ክፉ ቀን ብዙ ክፉ ምግባሮች ይዞ ይመጣል። በቀይሽብር ወቅ በመቀሌ ከተማ ያጋጠመ አንድ የክፉ ምግባር ምሳሌ ነበር። ዘስላሰ የተባለ ወጣት በፀረ ደርግነት ተጠርጥሮ የቀይ ሽብር ሰለባ በመሆን በባዛር እየተባለ የሚታወቀውና አሁን በስሙ ዘላሰ የተሰየመው የአፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት ፊትለፊት የሚገኝ አደባባይ ይረሸናል። ወላጅ እናቱ በደርግ ወታደሮች ተገድደው እልልል እያሉ፣ እያጨበጨቡ ደስታቸው እንዲገልፁ ተደርገዋል። ያ ቀይ ሽብር ክፉ ቀን የወለደው ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል። አሁንም ይሄ ጥቁር ታሪክ ዳግማዊ ትንሳኤውን አግኝቷል። የጥቁር ታሪክ ባለቤት የሆነችው የሰሜን ወሎ ዞን፣ ቆቦ ወረዳ 027 ቀበሌ ነዋሪ እናት ወይዘሮ ብርቱኳን ዓሊ ነች። የ5 ዓመት ልጇን በረሃብ አጥታ እያነባች ለቢቢሲ የሰጠችው ቃለ ምልልስ ኢህአዴግን አስቆጥቶ ልክ እንደ የዘስላሰ እናት አስገድደው … [Read more...] about ክፋት በዛ
ከ9ሺህ በላይ ፈላሻ ሙራዎች ወደ እስራኤል ሊጓዙ ነው
ከ25 ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ለመጓዝ እየጠበቁ ያሉ በተለየ ፈላሻ ሙራ ተብለው የሚጠሩት ቤተ እስኤላውያን ወደ “ቅድስት አገራቸው” እንዲመጡ የእስራኤል መንግሥት ወሰነ፡፡ እስኤል እንደገቡም የአይሁድ እምነትን በተመለከተ የተሃድሶ ትምህርት እንደሚሰጣቸው ተመልክቷል፡፡ በእስራኤል ያሉ እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ የዜና ምንጮች እንደዘገቡት የጠ/ሚ/ር ቢኒያም ኔታንያሁ መንግሥት ውሳኔውን ያስተላለፈው እሁድ ዕለት በሙሉ ድምጽ ነበር፡፡ ይህ የአሁኑ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የዛሬ ሁለት ዓመት እስራኤል ምንም ዓይነት ዜጋዋ በኢትዮጵያ እንደሌለ ይፋ ነበር፡፡ “ዛሬ ጠቃሚ ውሳኔ አስተላልፈናል” በማለት የተናገሩት ኔታንያሁ ውሳኔው በእስራኤል እየኖሩ ከቤተሰቦቻቸው ለተለያዩት ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሰጪና ጠቃሚ እንደሆነ በላኩት መግለጫ አመልክተዋል፡፡ ከዚህ በፊት እስራኤል “የተስፋዋ … [Read more...] about ከ9ሺህ በላይ ፈላሻ ሙራዎች ወደ እስራኤል ሊጓዙ ነው
ካልተጠነቀቅን አፋፍ ላይ ነው ያለነው!!
ቁጥሮቹ አስገራሚ ናቸው - ማለቴ ለኢትዮጵያ። በ1997 ዓ.ም፣ (ከአስር ዓመት በፊት መሆኑ ነው...) የአገሪቱ ገበሬዎች ጠቅላላ የእህል ምርት 119 ሚሊዮን ኩንታል ነበር። አምና ደግሞ፣ 236 ሚሊዮን ኩንታል። እነዚህ፣ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ቁጥሮች... ስህተት ይሆኑ እንዴ? ሊሆኑ አይችሉም ለማለት አስቸጋሪ ነው። አንደኛ ነገር፣ አስደናቂው የእድገት መረጃ፣ ከሌሎች በርካታ መረጃዎች ጋር ሲጋጭ፣ ምን ታደርጉታላችሁ? መስኖ፣ ... እንደድሮው ነው (1% ለመሙላት ብዙ ይቀረዋል)! መቼም፣ ከእርሻ እድገት ጋር አብሮ፣ የመስኖ ጉዳይ መነሳቱ አይቀርም። ባለፉት አስር አመታት፣ የመስኖ እርሻ ተሻሽሎ ይሆን? አልተሻሻለም - ከጫት እርሻ በቀር። መስኖን በመጠቀም፣ የጫት ማሳዎችን የሚስተካከል የለም። በበሬ ማረስ? እሱም በሬ ከተገኘ ነው! ለእርሻ ስራ፣ ሁለት በሬ ካላቸው … [Read more...] about ካልተጠነቀቅን አፋፍ ላይ ነው ያለነው!!
ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!
* ከአገዛዝ ለውጥ በፊት ችጋር ይቀድማል? * “በአሁኑ ጊዜ ችጋሩ እንደ 1977 ሆኗል!” በኢትዮጵያ ላለፉት ፴ ዓመታት ያለታየ ችጋር ተከስቷል። ድርቁና ረሃቡ ከዚህም በላይ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ኢህአዴግን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይፋ እያደረጉ ነው። “የምግብ ዋስትናን አረጋግጫለሁ” በማለት ሲወተውት የኖረው ህወሃት ተገዶ ያመነው ችጋር ከ፩፱፯፯ ድርቅ በላይ የከፋ እንደሚሆን ስጋት አይሏል። ከዚህ በፊት እንደተከሰቱት ለውጦች ይህኛውም የአገዛዝ ለውጥ ሊያስከትል እንደሚችል ተነገረ። በአስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል መቋቋም እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ህወሃት ከድርቅ እና ድርቅን ተከትሎ ከሚገኝ ዕርዳታ ጋር በተያያዘ ካለው አስጸያፊ ተሞክሮ በመነሳት ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ እንደሚሉት ከድርቁ ጋር በተያያዘ ፍትሐዊነት ያሳስባቸዋል፡፡ ሲያብራሩም በከፍተኛ የሙስና እና የአድልዖ … [Read more...] about ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም!
ለሌባ ባለሥልጣናት መጦሪያ ቤት?
በ1967 የወሎ ሕዝብ በድርቅ ሲረግፍ ንጉሱ ለልደታቸው ከእንግሊዝ አገር በመጣ ኬክና ከእስኮትላንድ በተጫነ ውስኪ ይራጩ ነበር የሚል ዜና ደርግ ሲያስነግር አገሪቷ በሰላማዊ ሰልፍ ቀውጢ ሆነች። ይህም የቀዳማዊ ኃይለስላሴን አገዛዝ ለመገርሰስ ግብዓት ሆነ። በ1977 የትግራይና የወሎ ሕዝብ በረሃብ ሲረግፍ ደርግ አስረኛ የልደት በአሉን ለማክበር ከኮሪያ ባስመጣው ርችት ታጅቦና አገሪቷን በቀለም አዥጎርጉሮ ያረግዳል የሚል ዜና ሲያስተጋባ ምእራባውያን ለሕወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ እርዳታና ይሁንታ ሰጡ። ይህም ለደርግ መውደቅ የራሱን አስተዋጽኦ አበረከተ። በ2008 ድርቅ አስር ሚሊዮን የሚሆን ወገናችንን ሲያጠቃ ኢህአዴግ ሰፋ ብላ የድርጅቶቿን ልደት በሚሊዮን በሚቆጠር ብር እያከበረች ነው። ይህ ሁሉ ወገን በሚራብበትና በሚቸገርበት አገር ውስጥ ከሰሞኑ የተነገረው ዜና ደግሞ ጆሮ ጭው … [Read more...] about ለሌባ ባለሥልጣናት መጦሪያ ቤት?
Cry for Tigrai
Famine is back in Ethiopia. Famine and Ethiopia have become so interchangeable western comedians don’t feel shame making famine jokes using us as a punch line. How is our first 21st Century famine being welcomed in our precious homeland? I am afraid our response has not changed. Denial, surprise, blame and righteous indignation have been brought out of the closet. The response by the Emperor, the Junta and the ethnically challenged mafia group are typical Ethiopian. ‘Shit happens but this time … [Read more...] about Cry for Tigrai
ብሔር ወይስ ሰው-ነት?
መኃኑን ታሪክ ለማዋለድ በሚደረገዉ "ጥረት" አብዝቼ ባዝንም፣ የቀደመዉን የሃገሬን ጠመዝማዛ የታሪክ መንገድ ግን ከነእንከኑ እቀበለዋለሁ፡፡ የታሪክ ክህደትም ሆነ የታሪክ ብዜትን ሊጭኑብኝ ለሚሞክሩ ሰንባችም ሆኑ አርፋጂ ብሄረተኞች ጆሮዬንም ሆነ አዕምሮዬን የምሰጥ ሰዉ አይደለሁም፡፡ ትላንትን በዛሬ መነጽር ባላየዉ እንኳን የቀደመዉን ዘመን በሰብዓዊነትና በማህበረሰባዊ ዉል ሚዛን ላይ አስቀምጬ እንድመለከተዉ ሰው-ነቴ ያስገድደኛል። ሰው ነኝና። ሰው።. . . . በገባኝ መጠን የዛሬዋን ቁርጭምጭሚት ኢትዮጵያ ወደ ቀደመ ከፍታዋ ለማውጣትና ገጽታዋን ለማደስ ሲሚንቶው ሰብዓዊነት ሊሆን ይገባል። ከብሔር አጥር ባሻገር ዜግነት የሚባል ሰፊ ሜዳ እንዳለ ልብ እንበል። ኢትዮጵያችንን ከሁለንተናዊ ውድቀት ለመታደግም ሆነ ዳግም ለመገንባት የቀጥታ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ብቻ መፍትሄ አይደለም። ይልቁንስ … [Read more...] about ብሔር ወይስ ሰው-ነት?
Center for the Rights of Ethiopian Women welcomes Reeyot Alemu
Center for the Rights of Ethiopian Women (CREW) is delighted to announce the arrival of the award winning journalist, Reeyot Alemu to the United States on Saturday, November 7, 2015. CREW sent invitation to the respected journalist and freedom of speech advocate, Reeyot Alemu and her sister Eskedar Alemu to speak at the upcoming Women and Leadership Conference which will be held sometime in the coming month. Reeyot has been imprisoned for over 4 years and was released in July of 2015. Reeyot … [Read more...] about Center for the Rights of Ethiopian Women welcomes Reeyot Alemu
ሁለት ጥያቄ ብቻ አለን?
ድሬ ቲዩብ በመባል የሚታወቀው በአማርኛ "ትልቁ" የድህረ ገጽ እና ድህረ ምስል አውታር፣ ሰሞኑን አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፣ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ሁለት ጥያቄ ጠይቆ ነበር። 1ኛው የኢትዮጵያ መሪ (ፕሬዝዳንት) ማን ናቸው? የሚል ሲሆን 2ኛው ደሞ የአሁኑ የአዲስ አበባ ከንቲባ ስማቸው ማን ይባላል? የሚሉ ናቸው ። ሕዝቡም እንደ አቅሙ ትክክለኛውን መልስ ለማግኘት ጥሯል። ሙላቱ አስታጥቄ፣ እንዳለ አድምቄ፣ አሰፉ ደባልቄ፣ ዶቅዶቄ፣ ቦሎቄ፣ አረቄ እና ወዘተ። የጎዳና ተዳዳሪ ልጆች መለስ ነው አዲስ አበባን የቆረቆራት (ወይም ከንቲባዋ መለስ ነው) ሲሉ፣ የጥበቃ ሰራተኞች "ማን ነበር? ይገርማል!" በማለት አለማወቃቸውን አሳውቀዋል። ሃይለማርያም ደሳለኝ፣ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ እና ኩማ ደመቅሳም ያሉም አሉ። ይህ እንግዲህ የአዲስ አበባ ከተማ ነው። የኢትዮጵያ ዋና ከተማ። መረጃ … [Read more...] about ሁለት ጥያቄ ብቻ አለን?
“የኤርትራ ምሽት” ለስደተኞች ደራስያን
ካንድ አሰርት ዓመታት በላይ አባል ሁኜ የቆየሁበት ኖርዌጂያን ፔን (Norsk PEN/N0rwegian PEN) የሚያከናውናቸው የተለያዩ ተግባራት አሉት፡፡ ከነዚህም አበይት ትግባራቱ መካከል በያገራቱ ያሉ እህት ማህበራትን መታደግና ለስደተኛ ደራስያን የከተሞች የጥገኝነት (By Forfatter) መብትን ማሰጠት ነው፡፡ ሥራቸውም እንዲታተምና ለሕዝብ እንዲደርስ ጥረት ያደርጋል፡፡ በእስር ላይ የሚገኙ የሌሎች አገር ደራስያንንና ጋዜጠኞችን ማሰቢያ ምሽቶችን በየጊዜው ያዘጋጃል፡፡ ከዚህ ቀደም የማሰቢያ ምሽት ከተዘጋጁላቸው ጸሐፍት መካከል እውቁ ጸሐፊ ኢትዮጵያዊው እስክንድር ነጋና ስዊድናዊ/ኤርትራዊው ዳዊት ይስሃቅ ይገኙባቸዋል፡፡ እናም ኖርዌጂያን ፔን ባለፈው ሐሙስ ጥቅምት 25 ቀን "የኤርትራ ምሽት" የተሰኘ የምሽት ፕሮግራም አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ይህ ምሽት ኤርትራ ወስጥ ያለውን የሰብአዊ መብት … [Read more...] about “የኤርትራ ምሽት” ለስደተኞች ደራስያን










