የምናውቀውን እንናገራለን ያየነውን እንመሰክራለን(ዮሐ 3፡11) ዓለም እንደሚያውቀው የጣሊያን ጦር በአድዋ ጦርነት እጅግ በሚያሳፍር ቅጣት ተቀጥቶ ከኢትዮጵያ ምድር መውጣት ለመላ አውሮጳ የሐፍረት ማቅ መከናነብ ምክንያት ሆነው። በዚህ ታሪካዊ ውርደት የተሸማቀቀው ጣሊያን፤ ዘመናዊ የምድርና የሰማይ ጦሩን ከበፊቱ በላቀ ሁኔታ አደራጅቶ፣ኢትዮጵያን በጎሳ ሸንሽኖ በቋንቋ ለያይቶ እርስ በርሱ የማዋጋት ስልቱን ቀምሮ፣ አማራና ተዋህዶ ቤተክርስትያንን የማጥፋት እቅዱን ዘርግቶ እንደገና በ1928 ዓ.ም. ወረረን። የመጀመሪያውን የክተት ጥሪ የሰሙ ኢትዮጵያውያን የየራሳቸውን መሳሪያ እየገዙና ሥንቃቸውን እያዘጋጁ ከሸዋ፣ ከወሎ፣ ከምስራቅ፣ ከምዕራብ፣ ከመካከለኛውና ደቡቡ ክፍል ወረራውን ለመመከት በማይጨው በኩል ዘመቱ። በተከዜ በኩል ከጎጃም ከቤገምድርና ስሜን ጣልያን መሰረቱን ወደ ጣለበት ወደ … [Read more...] about አጽማቸው የፈለሰው የመላከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ የአምስቱ ዘመን ተጋድሎ
የቅማንት ጉዳይ!
ብዙ ወዳጆቼ ስለምንድን ነው የቅማንትን ጉዳይ ዝም ያልከው እያሉ በየቀኑ መልዕክት ይልኩልኛል፡፡ ላም እሳት ወለደች እንዳትልሰው ፈጃት እንዳትተወው ቆጫት ይላሉ አበው ሲተርቱ፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ አንድ ጽንፍ ይዞ መሔዱን አማራጭ አድርጌ አላየሁትም፡፡ መሀል ሰፋሪ ለመሆንም አይደለም፡፡ ግና ዕውነታውን ይዘን ለሁሉም የሚበጀውን መከተል አስፈላጊ ነው ብዬ ስለማምን ነው፡፡ እነኚህ ወዳጆቼ እንደሚሉት ዝም ብዬም አላውቅም፡፡ ነገርን ከሥሩ ውኃንም ከጥሩ እንደሚሉ ከሥር መሠረቱ ጉዳዪን መዘርዘር አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ የቅማንትን ጉዳይ መከታተል የጀመርኩት በ2003/4 ዓም ጀምሮ ነበር፡፡ ይህም የተፈጠረበትን አጋጣሚ ከዚሁ ላይ መግለጹ አስፈላጊ ይመስለኛል፡፡ አይከል ከተማ እሜቴ አይከል የምትባል ዛፍ አለች፤ የሚገባላት ብጻት ብዛት ይኽ ነው አይባልም፡፡ ምርጥ ምርጡን ገብስማ ዶሮ ከጊወን … [Read more...] about የቅማንት ጉዳይ!
ኢትዮጵያ ያለ”ኢትዮጵያዊነት” ልትኖር አትችልምን?
በአዲስ አበባና ዙሪያዋ በጣም ተወዳጁ ኤፍኤም ሬዲዮ ሸገር ነው ቢባል የሚያጣላን አይመስለኝም። ሸገር መፈክሩ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር” የሚል ነው፡፡ አሁን ደግሞ ፖለቲከኞችም ይህንኑ መፈክር የንግግራቸው ማሳረጊያ ዓረፍተ ነገር እያደረጉት ነው። ሰማያዊ ፓርቲ ከመግለጫዎቹ ግርጌ “ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር” የሚል ዓረፍተ ነገር ያስቀምጣል። አዲሱ በእነሰይፉ ፋንታሁን እና ሠራዊት ፍቅሬ… የተከፈተው ኢትዮ ኤፍኤም ሬዲዮ “ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ” የሚል መፈክር ይዞ መጥቷል። በቅርብ ጌዜ ከተከፈቱት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንዱ – ጄቲቪ – መፈክሩ “ኢትዮጵያዊነት መልካምነት” የሚል ነው። “ኢትዮጵያ” የተሰኘው የቴዲ አፍሮ ዘፈን የአገር ውስጥ ሽያጭ ሪከርድ ሰብሯል። የሐበሻ ቢራ ማስታወቂያ ‘ኢትዮጵያዊነት’ የሚለውን ቃል ማዕከል ያደረገ እና ስለኢትዮጵያ ‘ገናና ታሪክ’ የሚያወሳ … [Read more...] about ኢትዮጵያ ያለ”ኢትዮጵያዊነት” ልትኖር አትችልምን?
ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል
የህወሃት አገዛዝ 2010 ዓ.ም አዲስ ዓመትን ለማክበር የጀመረውን ከባህሪው የወጣ ድርጊት ተመልክተው አንዳንዶች ስርዓቱ እውነተኛ የመንግስትነት ባህርይን እየያዘ ነው ሲሉ ይደመጣል። እነዚህ የዋሆች ሰሞኑን ከነሀሴ 26 ቀን ጀምሮ የፍቅር ቀን፣ የእናቶችና ህፃናት ቀን፣ የአረጋውያን ቀን፣ የሰላም ቀን፣ የንባብ ቀን፣ የአረንጓዴ ልማት ቀን፣ የመከባበር ቀን፣ የሀገር ፍቅር ቀን፣ የአንድነት ቀን እና የኢትዮጵያ ቀን በሚሉ መለያዎች አዲሱን ኣመት ለመቀበል ህወሀት የያዘውን ፕሮግራም እንደ አንድ ማስረጃነት ሲጠቅሱ ይታያል። ታርሟል በሚል። መሬት ላይ የምናያቸው የስርኣቱ ባህርያት በምክንያት ለገመገመ ሰው ግን ስርዓቱ ለመሻሻል ፍላጎት እንደሌለው ይገነዘባል። በእኔ ምልከታ ችግሩ ከድርጅቱ ፍጥረታዊ ባህርይ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ተገንዝቤአለሁ። በመጀመሪያ ደረጃ ህወሀት ከምስረታው ጀምሮ … [Read more...] about ስትሄድ የመታህ ድንጋይ ስትመለስ ከደገመህ ከራስህ ጋር ስብሰባ መቀመጥ ይገባሀል
የወያኔ የሩብ ምዕተዓመት ስልጣንና ፀረ−ወያኔው የትግል ጉዞ
ወያኔ ስልጣንን የሙጥኝ ይዞ ሀገራችንንና ህዝቧን ቁም ስቅል ማሳየት ከጀመረ እነሆ 26 ዓመታት ተቆጠሩ። ከጀሌዎቹና ፍርፋሪ ከሚበትንላቸው አጨብጫቢዎቹ ያለፈ እዚህ ግባ የሚባል የህዝብ ድጋፍ ሳይኖረው ይልቁንም በህዝብ ተጠልቶና ተተፍቶ ከሩብ ምዕተዓመት በላይ ስልጣን ላይ የመቆየቱ ነገር እንቆቅልሽ የሆነባቸው እጅግ በርካታ ናቸው። በአንፃሩ ስርዓቱን ለማስወገድ በተለያየ አቅጣጫ የሚደረገው ትግል ውጤት አልባ መሆን ተስፋ አስቆርጧቸው የወያኔ ከወንበሩ መነሳት የማይታሰብ እንደሆነ የደመደሙም አልጠፉም። ይህ ፅሁፍ የገዢው ቡድን የስልጣን ዕድሜ እንዲህ የተንዘላዘለበትንና እስካሁን የተደረጉ የለውጥ ትግሎች ውጤት ያላመጡባቸውን ምክንያቶች እንዲሁም ወደፊት ወያኔን ለማስወገድ የሚደረጉ ትግሎች ከግንዛቤ ቢወስዷቸው መልካም የሚሆኑ ነጥቦችን ለመዳሰስ ይሞክራል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ … [Read more...] about የወያኔ የሩብ ምዕተዓመት ስልጣንና ፀረ−ወያኔው የትግል ጉዞ
አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ ምን ነካው?
ከአጭር ግዜ እረፍት በኋላ፣ EBC ላይ ብቅ ያለው "ቤቶች" በተሰኘው ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ በክፍል185 እጅግ አስደምሞናል። ተመልካቹ ህዝብ በማህበራዊ ድረ-ገጾች ጥላሁን ጉግሳ ላይ እየወረደበት ያለው "አሽቃባጭ፣ የወያኔ አቃጣሪ..." ወዘተ ውግዘቶችና ስድቦችን ባልጋራም፣ ይህ አንጋፋ አርቲስት ጥበብን የፖለቲካ መደለያ ስለማድረጉ ግን ምስክር አያሻም። በአንድ ወቅት እጅግ ተወዳጅ የነበረ ይህ ድራማ በመጠነኛ የህወሃት ልማታዊ ቅኝት እየተቃኘ መጥቶ አሁን ላይ ወገን የለየ ይመስላል። ዶፍ ሲጥል ገሚሱ ይበሰብሳል፤ ሌላው ተጠልሎ ይመለከታል፣ ጥቂቱ ደግሞ ይቀልዳል። ቀልደው ሞተዋል! ይህንን ድራማ ስመለከት፣ ገሃዱን አለም ከምናቡ አለም በቅጡ ሳይለዩ፣ ሃያልነትዋን ያልተረዱ አርቲስቶች ጥበብን ለተልካሻ ጉዳይ ሲመነዝሩዋት አስተዋልኩ። ወዶ ይሁን ተገድዶ ብቻ፣ በህዝብ ላይ የተከፈተ … [Read more...] about አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ ምን ነካው?
ለብቻው ቤተ-መንግስቱን ያንቀጠቀጠ ብላቴና፣ ቴዲ አፍሮ
በነዚያ የነተቡ ብዕሮች "ተራራውን ያንቀጠቀጠ" እየተባሉ ሲወደሱ የነበሩ ሁሉ እነሆ በአንድ ብላቴና ሲንቀጠቀጡ ከማየት የበለጠ ምስክር ከየትም ሊመጣ አይችልም። የ"ኢትዮጵያ" ስም ሲጠራ ብርክ እንደያዘው የሚሽመደመዱ፤ አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት እያልን በጣት የምንቆጥራቸው የጥላቻና የበቀል ጉግማንጉጎች ለመሆናቸውም ትውልድን ደፍሮ ይናገርላቸዋል። የዚህ ቡድን አባላት ከመጠን ያለፉ ጭቃዎች መሆናቸውን እንኳ ለማወቅ ራሳቸውን በመስታወት የሚመለከቱ አይመስልም። መቶ ሚሊዮን ሕዝብ እየመራ ያለው ይህ ቡድን በየትኛውም መመዘኛ ቢለካ አርቆ ማሰብ እና አስተዋይነት ይጎድለዋል። አስተዋይነት ደግሞ የታላላቆች ውድ ስጦታ ስለሆነ ከርካሽ ሰዎች አይጠበቅም። አበው ትተውልን ያለፉት አንድ ቅርስ፣ ያቺ የቀስተደመና ተምሳለት፣ ያቺ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንዲራ ስትነሳ አጋንንት እንደለከፈው እርያ … [Read more...] about ለብቻው ቤተ-መንግስቱን ያንቀጠቀጠ ብላቴና፣ ቴዲ አፍሮ
አታስብ ይሉኛል!
ማሰብ ማሰላል - ማጤን ማውጣት ማውረድ፤ ባ'ይምሮ መፀነስ - ሃሳብን ማዋለድድ፤ ከምናብ ጓዳ ውስጥ - ምስጢርን ፈልፍሎ፤ ያይምሮ መረዋን - ማንኳኳት ደውል :: መላ ማፈላለግ - እንዲህ ቢሆን? ማለት ፤ አይምሮን ኮትኩቶ - ዕውቀት ዘርቶ ማምረት፤ ባ'ንዱ ውስጥ ሌላው_ በሌላው ውስጥ አንዱ_ እንዳለ መረዳት:: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) አሥራደው (ከፈረንሳይ) … [Read more...] about አታስብ ይሉኛል!
ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን በፍርድቤት ውድቅ በማድረግ ኬኒያ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች!
“ፍርድ ቤቶች በነጻነት እንዲሠሩ ከተለቀቁ ፍትሕ ይበየናል” “ሁለቱም ተወዳዳሪዎች ውሳኔውን በመቀበል ለአገራቸው አኩሪ ተግባር ፈጽመዋል” ኦባንግ ሜቶ “ዛሬ በአፍሪካ ታላቅ ፍትኅ ተፈፀመ” ራይላ ኦዲንጋ በኬኒያ በቅርቡ የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በርካታ ችግሮች የገጠሙትና በአገሪቱ ሕግጋት መሠረት ያልተካሄደ ነው ሲል የኬኒያ ጠቅላይ ፍርድቤት ውጤቱን ውድቅ አድርጎታል፡፡ ከምርጫው ከመጀመሩ በፊት የኬኒያን ፖለቲካ በቅርቡ የሚከታተሉት ኦባንግ ሜቶ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በማድነቅ “ፍርድ ቤቶች በነጻነት እንዲሠሩ ከተደረጉ በምዕራቡ ዓለም ብቻ ሳይሆን አፍሪካም የሕግ የበላነይትና ፍትህ ይሰፍናል፤ ሁለቱም ተወዳዳሪዎች፤ ራይላ ኦዲንጋ ከአመጽ ይልቅ በሥርዓት ጥቄያቸውን ለፍትሕ አካል በማቅረባቸው፤ ኡሁሩ ኬኛታ ደግሞ ለፍርድ ቤቱ ውሳኔ እገዛለሁን ማለታቸው የሚደነቁ ናቸው፤ … [Read more...] about ፕሬዚዳንታዊ ምርጫን በፍርድቤት ውድቅ በማድረግ ኬኒያ ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች!
የህወሓት/ኢህአዴግ የገጠር መዋቅር ሊፈርስ ይችላል ተባለ
ህወሓት በትግራይ ላይ የራሱን አቋም እንዲወስድ ተመክሯል በኢትዮጵያ ያለማቋረጥ ሲካሄድ ከቆየው ሕዝባዊ ተቃውሞ አኳያ በህወሓት የደህንነት ክፍል የተሰበሰበው መረጃ፤ አሁን ካለው የተቃውሞ ንቅናቄ የተነሳ የኢህአዴግ የገጠር መዋቀር በኦሮሚያና በከፊል የአማራ ክልሎች ሊፈርስ እንደሚችል አስታወቀ። ከሁኔታው አሳሳቢነት የተነሳ ሊወሰዱ የሚችሉ አማራጮች ቢኖሩም ህወሓት ትግራይን አስመልክቶ የራሱን አቋም እንዲወስድ ሃሳብ ተሰጥቶታል። ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየደረሰበት ያለውን የሕዝብ ተቃውሞ ለመቆጣጠር ተስኖት ይገኛል። በተለይ “ባለራዕዩ መሪውን” ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ካስፈነጠረው ወዲህ ግምባሩ በአንድ መጓዝ፣ በአንድ መስማማት፣ በአንድ ማሰብ አቅቶት በተቃዋሚው መዳከምና በአንጋሾቹ አለሁ ባይነት … [Read more...] about የህወሓት/ኢህአዴግ የገጠር መዋቅር ሊፈርስ ይችላል ተባለ










