• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተላለፈ ብሔራዊ የሃዘን ጥሪ

August 25, 2016 05:47 am by Editor 5 Comments

“ለኦሮሞ ህዝብ በሙሉ የተላለፈ የሃዘን ቀን ጥሪ” የሚለውን ጥሪ ካተምን በሁዋላ ይህንን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተብሎ የተላለፈውን መረጃ ስላገኘን ከዚህ በታች ደብዳቤውን አቅርበናል። ስለተፈጠረው ሁሉ ይቅርታ እንጠይቃለን፣ አስተያየት ለሰጣችሁን ሁሉ ምስጋናችን ይድረሳችሁ። (የደብዳቤው ፎቶ ምንጭ ኢሣት)

kilinto letterkilinto letter 2

ለኦሮሞ ህዝብ በሙሉ የተላለፈ የሃዘን ቀን ጥሪ

(ከበቀለ ገርባና ቂሊንጦ እስርቤት ከሚገኙት ሌሎች የፖለቲካና የህሊና እስረኞች…ነሃሴ፤2008)

በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ፣ የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄ አንግበው በሰላም የወጡ በርካታ ዜጎች ከነዚ የህዝብ መብቶች ተቃርኖ በጉልበት እየገዛ ባለው የኢህአዴግ የጭቆና አገዛዝ ስርዓት (tyrannical regime) ተተኪ አልባ ህይወታቸውን አጥተዋል፤ እያጡም ነው። “የዲሞክራሲ ስርዓት ተገንብቷል፣ የዜጎች ህገ-መንግስታዊ መብት ተከብሯል” እያለ የአገዛዝ ስርዓቱ ካለምንም ሃፍረት ሲለፈልፍ በቆየባቸው ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት፣ ዲሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉትን በሙሉ ሲያፍንና ሲገድል ኖሯል።

እንደ አለመታደል ሆኖ ባገራችን የገዳዮች ገድል እንጂ የሟቾች ጀግንነትና ሃቅን መዘከር አልተለመደም። ምንም እንኳን እንዲ ዓይነት ጥቂት ጀግኖች በህዝብ ዘንድ ሃሃቃቸውና ህዝባዊነታቸው ታውቆ የሚዘከሩ ያሉ ቢሆንም፣ ኣብዛኞቹ ግን በስርዓቱ “የአድኖ መብላት” (predatory) የውሸት ገድል ትርክት መርህ መሰረት እንደ ወንጀለኞችና ሃገር አፍራሾች ተደርገው ለስርዓቱ ባደሩ ሚዲያዎች የፕሮፕጋንዳ ሰለባ ሆነዋል።

ከ2006 (እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር) ጀመሮ በኦሮሚያ ከማስተር ፕላኑ ጋር ተያይዞ፣ በአማራ ከወልቃይት ጠገዴ የማንነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ፣ በደቡብ ክልል እራስን በራስ ከማስተዳደር መብት ጥያቄ ጋር ተያይዞ እንዲሁም በጋምቤላ የእኩልነትና የፍትህ ጥያቄ አንግበው የሃገሪቱ ህገ-መንግስታዊ ስርዓት በሚፈቅደው መሰረት በሰላማዊ መንገድ ለተቃውሞ የወጡ በርካታ ዜጎች በመንግስት የታጠቁ ሃይሎች ተገድለዋል። አሁንም እየተገደሉ ነው።

የእንስሳቶችን መብት ጥበቃ እንኳን ለማረጋገጥ አለም ሁሉ በሚረባረብበት በዚህ ወቅት፣ የዜጎቻችንን አንገት በመቁረጥና በሌሎች የጭካኔ መንገዶች በመግደል፣ የውሸት ፕሮፓጋንዳ ሰለባ ማድረግ እጅግ አሳፋሪና አስነዋሪ ተግባር ነው። በታሪክም የማይረሳ ብቻም ሳይሆን ይቅር ሊባል የማይችል የአረመኔዎች ተግባር ነው።

አገዛዙ በዚሁ ዓይነት የጭካኔ መንገድ በተገደሉት ሰማዓቶቻችን ላይ በውሸት የቴሌቪዥን ዶክሜንታሪና በካድሬዎቹ በኩል በሚጠናቀሩ ዜናዎች ከማውገዝና እነዚ ንጹህ ሰማዕታት የከፈሉት መስዋዕትነትን በፕሮፓጋንዳ ጥላሸት ከመቀባት አልፈው፣ ለነዚሁ በግፍ ለተገደሉ ዜጎች ሃዘናቸውን ለመግለጽ እዚህ እስር ቤት ውስጥ ጥቁር ልብስ በለበስነው የግፍ ታሳሪዎች ላይ ከፍተኛ ድብደባና የማሰቃየት (torture) እያደረሱ ነው። በእስር ቤቱ ሃላፊዎች ትዕዛዝ ልብሶቻችን ሁሉ ተቀምተው ተወስደዋል። በተጨማሪም ለነዚሁ በግፍ ለተገደሉ ዜጎች ሃዘናቸውን ለመግለጽ ጸጉራቸውን በተላጩት እስረኞች ላይ ከፍተኛ ድብደባና አሰቃቂ የማሰቃየት ተግባር (severe torture) ደርሶባቸዋል። በቀጠሮአቸው ቀንም ፍርድ ቤት እንዳይቀርቡ ተደርገዋል።

እኛ አሁን በዚህ ዓይነት ሁናቴ ውስጥም እንኳን ሆነን እነዚህ የዲሞክራሲና የፍትህ እንዲሁም የእኩልነት ጥያቄን በሰላማዊ መንገድ አንግበው ለተሰውት ዜጎቻችን ያለንን ልባዊ ክብርና ህያውነታቸውን ለመግለጽ፣ እነሱ የተሰውለትን ዓላማ ለማሳካት ያለንን ቁርጠኝነት ለማሳየት እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው አጋርነታችንን ለመግለጽ ለሶስት ቀናት የሚዘልቅ ብሄራዊ የሃዘን መርሃግብር (ከነሐሴ 18-21፣ 2008) ሁላችንም ባንድነት እንድናደርግ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ስለሆነም በነዚህ ሶስት የብሄራዊ ሃዘን ቀናት፣ ሁሉም ዲሞክራሲና ፍትህ እንዲሰፍን የምትመኙና ለዚህ ዓይነቱ ትግልም አጋርነትን ማሳየት የምትሹ ዜጎች፥

1) ጥቁር ልብስ በመልበስ፣ በትግሉ የተሰውትን ሰማዕታት ምስሎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመለጠፍና በሰፊው እንዲሰራጩ በማድረግ፣ በታክሲዎች፣ በበጃጆችና በሌሎች የህዝብና የግል ትራንስፖርት መኪናዎች ላይ ጥቁር ጨርቅ በማንጠልጠል፤
2) በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሃገር ያላቹ ዜጎች የሰማዕታቱን ስሞች በማጠናቀር የጋራ ጸሎት ወይም ህዝባዊ ውይይት ፕሮግራም ማድረግ፤ በተለይም ደግሞ ሃገር ውስጥ ያላቹ ወደ ሰማዕታቱ ቤተሰቦች ዘንድ በመሄድና በማጽናናት አብሮነታቹንና አጋርነታቹን ማሳየት፤
3) የሰማዕታቱን ሙሉ መረጃ፣ ከተቻለም ፎቶግራፎቻቸውን ጨምሮ ገደይና አስገዳዮቻቸውን ለፍርድ ለማቅረብ መረጃ እያጠናቀሩና ባለማቀፍ ደረጃ እየሰሩ ላሉት አካላት መረጃዎችን በተቀናጀ መልኩ በመላክ (ለዝርዝሩ ይሄንን ገጽ ይጎብኙ . . . ኮንታክት ያድርጉን https://daandii.com/)፤
4) እያደርግን ያለውን የዴሞክራሲና የፍትህ እንዲሁም የእኩልነት ትግል ለማስቀጠል ባለን ቁርጠኝነት ላይ ቃል በመግባትና ያንኑ የሚያሳዩ መልዕክቶችን፣ የአርት ወይም የሙዚቃ ስራዎችን በማሳየት … በማህበራዊ ሚዲያዎች በማሰራጨት፤
5) እንዲሁም ይሄን ማድረግ የምንችል ደግሞ ጸጉራችንን በቡድን በመላጨት ለንጹሃን የተሰው ሰማዕቶቻችንን እንድናስባቸው በነዚሁ ለነጻነት፣ ለእኩልነት፣ ለዲሞክራሲና ለፍትህ በተሰዉት ሰማዕታት ስም ጥሪ ልናደርግላችሁ እንወዳለን።

ህዝባዊና ሰላማዊ ታጋዮቻችን የተሰውለት ቅዱስ ዓላማ በህዝብ የተባበረ ትግል ግቡን ይመታል!!

እናመሰግናለን

(ምንጭ:#oromoprotests)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Yinegal Belachew says

    August 26, 2016 07:03 am at 7:03 am

    ebakachihu yihen hizbin begosana bezer mekefafel tewut. ye’ethiopia hizb min bedelachihu endewoyane yemtkefaflut? hizbu aand nen eyale poletikegnoch beyegosa qirchat wust eyeketetu ye’oromo hazen yamara hazen yilutal. yihe akahed yibkan, ej ej blonal. bzuw hizbum teltotal. begzer yihunbachihu astesasebachin ke’afnchachin tinish kef yibelna wodeginbarachin enkuan yidres. woy meregem. woyane tkur wusha yiwuled!

    Reply
    • አሰፋ says

      August 26, 2016 10:50 am at 10:50 am

      መልዕክቱ ቆነጆ ነው። መልዕክቱ የሚገለጥባቸው መንገዶችና ዘዴዎችም ግሩመ ናቸው።
      የበደል ሰለባዎቹም ዝርዝር ከሞላ ጎደል ሁሉንም ያካተተ ነው። ጎሽ!
      “ለኦሮሞ ሕዝብ በሙሉ የተላለፈ የሃዘን ቀን ጥሪ” የሚለው
      ለመልዕክቱ በርዕስነት እንዴት ተመረጠ? ጥያቄዬ ነው።
      በተረፈ በአረመኔው የወያኔ እስር ቤትም ሆናችሁ መከራና ስቃይ እየተቀበላችሁም እንኳን
      ለወገኖቻችሁ የምታሳዩት ጭንቀትና ጥበት፤ ለነጻነት ታጋዮች ጥንካሬ አጎናጻፊ ነው።

      ለመለወጥ የማትችሉትን ለመቀበል መረጋጋቱን አይንፈጋችሁ።

      Reply
      • Editor says

        August 27, 2016 01:09 am at 1:09 am

        አሰፋ

        ስለ አስተያየቱ እናመሰግናለን – ከይቅርታ ጋር አስተካክለናል!

        አርታኢ

        Reply
    • Editor says

      August 27, 2016 12:50 am at 12:50 am

      Yinegal Belachew

      ስለ አስተያየቱ እናመሰግናለን – ከይቅርታ ጋር አስተካክለናል!

      አርታኢ

      Reply
  2. Aman says

    August 26, 2016 04:35 pm at 4:35 pm

    ኢሳት ከሚነዛው የዘር ፖለቲካና እናንተ ከምታራግቡት ፕሮፐጋንዳ፡ ወያነን እናባርራለን ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ፡ ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁነታ ወደ ህውላ ቀርታቹሃል።
    የትግራይን ህዝብ በመስደብና በማግለል፡ ወያነ ከፈጸሙት የዘር ፖለቲካ የባሰ ስህተት እየፈጸማችሁ ነው። የትም ኣያደርስም። ጭንቅላታችሁ ማሳደስ ኣለባችሁ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule