• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለሌባ ባለሥልጣናት መጦሪያ ቤት?

November 12, 2015 12:26 am by Editor 1 Comment

በ1967 የወሎ ሕዝብ በድርቅ ሲረግፍ ንጉሱ ለልደታቸው ከእንግሊዝ አገር በመጣ ኬክና ከእስኮትላንድ በተጫነ ውስኪ ይራጩ ነበር የሚል ዜና ደርግ ሲያስነግር አገሪቷ በሰላማዊ ሰልፍ ቀውጢ ሆነች። ይህም የቀዳማዊ ኃይለስላሴን አገዛዝ ለመገርሰስ ግብዓት ሆነ።

በ1977 የትግራይና የወሎ ሕዝብ በረሃብ ሲረግፍ ደርግ አስረኛ የልደት በአሉን ለማክበር ከኮሪያ ባስመጣው ርችት ታጅቦና አገሪቷን በቀለም አዥጎርጉሮ ያረግዳል የሚል ዜና ሲያስተጋባ ምእራባውያን ለሕወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ እርዳታና ይሁንታ ሰጡ። ይህም ለደርግ መውደቅ የራሱን አስተዋጽኦ አበረከተ።

በ2008 ድርቅ አስር ሚሊዮን የሚሆን ወገናችንን ሲያጠቃ ኢህአዴግ ሰፋ ብላ የድርጅቶቿን ልደት በሚሊዮን በሚቆጠር ብር እያከበረች ነው።

ይህ ሁሉ ወገን በሚራብበትና በሚቸገርበት አገር ውስጥ ከሰሞኑ የተነገረው ዜና ደግሞ ጆሮ ጭው ያደርጋል።

“ጡረታ ለሚወጡ ስድስት ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣናት በመቶ ሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር (እያንዳንዳቸው ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ) መጦሪያ ቤቶች ተገንብተው እየተጠናቀቁ ነው” የሚል ዜና ተነገረ።

እነዚህ ቤቶች ለባለስልጣኖቹ በስጦታ መልክ የሚተላለፉት ሲሆኑ ሊሸጡት ወይም ሊለውጡት ይችላሉ ተብሏል።

ሃላፊው አቶ ተክለጻዲቅ ተክለአረጋይ (አቡነአረጋይ) ለሸገር ሬድዮ እንደተናገሩት አገራችን እነዚህን ቤቶች ለባለስልጣኖች መገንባቷ ከአፍሪካ አንደኛ ያደርጋታል ብለዋል። የመዋኛ ገንዳ (ስዊሚንግ ፑል) ያላቸው እነዚህ ቅንጡ ቤቶች የሚገነባላቸው ባለስልጣኖች ተለይተው መታወቃቸውን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ከጠቅላላ ሕዝቦቿ ውስጥ ከ2 ፐርሰንት በታች ለሆኑ አዛውንት ሕዝቦቿ የጡረታና የማህበራዊ ዋስትና የሌላት አገር ብትሆንም በስልጣን ዘመናቸው በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ለዘረፉ ሌባ ባለስልጣኖቿ ግን ቅንጡ መጦሪያ ቤት የምትገነባ አገር ሆናለች።

አንድ ቤት በ25 ሚሊዮን ብር ተገንብቶ በስጦታ ሲታደል ሕዝቡ ተጠይቋል?

የዜጎችን ኑሮ ትርጉም ባለው መልኩ ለውጠው ቢሆን ኖሮ መጦሪያ ቤት መውሰዳቸው አያስፈርድባቸውም ነበር።

ሆኖም ግን እውነታው:-

* ጧሪ ቀባሪ ያጡ ሽማግሌዎች በየመንገዱ ወድቀው በሚለምኑበት አገር

* መንግስት አንድ መጠለያ ጣቢያ ሰርቶ አዛውንቶችን በማይጦርበት አገር

* በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች እየተራቡ ባለበት አገር

* በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተበድረው ኮንዶሚኒየም ለመግዛት ለአመታት ሰልፍ በሚጠብቁበት አገር

* ወጣቶች በጅምላ አገራቸውን ትተው በሚሰደዱበት አገር

* በድህነቷ የአለም አገሮች ውራ በሆነች አገር

ሰርቀው የሰሩትን ቤት በሚሊዮኖች ለሚያከራዩ ሞሳኝ ባለስልጣኖች ከዜጎች ጎሮሮ ላይ ነጥቆ የተንጣለለ መጦሪያ መገንባት ምን ማለት ይሆን?

በርካታ ገንዘብ ሰርቀው ላልጠረቁ ባለስልጣናት ተጨማሪ ቤት ማደል ምን ያህል ነውር መሆኑን ያውቁት ይሆን?

ከመንግስት ባለስልጣናት እጃቸው በሙስና ያልተጨማለቁ ካሉ ቢሰጣቸው አይከፋም ነበር።

ሆኖም ግን እውነታውን እነሱም ያውቁታል፤ እኛም እናውቀዋለን።

(ጽሁፉ ከነፎቶው ከYona Bir ፌስቡክ የተወሰደ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Shacka says

    November 12, 2015 06:00 pm at 6:00 pm

    The true it hurts. Let me add another fact.
    Tele me which poor country in the world multiply poor Human.Since Dergee thrown 60,000,000 poor people’s was born.Th hat is very scary numbers.The German population for 100 years it been the same no plus or Minus

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule