ቦሳሶ፣ ሶማሊያ ቦሳሶ በገልፍ ባህረ ሰላጤ ደቡባዊ ክፍል፣ሶማሊያ ጠርዝ ላይ የምትገኘው ከተማ፣ ካርታ ላይ ሲመለከትዋት፣ ያፍሪካ ቀንድ ላይ የተቀመጠች ዝምብ ትመስላለች። አፈ ታሪክ ስለከተማዋ አሰያየም እንዲህ ይላል። ቦሳሶ የቀድሞ ሥያሜዋን ያገኘችው ካንድ ታዋቂ ነጋዴ ሥም ነበር - ባንዳር ቃሲም ከተባለ ነጋዴ። ቃሲም ከተማ እየተባለች ትታውቅም ነበር። ነጋዴው፣ ባንዳር ቃሲም ደግሞ እጅግ በጣም የሚያፈቅራት ቡሳስ የተባለች ግመል ነበረችው። ሥለዚህ ከተማዋ ከጊዜ በኋላ በቃሲም ተወዳጅ ግመል ቡሳስ ተብላ ተሰየመች። እያደር ከቡሳስነት ወደ ቦሳሶ ተቀየረች። አለምሰገድና ባለቤቱ ምህረት፣ ምህረትያንድ አመት ልጃቸውን አቅፋ፣ ከቦሳሶ ተነስተው ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ማሬሮ ገብትዋል። ማሬሮ ገደላማ ናት። ካርቶን አንጥፈው የሚቆረቁረው መሬት ላይ ተቀመጡ። አለምሰገድ ለራሱና ለምህረት … [Read more...] about ሥደት
ሥደት
ንቧ ድፍት ኣለች
እንደው ባለፈው አመት ህወሓት 40ዋን ስታወጣ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ እንዳደረገች የምታስታውሱት ነው። የዲያስፖራ ቀን በትግራይ ሲከበር 200 ሚሊዮን ብር ወጪ፣ የአርቲስቶች ጉብኝት፣ የከተሞች ቀለሞች መቀባት፣ የዜሮ አምፑል መብራቶች (ህዝቡ ዜሮ አምፑል መንግስት ያለው)፣ የካኪ ልብሶች፣ ድግሶችና ግዢዎች ወጪ ከ2 ቢሊዮን እንዳወጣች በወቅቱ የተገለፀ ነው። በወቅቱ የ38 ሚሊዮን ኩንታል ከክረምት፣ 75 ሚሊዮን ኩንታል ደግሞ ከመስኖ እርሻ እህል ተመረተ ብለው የተተረተሩበት ዓመት ነበር። እያንዳንዷ ካድሬ፣ ልማታዊ ጋዜጠኛ፣ የሊግ፣ የማህበራትና የአንድ ለ አምስት ኔትወርክ መሪ ሁላ አካኪ ዘራፍ እያለች የመለስ ራዕይ ተሳካ እያለች ስታሽካካ ነበር። እውነት እንኳን ድሃ ድህነት የሚል ቃልም ድራሹ የጠፋ አስመስለውት ነበር። ዳሩ ግን ያሁሉ ፕሮፖጋንዳ 4 ወር ሳይቆይ ለአለም ማህበረሰብ … [Read more...] about ንቧ ድፍት ኣለች
ሻምበል ሞገስ ወልደሚካዔል
በግልጽ መታወቅ ያለበት የግለሰቡ ማንነትና ያደረገው አስተዋፅዖ ዓመቱ ፲፱፻፷፫ ነበር። በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ፤ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ነበርኩ። በዚያ ጊዜ ከአራት ኪሎ ወደ ፒያሳ በሚወስደው መንገድ፤ በስተግራ ከነበረው የፋሲካ ሆቴል፤ ከሆቴሉ በስተሰሜን ገባ ብሎ በረባዳው በኩል፤ ተከራይቶ የሚኖር፤ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር ነበር። ይህ መምህር አቶ ክብረት ተስፋሁን ይባላል። የሻምበል ሞገስ ወልደሚካዔል የናቱ ታናሽ ወንድም ነው። አራት ሆነን ምሳ ስንበላ፤ ሞገስና እኔ በዩኒቨርሲቲው የምናደርገው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃመወያየት ጀመርን። ለኮንግሬስ ( የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማኅበር - አዩተማ University Students Union of Addis Abeba – USUAA - ኡዙዋ) የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን … [Read more...] about ሻምበል ሞገስ ወልደሚካዔል
በስዊድን ለአርበኞች ግንቦት ሰባት መርጃ ገንዘብ ተሰበሰበ
በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም ለአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ መርጃ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ኦክቶበር 31 -2015 (ጥቅምት 20 - 2008 ዓ.ም) ተደረገ። በዝግጅቱ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ተገኝተዋል። በቦታው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ አበበ ቦጋለ የውጪ እንቢተኝነት ሊቀመንበር እና አቶ ቸኮል ጌታነህ የንቅናቄው ከፍተኛ አመራር ናቸው። ዝግጅቱ ረፋዱን 14፡00 ሰዓት የተጀመረ ሲሆን አቶ ጌታሁን ማሬ የዝጅቱ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ የስዊድን የአርበኞች ግንቦት ሰባት የስራ አስፈጻሚ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ ዘለሌ ፀጋ ሥላሴን ስለዝግጅቱ ገለጻ እንዲያደርጉና ዝግጅቱንም እንዲመሩ ጋብዘዋል። አቶ ዘለሌ በበኩላቸው የከተማው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ያለበትን ሁኔታ ገልጸው እንግዶቹንም በማስተዋወቅ አቶ አበበ ቦጋለና አቶ ቸኮል … [Read more...] about በስዊድን ለአርበኞች ግንቦት ሰባት መርጃ ገንዘብ ተሰበሰበ
የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!
የብላቴናው መሀመድን እናት እርዳታ አድራጊ ወገኖቸ የቻልኩትን እርዳታ ለመሰብሰብ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ስልክ ተደወለልኝ። አነሳሁት፣ ከሰላምታ በኋላ "ጠፋህ? የት ነው ያለህ?" ከሚለው አጭር የተለመደ የሰላምታ ማጀቢያ በኋላ ወዳጀ ወደ መልዕክታቸው ገቡ ... "አንተ ነብዩ የት ጠፋህ?" ሲሉ ደገሙና ስመለጥፋቴ ጠይቀውኝ ሲቀጥሉ "ናና አንድ እህት ከጅዳ ቆንስል በር ወድቃለች፣ ጸሀይ እየደበደበ አድክሟታል! እነሱ (የቆንስል ሰዎች ማለታቸው ነው) ቢነግሯቸው አይሰሙም። ሌላም ሶስት እህቶች ከቆንስሉ አጠገብ ካለው ንጉድ ፉአድ ሆስፒታል ያለ ጠያቂ ተኝተዋል። ጎብኟቸውና ችግራቸውን ተረዱ ወይ መፍትሄ ፈልጉ ወይ ወደ ሀገር ስደዷቸው ብል የሚሰማ የለም! አንተን ከሰሙህ ናና እያቸው!" ብለው ቁጣ የተቀላቀለበት መልዕክት አስተላለፈውልኝ ተጣድፈው ስልኩን ዘጉት ... ! የእኒህ ወንድም … [Read more...] about የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!
ደሳለኝ ደበረኝ
የኢቢሲ “ጋዜጠኛ ሚሚ ስብሃቱ” “መንግሥት ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። እነዚህ ከባባድ ኢንቨስተሮች ምርቱን በሞኖፖል ከያዙት፣ ይኸ ነገር በሃገራችን “እየተሰፋፉ የመጡትን መካከለኛ ኢንቨስተሮች” ሊያፈናቅላቸው ይችላል ተብሎ ይሰጋል። ይህንን እንዴት ይመለከቱታል። ¼ኛ ጠ/ሚ ደሳለኝ “ትክክል ነው ልማታዊው መንግሥታችን ታላላቅ የኢንዱስትሪ ፓርኮችን እየሰራ ለትላልቅ ኢንቨስተሮች ይሰጣል። ይህን ነገር እኮ እኛ የፈለሰፍነው አይደለም። ከሌሎች ሃገሮች ተመክሮ (ኮርጀን - ባግባቡ ወይም ባላግባቡ) ወስደን፣ ለምሳሌ ከደቡብ ኮርያ፣ ቬትናምና ቻይና አይተን ነው። የኢንዱስትሪ ፓርኮችን የምንሰራበት ምክንያት ኢንቨስተሮች እንዳይቸገሩ ነው። ለምሳሌ መብራት እንዳይቋረጥባቸው። እነሱ ለምን ይቸገሩ? እ? ጨርቁን ቀለም እየቀቡት እያለ መብራት ቢቋረጥ እኮ … [Read more...] about ደሳለኝ ደበረኝ
Me, my country and corruption
Have you seen a movie titled ”me, myself and Irine” or ”me and Marley”? Both are my favorite movies. When I decided to write article about corruption what it does to me and my country. The title concept of these movies clicked to my mind. I borrowed the concept, convinced it will explain the theme of my article. In this article I will try to discuss the harm corruption can cause to an individual that is me and my country. I will also try to shade some light on the issue from the global … [Read more...] about Me, my country and corruption
የዶ/ር አክሊሉ ሐብቴ አቋም ሰውን ግራ አጋባው
ዶ/ር አክሊሉ ሀብቴ አቋማቸውን በየጊዜው በመቀያየር፡ የዋሽንገትን ዲሲ ቅድስት ማርያምን ወደ አቡነ ማትያስ ጉያ ለመክተት ከፈለጉት ሰዎች ጋራ መስማማታቸው ሰውን ግራ አጋባው። በትምህርት፡ በሽምግልና፤ የዩንቨርሲቲ ፕሬዝደንት ሆነውም፤ የምሁራንን ጭንቅላት በመምራት እና ፤ ጥራት ባላቸው መምህራን በሚቀርብላቸው የእውቀት ትምህርት እንደ ሰንጋ ፈረስ የሚቁነጠነጠውን የተማሪ አዕምሮ በመግራት ሰፊ ልምድ አላቸው የሚባሉት ዶክተር አክሊሉ በዚህች ጦማር ከዘረዘርኳቸው ሰዎች ጋራ ራሳቸውን ደምረው ራሳቸውን ማስመዘናቸው የራሳቸውን ሁለንተናነት በማዋረድ ተመልካቹን ግራ እያገቡ ነው። ይልቁንም ምሳሌነታቸው ለሚዛንነት ከሚጠቀስላቸው በኢትዮጵያ ታሪክ እና በትውልድ ጭንቅላት ላይ እንደ ወርቅ አእማድ ሲፈልቁ ከሚኖርት አባቶቻችን ጋራ መደመር በተገባቸው ነበር። የወርቅ አእማድ ያልኳቸው አባቶቻችን፤ … [Read more...] about የዶ/ር አክሊሉ ሐብቴ አቋም ሰውን ግራ አጋባው
Genocide Committed Against the Amhara in Metekel, Ethiopia
1. Background/Introduction This report has been compiled on the recent incidents of genocide in Wembera and Bulen district (Woredas) of Metekel Zone of Benshangul-Gumuz Regional State in Ethiopia. The report pinpoints and underscores the outrageous atrocities committed by members of the Gumuz ethnic group against Amaras with the full knowledge and encouragement of Tigrean People’s Liberation Front (TPLF), the current Oligarchy ruling Ethiopia. The cruel and inhumane crimes are another sad … [Read more...] about Genocide Committed Against the Amhara in Metekel, Ethiopia
የኮንትሮባንድ ንግድ እንደ ተቋም
በሻሸመኔ አካባቢ የኮንትሮባንድ ንግድ ተቋማዊ ቅርጽ መያዙን የሚያሳይ መረጃ ጠቆመ፡፡ ሌሎች በኮንትሮባንድ ንግድ እንዳይሳተፉ የሚከለክለው ሕግ የሚጸናባቸው ከህወሃት ራቅ ያሉ የኅብረተሰብ ክፍሎች መሆናቸው ድርጊቱን “ማስመጥ” አሰኝቶታል፡፡ ዜጎችም “የኮንትሮባንድ ንግድ ትርጉሙ ምን ይሆን?” እያሉ ነው፡፡ የኮንትሮባንድ ንግድ በህጋዊነት በተለይ የሚፈጸመው ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም ላለፉት 25 ዓመታት በግፍ እየገዛ ባለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ህወሃትና በአፍቃሪዎቹ መሆኑን በማረጋገጥ የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በዓይን ምስክርነት የታዘቡትን በፎቶ የተደገፈ መረጃ ልከውልናል፡፡ ዜናውን እማኝ ዘጋቢው ይላኩት እንጂ በድፍን አገሪቱ ህወሃቶች፣ የህወሃት አገልጋዮች፣ የህወሃት ሽፋን ሰጪዎች፣ ነባር ተጋዳላዮች፣ ተላላኪዎች፣ ወዘተ በዚህ ሥራ እንዲሰማሩ … [Read more...] about የኮንትሮባንድ ንግድ እንደ ተቋም










