ በፊት ቀድመው ፈራርሰዋል፤ ወደፊትም ይፈራርሳሉ። ይህንን የፕሮፌስር መስፍን ወልደማርያም ጽሁፍ October 22, 2012 አትመነው ነበር። ሆኖም አገራችን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ አግባብነት ያለው ሆኖ ስላገኘነው እንደገና አትመነዋል፡፡ ይቺ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ስንት የመከራ ወንዞችን ተሻግራለች! ገና ስንት ትሻገራለች! ስንት የግፍ ተራራዎችን አቋርጣለች! ገና ስንት ታቋርጣለች! ስንት የበደል ሰይፎችንና ጦሮችን አምክናለች! ገና ስንት ታመክናለች! ስንት የውጭ ኃይሎችን አሳፍራለች! ገና ስንቱን ታሳፍራለች! ስንት አምባገ- ነኖችን እያለቀሰች ቀብራለች! ገና ስንቱን ትቀብራለች! ጭቆና ከኢትዮጵያውያን ደም ሙልጭ ብሎ ወጥቶ በነፃነት፣ በእኩልነት፣ በዳኝነት በጠራ ደም እስቲተካ ድረስ “ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ” ትጸልያለች! እግዚአብሔርም ቃል … [Read more...] about ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!
በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በትግሬ-ወያኔ ግፍ የተጨፈጨፉትን እንድናውቃቸውና እንድንዘክራቸው!
ዘረኛው የትግሬ ወያኔ የወልቃይት ጠገዴን የማንነት ጥያቄ ደግፈው በወጡ የባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በግፍ የገደላቸው ወገኖቻችን ዝርዝር በከፊል። «የወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ፣ የእኛም የዐማራነት ጥያቄ ነው፣» ብለው እሑድ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓም ላይ በባሕርዳር ከተማ፣ በሰላማዊ መንገድ ድምፃቸውን ለማሰማት በወጡ ዐማሮች ላይ፣ የትግሬ ወያኔ ዘረኛ ቡድን በርካታ፣ ሩቅ አሳቢ፣ ለሥራ የጓጉ፣ ላገርና ለወገን ታላቅ ተስፋ ሰንቅው የነበሩ የአያሌ ወጣቶችን ሕይዎት በግፍ ነጥቋል። በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወያኔ ከገደላቸው በርካታ ቁጥር ያላቸው ወጣቶች መካከል ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት በውስጥ የመረጃ ምንጮቻችን የከፊሎቹን አገኝቷል። ከሰንጠረዡ ለመረዳት እንደሚቻለው፣ በግፍ ከተገደሉትና ዝርዝራቸውን ማወቅ ከተቻለው አርባ ዘጠኝ(49) ሰዎች ውስጥ፣ ዕድሜአቸው ሰላሳና ከዚያም … [Read more...] about በባሕርዳሩ ሰላማዊ ሰልፍ በትግሬ-ወያኔ ግፍ የተጨፈጨፉትን እንድናውቃቸውና እንድንዘክራቸው!
በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ
በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር የአቋም መግለጫ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን። በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ዙሪያ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት መነሻ በማድረግ ያወጣውን መግለጫ በመደገፍ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር የተሰባሰብን ተወካዮች ባካሄድነው አስቸኳይ ጉባኤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በሰፊው ተመልክተን የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተናል። ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ምዕ. ፪ ከቁ. ፲፰ ጀምሮ “ልጆቼ ሆይ ይህቺ የመጨረሻዋ ሰዓት ናት እኛም የመጨረሻዋ ሰዓት እንደሆነች አውቀን በአንድነት እንቁም” ብሎ ባስተማረን መንፈሳዊ መሪ ቃል መሠረት … [Read more...] about በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ
ለመሆኑ አማራ ማነው?
ዛሬ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ መንግሥት ዐማራ በተባለው ኅብረተ-ሰብ ላይ ብዙ ግፍና ዐመፅ እንደፈጸመና እንዳስፈጸመ በገፍ ይነገራል። በኅብረተሰቡ ላይ ተፈጸሙ ከተባሉት ድርጊቶች አብዛኞቹ በሥዕል የተቀረጹ፣ ለሰው መብት በቆሙ ባስተማማኝ ብሔራዊና ዓለም-ዐቀፍ ድርጅቶች ከነማስረጃቸው የተጠናቀሩ፣ እሙን በሆኑ ያይን ምስክሮች የተደገፉ ስለሆኑ ማስተባበሉ ከመደናቈርና የአተካራ ግብግብ ከመግጠም ውጭ ሌላ ፋይዳ ያለው አይመስለኝም። የግፎቹ ኢሰብኣዊነትና የፈጻሚዎቻቸውም አውሬነት ለሚሰማ ሁሉ ከመዘግነን አልፎ፣ ሰው ሁኖ መፈጠሩን ራሱን የሚያስጠላ ከመሆኑ የተነሣ፣ ልቦና ያለው ተመልካችም ሆነ ሰሚ፣ መንግሥት ነን ባዮቹ የወያኔ ገዢዎች በጀርመንና በኢጣሊያን ምድር ከታዩት ከናዚና ከፋሽስት መንግሥታት መሪዎች በምን ይለያሉ ብሎ ለመጠየቅ ይገደዳል። በበኩሌ ጥላቻው ከየት መጣ ብዬ አውጥቼ … [Read more...] about ለመሆኑ አማራ ማነው?
የአማራውን ሕዝብ ሁለገብ የሕልውና ትግል ለማገዝ መደራጀት ያስፈልጋል!
ከኃይለገብርኤል አያሌው የቀድሞው የመዐሕድ አመራር አባል ለአመታት በሕዝባችን ላይ ተከማችቶ የቆየው የጭቆና አገዛዝ የፈጠረው ምሬትና ቁጣ በመላው ሃገሪቱ መፈንዳት ጀምሮል። በተለይም በኦሮምያ ባለፉት ተከታታይ ወራት የቀጠለው ሰላማዊ ተቃውሞ የአያሌ ወገኖቻችንን ህይወት እየቀጠፈ ቀጥሏል። ይህም ትግል የኦሮሞ ህዝብ ትግል ተብሎ በሃገር ወስጥና በውጭ ሚድያዎች እውቅና አግኝቷል። በተለያዩ ልዩነቶች ተብታትኖ የኖረውን የኦሮሞ ፖለቲካ ሃይሎችና ሊህቃንን አቀናጅቶ ሃገር ውስጥ ያለውን ትግል ማዕክል ያደረገ እንቅስቃሴ ሲደረግ ይታያል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የአማራውን ሕዝብ ሁለገብ የሕልውና ትግል ለማገዝ መደራጀት ያስፈልጋል!










