• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ

August 19, 2016 09:15 am by Editor 1 Comment

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ

የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር

የአቋም መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን።

በስደት ላይ ያለው ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ በቅርቡ በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ዙሪያ የተቀጣጠለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት መነሻ በማድረግ ያወጣውን መግለጫ በመደገፍ በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማህበር የተሰባሰብን ተወካዮች ባካሄድነው አስቸኳይ ጉባኤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በሰፊው ተመልክተን የጋራ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ምዕ. ፪ ከቁ. ፲፰ ጀምሮ “ልጆቼ ሆይ ይህቺ የመጨረሻዋ ሰዓት ናት እኛም የመጨረሻዋ ሰዓት እንደሆነች አውቀን በአንድነት እንቁም” ብሎ ባስተማረን መንፈሳዊ መሪ ቃል መሠረት የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖ እንዳሻው እየዘረፍ እና እየገደለ ያለው በደም የተጨማለቀውን ወያኔን በአንድነት ሆነን በቃ ልንለው ይገባል።

የእናት ሀገሩ ፍቅር እንደ እግር እሳት የሚያቃጥለው ወጣት ትውልድ እምቢ ለሀገሬ! እምቢ ለነፃነቴ! ብሎ ግንፍሎ ወጥቷል። በአንፃሩ ሥልጣን ያሰከረውና ገንዘብ ያሳበደው ወያኔ ያገኘውን ሁሉ መግደልና መጨፍጨፉን ቀጥሏል። ሁሉም እንደሚያውቀው ሀገራችን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት የተጣሰባት፣ የዲሞክራሲ ጭላንጭል የጠፋባት፣ የዘር መድልኦ አገዛዝ የሰፈነባት የአምባ ገነኖች መፈንጫ ሆናለች። የወያኔ የግፍ አገዛዝ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለድህነት ለርሃብ ለዕርዛት ለስደትና ለመሐይምነት ዳርጎታል።

ውድ ኢትዮጵያዊ ወገን!

“ድር ቢያብር አንበሳ ያስር” እንደሚባለው የኢትዮጵያ ውድ ልጆች በየቀኑ በወያኔ ጥይት መቀላት ብቻ ሳይሆን በወያኔ ቆመጥ ተደብድበው እየተገደሉ ደማቸው እንደ ጅረት ውሃ እየፈሰሰ ከሞት የተረፉትም ለቀጣይ ግድያ እንዲጠባበቁ በጅምላ እየታሰሩ ናቸው። የዘረኛው ወያኔ የግፍ አገዛዝ ፅዋው ሞልቶ ከፈሰሰ ቆዬ። በመሆኑም እኛ በሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ-ቤተክርስቲያን መዋቅር በሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሥር የተሰባሰብነው የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት አንድነት ማኅበር አባላት ይህን የአቋም መግለጫ በጋራ አውጥተናል።

፩ኛ/ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሕ.ወ.ሓ.ት የባርነት ቀንበር ተላቆ የሰላምና የነፃነት አየር እንዲተነፍስ ትግሉን በየአቅጣጫው እንዲያፋፍም ጥሪ እናቀርባለን። እኛም በማንኛውም ረገድ አስተዋጸኦ ለማበርከት ቃል እንገባለን።

፪ኛ/ አረመኔውንና ዘረኛውን የወያኔ ቡድን ለማንበርከክ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በተደራጀና በተቃናጀ መልኩ በየቦታው ዘብ ይቁም።

፫ኛ/ የሀገር አለኝታ የወገን መከታ የሆነው ወጣቱ ትውልድ እንደ ጽጌረዳ አበባ በየቦታው እየረገፈ ነው። እናት ልጇን ተነጥቃ ግንባሩ በአጋዚ ጥይት ተበርቅሶ ሲወድቅ እያየች የወላድ አንጀቷ አልችል ብሏት የሀገር ያለህ፤ የወገን ያለህ፤ ድረሱልኝ እያለች ትጮሃለች። ከዚህ የበለጠ ምድራዊ ገሀነም ምን ሊኖር ይችላል? በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሰን ይህንን ዘረኛና ገዳይ ቡድን ልናስወግደው ይገባል በማለት ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

፬ኛ/ ሀገር በቀል የሆነው ከሀዲ ወራሪ ኃይል ቀደም ብሎ በነደፈው የከፋፍለህ ግዛ ያረጀና ያፈጀ ሥልት ሊሠራለት አልቻለም። ሕዝቡም ነቅቶበታል። አንድ ለአምስት በሚል አደረጃጀት ያዋቅረውን የሰሜን ኮሪያ ኮምኒስታዊ የአፈና አገዛዝ ሰንሰለት  ኢትዮጵያዊ ወገናችን በጣጥሶ ጥሎት በአንድነት ፀንቶ ቆሟል። ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ እስከሚሆን ድረስ የነፃነት ትግሉ ይቀጥላል። እኛም ድጋፋችንን እንቀጥላለን።

፭ኛ/ ወቅቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች የፍልሰታ ፆምን ምክንያት በማድረግ በየቤተክርስቲያኑ በጸሎትና በሱባኤ ላይ ናቸው። በስቃይና በመከራ ላይ ያሉትን ወገኖቻቸውንም ዕለት በዕለት በጸሎት ያስባሉ።በአንፃሩ ግን ወያኔ በሃይማኖትና በእምነት ውስጥ ገብቶ ታጋይ ካድሬዎቹን በካሕናት ስም እያሰማራ ቤተክርስቲያናችንን እያመሰ ይገኛል። እውነተኛ የሃይማኖት አባቶች የሆናችሁ የወያኔን አፀያፊና ዘግናኝ ድርጊት ልታወግዙ ይገባል። በኢትዮጵያም ሆነ በየትኛውም የዓለም ክፍል የምትገኙ አባቶች ሕዝባዊ ወገናዊነታችሁን የምትገልጹበት ጊዜ አሁን ነው እንላለን።

እግዚአብሔ አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቅ ሕዝቧንም ይባርክ። አሜን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Abebe says

    August 22, 2016 02:52 pm at 2:52 pm

    አባቶች ካስተማሩኝ እንጅ መፅሀፍ ቅዱሳዊ እውቀት የለኝም። መቼም “ህገ-ወጦቹ አባቶች ስላስተማሩህ ነው፤ ህጋዊዎቹ አባቶች እኛ ነን” እንደማትሉኝ ተስፋ አደርጋለሁ። ለመሆኑ የሀይማኖት አባቶች መንግስትን ለመጣል የአቋም መግለጫ እንዲያወጡ ኢየሱስ ክርስቶስ አስምሯቸዋልን? የቀደሙት አባቶቻችንስ በፅናት አንገታቸውን ለሰይፍ ሰጡ እንጂ እነሱ ሸሽተው ልጆቻቸውን ሙቱ ብለው ነበርን? እናንተ ታዲያ…

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule