ጓቲማላዊው የቀድሞ ወታደር በሀገሪቱ የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት በተፈጸመ ጭፍጨፋ እጁ አለበት በሚል ከ5 ሺህ 160 ዓመት እስር ተፈረደበት። በፈረንጆቹ 1982 ጓቲማላ ውስጥ ዶስ ኤሬስ በተባለች ሀገር በተፈጸመ ጭፍጨፋ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸው የሚታወስ ሲሆን በ36 ዓመታት የእርስ በእርስ ጦርነት አሳዛኙ አጋጣሚ ነው ተብሏል። የቀድሞው ወታደር ሳንቶስ ሎፔዝ በአሜሪካ ስልጠና የተሰጣቸው የጓቲማላ ካይበለስ ሃይሎች አባል እንደነበር ተገልጿል። ሎፔዝ በመንደሯ ከሞቱት ሰዎች መካከል በ171ዱ በእያንዳንዳቸው 30 ዓመት እስራት የተቀጣ ሲሆን በህይወት የተረፈች ሴት ልጅ እንድትገደል በነበረው ሚና ተጨማሪ 30 ዓመት ተቀጥቷል። በጓቲማላ ህግ መሰረት ማንኛው ግለሰብ በእስር ከተቀጣ ከፍተኛው ቅጣት 50 ዓመት ነው። ከአውሮጳውያኑ 1960-1996 በቆየው የ36 ዓመታት የጓቲማላ … [Read more...] about የ5ሺ 160 ዓመት እስር ፍርድ ለሳንቶስ ሎፔዝ
በኮሞሮስ ባንዲራ የሚቀዝፉት የሜቴክ መርከቦች እና በካሪቢያን ስም የምትቀዝፈው የኢትዮጵያ መርከብ
የፌደራል ዋና አቃቢ ህግ ሜቴክ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ በገዛቸው ሁለት መርከቦች አማካኝነት በህግወጥ የንግድ እንቅስቃሴ መሰማራቱን ገልፆ እንደነበር ይታወሳል። ሆኖም ግን በሜቴክ ዋና ዳይሬክተር ሜ/ጄ ክንፈ ዳኘው ላይ የቀረበው ክስ ድርጅቱ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጪ አባይ እና ህዳሴ የተባሉትን ሁለት መርከቦች በመግዛት ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት የሀገርና ህዝብን ሃብት ያለ አግባብ አባክኗል የሚል ነው። ሆኖም ግን ለድረገፃች አዘጋጅ በደረሰው መረጃ መሠረት ሜቴክ የገዛቸው ሁለት መርከቦች እ.አ.አ. እስከ 02 – 07/-01-2016 በምስራቅ አፍሪካዊቷ የኮሞሮስ (Comoros) ደሴት ሰንደቅ ዓላማ አያውለበልቡ በህገወጥ ንግድ ተሰማርተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ በቀረበው የቴሌቪዥን ዶክመንተሪ ሜቴክ እ.አ.አ. በ2014 ዓ.ም አባይ እና ህዳሴ የተባሉን መርከቦች … [Read more...] about በኮሞሮስ ባንዲራ የሚቀዝፉት የሜቴክ መርከቦች እና በካሪቢያን ስም የምትቀዝፈው የኢትዮጵያ መርከብ
THE WAY FORWARD: CAN THE RIGHT CHANGE BE SUSTAINED IN ETHIOPIA?
Mr. Obang Metho, Executive Director, Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) will be a Guest Lecturer at The University of Gondar Lecture Title and Description: THE WAY FORWARD: CAN THE RIGHT CHANGE BE SUSTAINED IN ETHIOPIA? Ethiopia is in a state of great change. Many regard it as a miracle, a door that few believed could be opened, a glimmer of light that has resurrected hope for change that seemed impossible less than a year ago. This momentum for change has led to new freedoms and … [Read more...] about THE WAY FORWARD: CAN THE RIGHT CHANGE BE SUSTAINED IN ETHIOPIA?
ሌብነት፣ ውንብድ፣ ግፍና ውርደት ልክ እንደ ጌታቸው
“የእኔ ሀብት ሰውነቴ ብቻ ነው የተመዘገበው ሀብት የእኔ አይደለም” ክንፈ ዳኘው የያሬድ ዘሪሁን አሰቃቂ ድርጊት በፍርድ ቤት ተነገረ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የአገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ የነበሩት አቶ ያሬድ ዘሪሁን፣ በተጠረጠሩበት ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በዜጎች ላይ ፈጽመውታል የተባለ አሰቃቂ ድርጊት በፍርድ ቤት ተነገረ። አቶ ያሬድ የዜጎችን ሰብዓዊ መብት ማክበርና ማስከበር ሲገባቸውና ሕዝብ እንዲያገለግሉ የተሰጣቸውን ሥልጣን ወደ ጎን በመተው፣ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ከነበሩት አለቃቸው አቶ ጌታቸው አሰፋ የሚቀበሉትን ትዕዛዝ ለበታቾቻቸው ኃላፊዎችና ሠራተኞች በማስተላለፍ፣ ዘግናኝና ከባድ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውንና እንዲፈጸም ማድረጋቸውን የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መርማሪ … [Read more...] about ሌብነት፣ ውንብድ፣ ግፍና ውርደት ልክ እንደ ጌታቸው
የሜቴኩ ክንፈ እና የኢንሳው ተክለብርሃን በቁጥጥር ሥር ውለዋል
የቀድሞው የሜቴክ ዋና ኃላፊ የነበረው ክንፈ ዳኜው እና የኢንሳ (የህወሃት የኢንፎርሜሽን ስለላ) ኃላፊ የነበረው ተክለብርሃን ወልደአረጋይ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት (አብመድ) በፌስቡክ ገጹ ምንጮቹን ጠቅሶ አስታውቋል። ዋልታ እንደዘገበው ደግሞ “ሱዳን ድንበር አካባቢ የተያዙት ሁለቱ ተጠርጣሪ ግለሰቦች ዛሬ (ማክሰኞ) ከሰአት ወደ አዲስ አበባ እንደሚገቡ የደረሰን መረጃ ያመለክታል”። አብመድ ግለሰቦቹን በስም ባይጠቅስም በዜናው ላይ ግን “የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) እና የኢንሳ የቀድሞ ኃላፊዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል” በማለት ነበር የዘገበው። ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ትላንት በሰጠው መግለጫ ሜቴክ ያለምንም ጨረታ የ37 ቢሊዮን ብር ግዢ የፈጸመ መሆኑን የተናገረ ሲሆን በሽብር፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና በሙስና ወንጀሎች የተጠረጠሩ … [Read more...] about የሜቴኩ ክንፈ እና የኢንሳው ተክለብርሃን በቁጥጥር ሥር ውለዋል
አማራና ትግራይ ክልሎች ከቃላት ጦርነት ወደ መሣሪያ መማዘዝ?
ሰሞኑን በአማራና በትግራይ ክልል መካከል የተፈጠረው የመግለጫ እሰጥ አገባ ከቃላት ጦርነት ወደ መሣሪያ መማዘዝ እንዳይቀየር ፍርሃቻ አለ። የኤርትራው መሪ ኢሳያስ አፈወርቅ ወደ አማራ ክልል ለጉብኝት መምጣታቸው በህወሓት አቀንቃኞች ዘንድ በፍርሃቻ እየታየ ነው፤ ሌሎች የዘር ፖለቲካ አራማጆች ደግሞ ጉብኝቱን ስህተት ነው ብለውታል። የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅና የሱማሌው ፕሬዚዳንት ሙሐመድ አብዱላሂ ፎርማጆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ግብዣ ዛሬ በአማራ ክልል ጉብኝት ለማድረግ ጎንደር ገብተዋል። ይህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ጉብኝት የጎንደርና አካባቢውን ታሪካዊ ቦታዎች ለመመልከትና በባህር ዳር ውበት ለለመሰጥ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። በተለይ ኢሳያስ በተደጋጋሚ በትግራይ አመራር ላይ ካሉት የህወሓት ሰዎች የቀረበላቸውን የወዳጅነት ጥያቄ ችላ በማለት ከህወሓት ጋር … [Read more...] about አማራና ትግራይ ክልሎች ከቃላት ጦርነት ወደ መሣሪያ መማዘዝ?
የሰባት አመቷ ህፃን በፀሎት ብርሃኑ – ተሰርቃ፣ ተደፍራ በግፍ የተገደለች‼
ከጥቂት ቀናት በፊት በደሴ ከተማ አንድ የሰባት አመት ታዳጊ ለቀናት ከጠፋች በኋላ፤ ተገድላ መገኘቷን ተከትሎ የተቆጡ ነዋሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ አድርገው ነበር። በወቅቱ ታዳጊዋ ከመገደሏ በፊት መደፈሯን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በተያያዘ ታዳጊዋን አስገድዶ በመድፈር የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአማራ ቴሌቪዥን መዘገቡ ይታወቃል። አሰቃቂ ወንጀል በሚፈጽሙ ግለሰቦች ላይ ቀደም ሲል የሚሰጠው የፍርድ ውሳኔ ተመጣጣኝ ባለመሆኑ በርካቶች ሌላ የወንጀል ድርጊት እንዲፈጽሙ እያደረገ ነው ሲሉ የደሴ ከተማ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን ገለጹ። በርካታ ቁጥር ያላቸው የደሴ ከተማዋ ነዋሪዎች የሰባት ዓመት ህጻን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ የማያዳግምና ሌላውን ሊያስተምር የሚችል እርምጃ እንዲወሰድበትም ትላንት በአደባባይ ጠይቀዋል። የሟች ህጻን በጸሎት ብርሃኑ እናት ወይዘሮ አበባ ሙህዬ … [Read more...] about የሰባት አመቷ ህፃን በፀሎት ብርሃኑ – ተሰርቃ፣ ተደፍራ በግፍ የተገደለች‼
አዲሷ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሬስ ሴክሬተሪ በዜግነት ካናዳዊት ናቸው
በዚህ ሳምንት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬስ ሴክሬታሪ ሆነው የተሾሙት ወ/ሪት ቢልለኔ ስዩም ወልደየስ በዜግነት ካናዳዊት መሆናቸው ጥያቄ አስነስቷል። ሹመታቸውም በሥራ ላይ ያለውን ሕግ የሚጻረር ነው ተብሏል። ወ/ሪት ቢልለኔ ለማስተርስ ዲግሪ ያቀረቡትን ጥናታዊ ጽሁፍ “Transformative Spaces: Enabling Authentic Female Leadership Through Self Transformation - the Association of Women in Business” ወደሚል መጽሐፍ ቀይረው ባሳተሙት ገጽ 16 ላይ በትውልድ ኢትዮጵዊት በዜግነት ግን ካናዳዊት መሆናቸውን ጠቅሰዋል። ከዚህ አንጻር ከታየ ሹመታቸው የሕግ ጥያቄ እንደሚስነሳ የሪፖርተሩ ዳዊት እንደሻው ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያ ይናገራሉ፤ “አዋጅ ቁጥር 270/1994፣ ‹‹የኢትዮጵያ ተወላጅ የሆኑ የውጭ ዜጎች በትውልድ … [Read more...] about አዲሷ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሬስ ሴክሬተሪ በዜግነት ካናዳዊት ናቸው
ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሹመት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ
ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ መንግሥት ባደረገላቸው ጥሪ መሠረት ነገ ጠዋት 1:30 አዲስ አበባ ~ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ይደርሳሉ። ተወልደው ባደጉበት አዲስ አበባ ፈረንሳይ ሌጋሲዮን ሠፈር ለብርቱካን ደማቅ አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቶች ተጠናቀዋል። ሪፖርተር በዘገበው መሠረት ብርቱካን “በመንግሥት ጥሪ ወደ አገር ቤት ጠቅልለው ከተመለሱ ምናልባትም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር፣ ወይም የፌዴራል የመጀመርያ ወይም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ተደርገው ሊሾሙ እንደሚችሉ ከወዲሁ ትንበያዎች እየተሰሙ ነው” ብሏል። ወ/ሪት ብርቱካን ወደ አዲስ አበባ ከመብረራቸው በፊት ለአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ በሰጡት አስተያየት “አገሪቱ ባለችበት ሁኔታ ለመርዳት ማንም ሰው የሚችለውን ነገር ለማድረግ ወደ ኋላ የሚልበት ጊዜ አለመሆኑን በመረዳት እኔም በበኩሌ … [Read more...] about ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ለሹመት ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ
ሽመልስ አብዲሳ አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ
ለበርካታ ወራት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ፍጹም አረጋ ወደ ቀድሞ መሥሪያ ቤታቸው የኢንቨስትመንት ጽ/ቤት እንደሚመለሱ ከተነገረ ወዲህ ቦታቸውን የሚተካው ማን እንደሚሆን እስካሁን አልታወቀም ነበር። ዛሬ ከተለያዩ ምንጮች የተሰራጨው መረጃ እንደሚያመለክተው አቶ ሽመልስ አብዲሣ የፍጹም አረጋን ቦታ ተክተው እንደሚሠሩ ታውቋል። በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት በአዲስ መልክ በተደራጀው “ፕሬስ ሴክሬተሪ” ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2011 ዓ.ም. ከቀኑ በ8:00 ላይ በጽ/ቤቱ አዳራሽ ጋዜጣዊ መግለጫ የሚሰጥ ሲሆን ሹመቱም በዚሁ ጊዜ ይፋ እንደሚገለጽ ይነገራል። አቶ ሽመልስ አረጋ በቡድን ለማ (ቲም ለማ) ውስጥ ቁልፍ ቦታ የነበራቸው የለውጡ አካል ሲሆኑ የኦዴፓ እና ኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ አባል ናቸው። አቶ ሽመልስ በኦሮሚያ ክልል የኮንስትራክሽን ቢሮ … [Read more...] about ሽመልስ አብዲሳ አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ኃላፊ










