• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሞት የሰጠን ደስታ

September 22, 2017 02:02 am by Editor Leave a Comment

                         የታጨደው ሳር ድርቆሽ ነው የከብቶች መኖ በመሆን

                             በበሬ ጫንቃ ድካም ጠግቦ አደር ያደረገን፤

                             የሞተው የግጦሽ ሳር ነው ጮሌ ፈረስ አሳድጎ

                     በጦር ሜዳ የድል ብሥራት ያቀዳጀን ጀግና ተዋጊ አድርጎ፤

                             የበሬውን ቆዳ ከበሮ የበሬውን አንጀት ጅማት

                             የፈረሱን ሞት በደል የሸንበቆውን ያካል ስብራት፤

                             የእንስሳቱን ሞት ከእሳሩ ሞት ጋር ስናዋድደው

                       ከሞት ምንጭ ነው ለካስ የደስታ ጅረት የሚወርደው።

                             የሞተ በሬ አንጀት ነው፤የክራር ጅማት ሆኖ

                             ያሳለፍነውን ህይዎት ወደ ፊት አጠንጥኖ

                             መልሶ የሚያኖረን ያለፈውን ጊዜ ትዝታ

                             ሳናውቀው ለካስ ሞት ነው፤የሚለግሰን ደስታ።

 

                            የሞተ በሬ አንጀት ነው፤የክራር ጅማት ሆኖ

                            ልባችንን የሚያሸፍተው በቸበለው ቅኝት ፋኖ።

  

                            የሞተ በሬ ቆዳ ነው፤ከበሮ ሆኖ ተወጥሮ

                            ሲነረት ሲደበደብ ልዩ ቃና ድምጽ ፈጥሮ 

                            ባጀቡት ዜማዎች ግነት ቅላጼውን አጉልቶ

                            መድረኩን ሲነቀንቀው ንዝረቱ ስሜት ነክቶ፤

                            የተሰበረው ሸንበቆ ነው፤አካሉ ተበሳስቶ

                       በጣት ላይ ትንፋሽ ጨምሮ፤የዋሽንት ድምጽ አፍልቆ

                            አእምሮን የሚያብከነክን የሰውን ቀልብ ሰርቆ

                           የሞተ ፈረስ ጭራ ነው፤የአዝማሪ ጥበብ ማሲንቆ

                               ደስታ የሚዘራብን ስሜታችንን ሰርቆ።

 

                           ከተገደለ እሳር፣ከተገደለ በሬ፣ ከተሰበረ ሸንበቆ

                     ከሞተ በሬ አንጀት፣ከሞተ ፈረስ ጭራ መረዋ ድምጽ ፈንጥቆ

                           ከሞተው ክርስቶስ ህይዎት፣የምህረት ፀበል ፈልቆ

                           የአዳምን ልጆች ሁሉ በደሙ ዋጅቶ ያፀዳው

                           ከሞት ምንጭ ነው ለካስ፣የሰው ደስታ የሚቀዳው።

                                               መስከረም 2010

                             *መታሰቢያነቷ የሥነ ሃሳቡ ምንጭ ለሆነው ከያኒ እሱባለው ይታየው

                              አብርሃም በየነ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule