• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዲሷ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፕሬስ ሴክሬተሪ በዜግነት ካናዳዊት ናቸው

November 7, 2018 03:05 pm by Editor 3 Comments

በዚህ ሳምንት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬስ ሴክሬታሪ ሆነው የተሾሙት ወ/ሪት ቢልለኔ ስዩም ወልደየስ በዜግነት ካናዳዊት መሆናቸው ጥያቄ አስነስቷል። ሹመታቸውም በሥራ ላይ ያለውን ሕግ የሚጻረር ነው ተብሏል።

ወ/ሪት ቢልለኔ ለማስተርስ ዲግሪ ያቀረቡትን ጥናታዊ ጽሁፍ “Transformative Spaces: Enabling Authentic Female Leadership Through Self Transformation – the Association of Women in Business” ወደሚል መጽሐፍ ቀይረው ባሳተሙት ገጽ 16 ላይ በትውልድ ኢትዮጵዊት በዜግነት ግን ካናዳዊት መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ከዚህ አንጻር ከታየ ሹመታቸው የሕግ ጥያቄ እንደሚስነሳ የሪፖርተሩ ዳዊት እንደሻው ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያ ይናገራሉ፤ “አዋጅ ቁጥር 270/1994፣ ‹‹የኢትዮጵያ ተወላጅ የሆኑ የውጭ ዜጎች በትውልድ አገራቸው የሚኖራቸውን መብት ተጠቃሚነት ለመወሰን በወጣው ሕግ መሠረት፣ ማንኛውም የውጭ ዜግነት ያለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ በማናቸውም የአገር መከላከያ፣ የአገር ደኅንነት ወይም በውጭ ጉዳይና መሰል የፖለቲካ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በመደበኝነት ተቀጥሮ መሥራት እንደማይችል ተደንግጓል፤” ይላል።

“በዚህም አዋጅ መሠረት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትም እንደ አንድ ወሳኝ የፖለቲካ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የውጭ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መቀጠር እንደማይችሉ፣ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያዎች ያስረዳሉ። ይህ ጉዳይ መንግሥት ትኩረት ሊሰጥበት የሚገባው ነው። ምክንያቱም ዜጎች ለየትኛው ፖስፖርት ነው ታማኝነታቸው የሚለውን ጥያቄ ያስነሳል … ትውልደ ኢትዮጵያዊያኑ እንዲህ ዓይነት ቦታ ላይ መቀመጥ ካለባቸው፣ የያዙትን የውጭ አገር ዜግነት መመለስ ይገባቸዋል” ሲሉ አንድ የሕግ ባለሙያ ተናግረዋል።

ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ሪፖርተር ፕሬስ ሴክሬታሪዋን በስልክ የጥሪና የጽሑፍ መልዕክት፣ እንዲሁም በትዊተር ገጻቸው መልዕክት በመላክ ለማግኘት ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም መልስ ከመስጠት ተቆጥበዋል። አለቃቸውን አቶ ሽመልስ አብዲሣንም ለማግኘት ደረገው ሙከራ እንዳልተሳካለት ሪፖርተር ጠቅሷል።

ሪፖርተር ለቃል አቀባይዋ በስልክ የጥሪና የጽሑፍ መልዕክት፣ እንዲሁም በትዊተር ገጻቸው መልዕክት ቢልክም መልስ ማግኘት አልቻለም። በተጨማሪም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተደርገው የተሾሙትን አቶ ሽመልስ አብዲሳን ለማግኘት የተደረገው ሙከራም አልተሳካም።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: billene, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    November 8, 2018 06:43 pm at 6:43 pm

    የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፕሬስ ሴክሬታሪ ሆነው የተሾሙት ወ/ሪት ቢልለኔ ስዩም ወልደየስ በዜግነት ካናዳዊት መሆናቸው ጥያቄ አስነስቷል።
    አዋጅ ቁጥር 270/1994፣ ‹‹የኢትዮጵያ ተወላጅ የሆኑ የውጭ ዜጎች በትውልድ አገራቸው የሚኖራቸውን መብት ተጠቃሚነት ለመወሰን በወጣው ሕግ መሠረት፣ ማንኛውም የውጭ ዜግነት ያለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ በማናቸውም የአገር መከላከያ፣ የአገር ደኅንነት ወይም በውጭ ጉዳይና መሰል የፖለቲካ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በመደበኝነት ተቀጥሮ መሥራት እንደማይችል ተደንግጓል፤›› ይላል፡፡
    በዚህም አዋጅ መሠረት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትም እንደ አንድ ወሳኝ የፖለቲካ የመንግሥት መሥሪያ ቤት የውጭ ዜግነት ያላቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊያን መቀጠር እንደማይችሉ፣ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡
    ‹‹ይህ ጉዳይ መንግሥት ትኩረት ሊሰጥበት የሚገባው ነው፡፡ ምክንያቱም ዜጎች ለየትኛው ፖስፖርት ነው ታማኝነታቸው የሚለውን ጥያቄ ያስነሳል፤›› ሲሉ አንድ የሕግ ባለሙያ ተናግረዋል፡፡
    **************
    የዚህ ጉዳይ አንሺዎችና(ጋዜጠኞች) ሕጉን ያብራራው ባለሙያ(ጠበቃ) የሕጉን ትክክለኛነትና ጉድለትን አይተቹም!?ልዩ ጥቅማጥቅም
    በመሠረቱ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦችን ( አበበ አበባና አቦቦች) ማለትን አንድ ነው ብሎ የተቀበለ ይህንንም ሕገመንግስት የሚቃወም ይሁን ማሻሻል ወይንም አንድ ቃል ቢያወጣ አፈነዳለሁ! አፈርሳልሁ! እገነጥላለሁ! ለሚሉ ዲያስፐርስ ምንም አልተባሉም። አደለም እንዴ?
    ይህ ጫጫታ ምንድነው?
    “ኢትዮጵያውያንና ትወልደ ኢትዮጵያውያን” ለነገሩ ክልላዊ ማንነት እንጂ ሀገራዊ ዜግነት ዋጋ እንዳለው ሕዝቡ አሁን እንዴት ገባው? ለዚያውም ለጠ/ሚ ወሬ ተንታኝ ለመሆን? ሀገሪቷ አዲስ ነገር አይታይበሽ ተበላ እንደተረገመች አቃቂረኛና አሽሙረኛው አፉን አሹሎ ብቅ ይላል።
    ለምሳሌ የቻይና ቲቪ ጋዜጠኛ ግሩም ጫላ ጥያቄ መጀመሪያ የሥራ ቋንቋዬ እንግሊዘኛ ስለሆነ ጥያቂዬን በእንግሊዘኛ ላቅርብ ይላል” …ኢትዮጵያዊ ሆኖ በሥራ ቅጥር ቻይናዊ ሆኗል ማለት ነው። በአሜሪካ እና ካናዳ ሌሎችም ሀገር ያሉ የውጭ ጋዜጠኞች ስፓንሹም ፈረንሳዩም ትንታኔ የሚጠይቁት በሀገሩ ብሔራዊ ቋንቋ እንጂ በመጡበት ሀገር ወይም በተቀጠሩበት ሀገር ቋንቋ አደለም። ግሩም ጫላ ለምን ለየት ለማለት ፈለገ?
    ወ/ሪት ቢልለኔ ስዩም ወልደየስ በዜግነት ካናዳዊት መሆናቸው ለማሳጣት ወይስ እንግሊዘኛ ብቃታቸውን ለመፈታተን? (መሰሪነት!)
    ሌላው ያነሳው ነጥብ ” ከእናንተ ይልቅ ጠ/ሚ ኮ/ል አብይ አህመድ በወር አንድ ግዜ ከፈረሱ አፍ መስማት እንፈለጋለን” ይላል ይህ ሁለተኛው ጠለፋ ነው። (ግሩም ጫላ.አዲስ አበባ ኢትዮጵያ) ሲል በጣም ደስ የሚለኝ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነው።
    ጠ/ሚ ኮ/ል አብይ ለአዳራሽ የሚበቃ ጥሩ የንግግር ችሎታ ቢኖራቸውም (ጋዜጠኛው አፋጠጣቸው፡ ታሪክ ሰራ) የሚያስብል አልባሌ ጥያቄ በመጣል አድናቆትን የሚያነፈንፉ ጋዜጠኞች ) አስተሳሰብ ነው። ዓብይ አሁን አንዳንዱ ጨዋታም ገብቷቸዋል ማለት ነው፡ ወይ ፀጥ ለጥ አድራጊ አፈቀላጤ መቅጠር አለዚያም ይህንን ጥያቄ አልፈዋለሁ ማለት። በበኩሌ ጠ/ሚ ኮ/ል አብይ በአሽሙር ከመለሰው መልስ ይልቅ…በተለይ ሕግ ነክ ጥያቄዎችን ሳያጨማልቅ ጥያቄዎችን የዘለለበት ዘዴዎች በጣም ተስማምቶኛል..የመለስን ራዕይ ቢከተል እንዲሁ የቻይና ተረት፡ የጫት ላይ ቀልድ ፓርላማ እየቀለደ በውሸት ጭብጫቦ ይደነቁር ነበር።
    ሌላው ቱማታ “ዜጎች ለየትኛው ፖስፖርት ነው ታማኝነታቸው የሚለውን ጥያቄ ያስነሳል፤››
    ድንቄም! መጀመሪያ ግሎባላይዜሽን ሉዓላዊ ሀገርነትህን ገፎታል። የኢትዮጵያ ሕገመንግስትም ዳር ደንበር በክልሎቹ ይወሰናል ይላል እንጂ አዋሳኝ ሀገር ድንበር የለንም፡ጭራሽ አሁን አፍሪካን አንድ ማድረግ ሕልም በገዳ ሥርዓት ማስተሳሰር ሲባል አብረህ ታጨበጭባለህ ከፍተህ ምን ልትሰጥ፡ ምን ልትቀበል እንደሆን ይታያል!። ዛሬ የሚያበድሩንና የሚረዱን ሀገራት ፳፪ ቢሊየን ዶላር ዕዳ ሲቆሉሉብን የጋዜጠኛ ወሬን ሳይሆን ወርቅ፡ ነዳጅ፡ ቅርስ፡ ገንዘብ፡ብረትና ቡና የት እንዳለ ሥንት እንደሚያወጣ ከአየር ላይ እየተቆጣጠሩና እየመዘገቡ እንደሆነ ማወቅ ነው። ይህንን ለማድረግ ሳተላይት እንጂ ፓስፖርት(ዜግነት፡ቪዛ) አያስፈለጋቸውም ግድግዳ ላይ የተጻፈን ቆሞ ጋዜጠኛ ፊት ማውራት ምን ያህል የሀገር ድብቅ ሚስጠር ቢሆን ነው? ስንቱ የወጭ ዜግነት ይዞ ሚዲያ ከፍቶ ሁለተኛ መንግስት መስርቻለሁ ይል የለምን? የአንድን ደሃ ሀገር ዓመታዊ የትምህርት ፈተና ሰርቄ እኔነኝ መልስ የሰራሁትና መንግስትን ዕዳ የጨመርኩት የሚልን ጎረምሳ ቤተመንግስት አስገብቶ ያንፈላሰስ የለምን? ትውልደ ኢትዮጵያዊውን አደለም አንድ ዶላር ከቡና ቀንስ ሀገርህን ዕርዳ ተብሎ የሚለመነው? የትውልደ ኢትዮጵያዊው የቤተሰብ እርዳታ አደለም ከውጭ እርዳታ የሚበልጠው? ለመሆኑ ከነጭ እውቀት ከምንለምን የነጭ ዕውቀት ነጥቀው በሚመጡ ብንጠቀምበት ምንድነው ችግሩ? ለመሆኑ ጠ/ሚሩ በተለያዩ የውጭ ሀገራት ሲሄዱ ትምህርት፡ ጤና፡ መከላከያውን ለማጠናቀር እርዱኝ ብለው ሲለምኑ የሀገር ሚስጥር ሳይገለጥ ነው? እነኝህ ሰዎች ለመምከርና ለመርዳት ሲመጡ የክልል ዜግነትና ፓስፖርት ተሰጥቷቸው ነው? (ቂጥ ገልቦ ክንብንብ) አሉ
    **************
    ይህ ጉዳይ ኮ/ል አብይ አህመድ የአብዛኛውን ተቃዋሚ ተፎካካሪ ተደጋፊ ከበሮ ቀምቶ መደለቅ ሲጀምር ብዙው ሥራ ፈት ሆኗል። ከ፷፭ ፓርቲ ለምርጫ ውድድር የተመዘገበው እንኳ ፭ አልሆነም !? ሁሉንም ኢህአዴግ አድርጎ ደምሮታልና!!። ጋዜጠኛውንም..ሰበር ዜና፡ ሚስጥር፡ ሹክሹክታ፡ውስጥ አዋቂ የሚለውን በአንድ ቃል አቀባይ ለሁሉም ያወራዋል ስለዚህ ነገሮች ግልጽ እየሆኑ ይሄዳሉ የስሚ ስሚ የለም ቃል አቀባዮቹ ጠ/ሚስተሩንም ፓርቲውንም ይሞግቱለታል .. አሉ.. ተባለ አሉ.. መሰለኝ… ጠረጠርኩ የሚሉ እንቶፈንቶ ወሬ ይቀንሳል ይቀራልም። ስለዚህ ጅምሩን መተቸት፡ አለዚያም ማተራመስ ወይም መቀወጥ ስልታዊ መሸበርና ማሸበር ነው በለው!

    Reply
  2. አለም says

    November 8, 2018 07:22 pm at 7:22 pm

    ውድ ጎልጉል፣
    ለምን ይደንቃል? እንግሊዛዊው ግልክስ በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ዋና አማካሪ ሆኖ ሲሠራ ይኸ ጥያቄ እንዴት አልተነሳም? ወ/ት ቢልለኔማ ትውልደ ኢትዮጵያዊ ነች! አላሙዲ በእናቱ ኢትዮጵያዊ በአባቱ የመን የሳውዲ ዜጋ ሆኖ ከአንድ ኢትዮጵያዊ የበለጠ መብት አልነበረውም? ቢልለኔማ በእናትም ባባትም ኢትዮጵያዊት ነች። ፕሬስ ሰክሬተሪነት የሚጠይቀው ብቃት አለ፤ አንደኛው የውጭውን ኣለምና ያገር ቋንቋ አጥርቶ ማወቅ ነው።

    Reply
  3. demeke alamirew says

    November 9, 2018 11:40 am at 11:40 am

    አቶ ተወልደ አሜሪካዊ ሁኖ አይደል አየር መንገድን እፓርታይድ ያደረገው

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule