የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]፤ 2009ዓ.ም፤ አ/አ፤ አታሚ አልተገለጸም፤ 10ዶላር፣ 100 ገጽ የማለዳ ድባብ፣ ለ በዕውቀቱ ሥዩም አራተኛ የግጥም ሥራው ነው። መጽሐፉ ሦስት ክፍሎች አሉት፤ “ግጥምና የዘመን መንፈስ” [ገጽ 5-9]። ግጥሞች [ገጽ 17-91]። “ጉደኛ ስንኞች” እና “ሙሾና ባለቅኔ” [ገጽ 93-100]። መድብሉ፣ ቀድሞ ካስነበባቸው ላይ አዳዲሶች ተጨምረውበት የተዘጋጀ ነው [ገጽ 9]። የትኞቹ አዳዲሶች እንደሆኑ አልተገለጸም። ግጥም ከስድ ንባብ ይልቅ የግል እይታዎችን፣ ማህበራዊ ትረካዎችን ለመቋጠርና ለማስታወስ ይረዳል። ቅኝቱና አወራረዱ ለጆሮና ለዐይን ይጥማል። ግጥም ማህበራዊ እሴት አለው፤ በሥልጣን ለሚባልጉ እርምት ለመስጠት [“ይድረስ ለጥም ሚኒስትር”፣ ቁ.71]፣ የሕይወትን አጭርነት ለማሳሰብ፣ ከሚታየው ውጭ የላቀ ተስፋ እንዳለ ለማወጅ፣ የግለሰብ … [Read more...] about ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]
በዓለም ዙሪያ ለሚኖሩ የዐማራና የቅማንት ነገድ ተወላጆች የቀረበ ጥሪ!
ወደ ነበረው የአባቶቻችን ፍቅርና አብሮነት እንመልከት! የትግሬ-ወያኔ የሚያራምደው ዘርን መሠረት ያደረገ ፖለቲካ፣ የቋንቋ ልዩነት ያላቸውን ሰዎች ብቻ ሳይሆን፣ ከተለያዩ ነገዶች የተወለዱ እህታማቾች፣ ወንድማማቾች እና አንድ አካልና አምሳል የሆኑ ባልና ሚስቶችን እያለያየ እንደሆነ ባለፉት 26 ዓመታት የታዘብነው ጉዳይ ነው። ወያኔ ይህን ቋንቋን መሠረት ያደረገ የማለያየት ሥራ የሚሠራው ደግሞ፣ አንዳንድ የዋሆች እንደሚሉት ለነገዶችና ጎሣዎች ዕኩልነት አስቦ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያን የማፍረሻውና ለዘመናት ሲያልሙት የኖሩትን የትግራይ ረፐብሊክ ለመመሥረት አቋራጩና ቀላሉ መንገድ ይህ ሆኖ ስላገኙት ነው። «አባቶቻችን፣ ሁልህም ወደ ወገነህ ተጠጋ ቢባል፣ ዳዊት ወደ ቁርበት፣ አክንባሎ ወደ በረት ተጠጋ» ያሉት ኅይው ሆኖ፣ የተፋቀው፣ የለሰለሰው፣ በአያሌ ቀለሞች የተዋበው፣ ውብና መንፈሣዊ ሥዕሎች፣ … [Read more...] about በዓለም ዙሪያ ለሚኖሩ የዐማራና የቅማንት ነገድ ተወላጆች የቀረበ ጥሪ!
እምቢተኝነት በተግባር!
“ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”። የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተነተነበት ጽሁፍ ላይ ከተናገረው። ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ። ዛሬ በተከበረው የመስቀል በዓል ላይ የህወሓትን ማስፈራሪያና ዛቻ ከምንም ባለመቁጠር የውቅሮ፣ ዓዲግራት፣ መቀሌ፣ ጎንደር፣ ደሴና ሌሎች አካባቢዎች ህዝብ “ባለኮከቡን ባንዲራ አይወክለኝም” በማለት ኮከብ አልባውን ሠንቀድ ዓላማ ይዞ በመውጣት እምቢተኝነቱን አድፍረት አሳይቷል። ሃይለኪሮስ ታፈረ (Hailekiros Tafere) በፌስቡክ ገጹ የዘገበውን አስመልክቶ አምዶን ገብረሥላሴ ይህንን ብሏል፤ “ፖሊስ "ኮከብ የሌለው ባንዴራ ዳሜራ ሸፍናቹሃል" በሚል ሰበብ ዛሬ መስቀል በዓል እያከበረ የነበረው የውቅሮ … [Read more...] about እምቢተኝነት በተግባር!
የህወሃት አጀንዳ + የዘር ፖለቲካ + የሜንጫ ፖለቲካ – መጨረሻው ተያይዞ …
የኢትዮጵያ ህወሓት ሰራሹ “ፌደራሊዝም” ወደ ተፈራው ቀውስ እየተንደረደረ መሆኑንን የሚያሳዩ የዜና ዘገባዎች የተሰሙት ገና ከጅምሩ ነበር። በርካታ ባለሙያዎችና የተቀናቃኝ ፖለቲካ መሪዎች በተደጋጋሚ ስጋታቸውን ቢገልጹም ተቀባይነት ሊያገኙ ባለመቻላቸው የጎሣና የብሄርተኛነት በሽታ እያደር ኢትዮጵያን እየበላት አሁን ያለችበት ደረጃ አድርሷታል። ችግሩ አለመስማትና አለማወቅ ብቻ ሳይሆን ዓላማ ያለው፣ በቅጥረኝነት አገሪቱን የማፈራረስ ተልዕኮ የማሳካት ጉዳይ በመሆኑ የመከሩ፣ የዘከሩ፣ ያስጠነቀቁ፣ ስጋታቸውን አደባባይ ያወጡ ዜጎች ወንድ ሴት ሳይባል ተፈጅተዋል። አገሪቱ ምትክ የሌላቸውን ልጆቿን እንድትከስር ተደርጋለች። ግድያውና አፈናው ብቻ ሳይሆን መላውን የአገሪቱን ህዝብ እርስ በእርስ ጎሣና ጎጥ ለይቶ እንዲናከስ እየተወተወተና እየተገፋ አገሪቱ ቆዳዋ በልጆቿ ደም እንዲለወስ ሆኗል። ዛሬ … [Read more...] about የህወሃት አጀንዳ + የዘር ፖለቲካ + የሜንጫ ፖለቲካ – መጨረሻው ተያይዞ …
ድንበር: “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል”
ስለኢትዮጵያ ድንበር መፍረስ፤ መገሰስና መጠገን በተደረጉበት ዘመናት ሁሉ የነበረች አሁንም ታፍና በመታዘብ ላይ ያለች፤ ወደፊትም የምትኖር ይህች ጥንታዊት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን፤ አሁን ህዝቧ ስለሚነጋገርበት ስለ ድንበር ምን ትላለች? የሚለውን ለመዳሰስ ይህችን ጦማር ሳዘጋጅ በውስጧ የተሸከመቻቸውን ሀሳቦች በተጻፉባቸው ቋንቋዎች እንዳሉ አቅርቤያቸዋለሁ። ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚሰነዘረውን አፈና ለመከላከል የጠቀስኳቸውን ሀሳቦች በተጻፉባቸው ቋንቋዎች እንዳሉ በማቅረቤ (ግእዙን ግን ትርጉሜዋለሁ) ይቅርታ በመጠየቅ ያጎደልኩትን እየሞላችሁ፤ የተሳሳትኩትን እያረማችሁ ታነቧት ዘንድ በታላቅ ትህትና አቀረብኩላችሁ። መግቢያ “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል” በሚል ርእስ ይህች ጦማር የፈለቀችበት ዘመን፤ ኢትዮጵያን ከጎረቤት አገር የሚያዋስኗት ድንበሮችና፤ በውስጥም ዜጎቿ … [Read more...] about ድንበር: “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል”
‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ
"አከ’ሲ" አለ ያገሬ ሰው፣ ከሰሞኑ ‘አጃኢብ’ ያሰኘውን የአዜብ መስፍን ወሬ ሲሰማ። አዜብ ልምድ ያላት ውሸታም እንጂ ልምድ ያላት ኮሜዲያን አትመስልም ነበር። ከሚሚ ስብሃቱ ጋር በያዝነው ሳምንት የተወኑት ድራማ ግን ጦሽ አርጎ ያስቃል። መቼም ጥርስ እንጂ ልብ አይስቅ። ፈንድሻም'ኮ ልቧ እየተቃጠለ ነው ፊትዋ ሚፈካው። ሴትየዋ አይኗን ሳይሆን ቅንድቧን በጨው አጥባ "ምንም የለኝም ግን ይወረስ" ነው የምትለው። መለስ የባንክ ደብተር ይቅርና መንጃ ፈቃድ እንኳ የለውም ስትል የቀለደችበት ወቅት ሩቅ አይደለም። እርግጥ ነው አዜብ በራስዋ ስም እንኳን ሕንጻ፣ ሲም ካርድም ሊኖራት አይችልም። ጥሩ ጋዜጠኛ አልገጠማትም እንጂ፣ ቢገጥማት፣ "እመኑኝ ልጃገረድ ነኝ!" ብላ እያለቀሰችም ቢሆን ለማሳመን ትሞክር ነበር። ልጆቼን እየተበደርኩ ነው የማስተምረው ብላ በተናገረች ሰሞን ኤ.ቢ.ሲ … [Read more...] about ‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ
ሞት የሰጠን ደስታ
የታጨደው ሳር ድርቆሽ ነው የከብቶች መኖ በመሆን በበሬ ጫንቃ ድካም ጠግቦ አደር ያደረገን፤ የሞተው የግጦሽ ሳር ነው ጮሌ ፈረስ አሳድጎ በጦር ሜዳ የድል ብሥራት ያቀዳጀን ጀግና ተዋጊ አድርጎ፤ የበሬውን ቆዳ ከበሮ የበሬውን አንጀት ጅማት የፈረሱን ሞት በደል የሸንበቆውን ያካል ስብራት፤ የእንስሳቱን ሞት ከእሳሩ ሞት ጋር ስናዋድደው ከሞት ምንጭ ነው ለካስ የደስታ ጅረት የሚወርደው። የሞተ … [Read more...] about ሞት የሰጠን ደስታ
ሹፌሮችን ያስቆጣ መመሪያ ተሻሻለ ተባለ
የአማራ ክልል መንግስት የመንግስት ተሸከርካሪ አያያዝ፣ አጠቃቀምና የንብረት አስተዳደር መመሪያ ሰሞኑን ማሻሻሉን ይፋ ቢያደርግም የከፍተኛ አመራሮች ሹፌሮች በበኩላቸው የተሻሻለው መመሪያ የኛን ሕልውና የሚፈታተን ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ገለጡ። የክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ሰሞኑን ለክልሉ ቢሮዎች በላከው ደብዳቤ ከመስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ወይም የሥራ ኃላፊዎች ለሥራ ጉዳይ ክልሉን ለቀው ወደ አዲስ አበባ ሲሄዱ የሚመሩትን ተቋም ተሸከርካሪ ይዘው እንዳሄዱ እያሳሰበ በተማከለ መንገድ በከተማው በሚዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ አብራርቷል። በተማከለ መንገድ በሚዘጋጁ ተሸከርካሪዎች መጠቀም የሚችሉ የሥራ ኃላፊዎች ብሎ የተሻሻለው መመሪያ የጠቀሳቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር፣ ም/ርዕሰ መስተዳድርና በዚህ ደረጃ ያሉ ኃላፊዎች፣ የክልሉ … [Read more...] about ሹፌሮችን ያስቆጣ መመሪያ ተሻሻለ ተባለ
“ETHIOPIA DOESN’T NEED ANY MORE TALKING”
“Doing the same things and expecting different results is INSANITY” For the better part of 25 years we Ethiopians have watched as the TPLF has mutilated, killed, tortured, and destroyed our citizens and systematically torn apart our country. They have one sole mission, which is to completely and utterly destroy the country while propping up and developing Tigray. The evidence is quite clear for those who follow the goings on in the country that there is a clear systematic dismantling of … [Read more...] about “ETHIOPIA DOESN’T NEED ANY MORE TALKING”
Cultural competence is a game changer for Ethiopians in the Diaspora
If you’re an Ethiopian, live, work, and do business in another culture, cultural intelligence is one of the key soft skills that you need to develop. With the opportunity to meet, interact, and work with diverse people comes the challenge to get along and succeed in what you do. This challenge is understandable. You may have extraordinary social intelligence when it comes to interacting and working with people who are within your native Ethiopian culture. You know the customs, beliefs, and … [Read more...] about Cultural competence is a game changer for Ethiopians in the Diaspora

![ሐተታና ግምገማ፤ የማለዳ ድባብ [የአዳዲስ ግጥሞች መድብል]](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/10/dibab-191x300.png)








