• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከ9ሺህ በላይ ፈላሻ ሙራዎች ወደ እስራኤል ሊጓዙ ነው

November 16, 2015 11:13 am by Editor Leave a Comment

ከ25 ዓመታት በላይ ከኢትዮጵያ ወደ እስራኤል ለመጓዝ እየጠበቁ ያሉ በተለየ ፈላሻ ሙራ ተብለው የሚጠሩት ቤተ እስኤላውያን ወደ “ቅድስት አገራቸው” እንዲመጡ የእስራኤል መንግሥት ወሰነ፡፡ እስኤል እንደገቡም የአይሁድ እምነትን በተመለከተ የተሃድሶ ትምህርት እንደሚሰጣቸው ተመልክቷል፡፡

በእስራኤል ያሉ እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ የዜና ምንጮች እንደዘገቡት የጠ/ሚ/ር ቢኒያም ኔታንያሁ መንግሥት ውሳኔውን ያስተላለፈው እሁድ ዕለት በሙሉ ድምጽ ነበር፡፡ ይህ የአሁኑ ውሳኔ ከመሰጠቱ በፊት የዛሬ ሁለት ዓመት እስራኤል ምንም ዓይነት ዜጋዋ በኢትዮጵያ እንደሌለ ይፋ ነበር፡፡ “ዛሬ ጠቃሚ ውሳኔ አስተላልፈናል” በማለት የተናገሩት ኔታንያሁ ውሳኔው በእስራኤል እየኖሩ ከቤተሰቦቻቸው ለተለያዩት ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሰጪና ጠቃሚ እንደሆነ በላኩት መግለጫ አመልክተዋል፡፡

ከዚህ በፊት እስራኤል “የተስፋዋ አገር ዜጎቿን” ከኢትዮጵያ ያስወጣች ሲሆን መጨረሻ ላይ የቀሩት በተለይ ፈላሻ ሙራ የሚባሉት በ18ኛውና በ19ኛው ክፍል ዘመናት ወደ ክርስትና እንዲቀየሩ የተደረጉት ናቸው፡፡ ፈላሻ ሙራ የሚለው ስም የአይሁድን ሕግጋት የማይከተልና በግድ ወይም በፈቃደኝነት ወደ ክርስትና የተቀየረ የሚወክል እንደሆነ Jewishpress.com ባወጣው ዜና ላይ ጠቁሟል፡፡

የኤርትራ ክፍለ ሃገርን ጨምሮ ከጎንደር የመጡት 9ሺህ አንድ መቶ የሚሆኑት አይሁድ ተብለው ስለማይጠሩ እስራኤል እንደደረሱ በአክራሪ የአይሁድ ዕምነት መምህራን የተሃድሶ ትምህርት እንዲሰጣቸው የተወሰነ መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚ/ሩ ማስታወቃቸውን የዜና ዘገባዎቹ ጠቁመዋል፡፡ ከሚሰጧቸው ትምህርቶች መካከል የአይሁድ ሕግጋት እና የጽዮናዊነት እንቅስቃሴ ታሪክ ይገኝባቸዋል፡፡ ፈላሻ ሙራዎቹ በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባና በጎንደር ይገኛሉ፡፡

ጠ/ሚ/ሩ ባወጡት መግለጫ ላይ እንደተናገሩት እነዚህ “የመጨረሻ” የተባሉት ተጓዦች በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ወደ እስራኤል ይጓዛሉ፡፡ ለዚህ በርካታ ዓመታት ለፈጀ ውሳኔ ተግባራዊነት በአሁኑ ጊዜ የእስራኤል ሸንጎ አባል የሆኑት የኢትዮጵያ ዝርያ ያላቸው እንደራሴ አብርሃም ንጉሤ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳደረጉ በዜና ዘገባው ላይ ተመልክቷል፡፡ “ለአይሁድ ሕዝብ ይህ ታላቅ ቀን ነው” ያሉት እንደራሴው “ለሺዎች ዓመታት ኢትዮጵያውያን አይሁዶች ወደ እስራኤል ለመመለስ ሲጸልዩ ኖረዋል፤ ለዓስርተ ዓመታት ደግሞ ከቤተሰቦቻቸው ተለያይተው ሲጠብቁ ቆይተዋል፤ ዛሬ ጸሎታቸው ተሰምቷል” ብለዋል፡፡

መጽሓፍቅዱሳዊ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ኢየሱስ ክርስቶስ “ቤታችሁ የተፈታ ይሆናል” ካለ በኋላ በወቅቱ የሮም ጄኔራል የነበረው ቲቶስ (ታይተስ በኋላ አባቱን ተክቶ ቄሣር ሆኗል) ኢየሩሳሌምን ከብቦ ካሰጨነቃት በኋላ በ70ዓም ቤተመቅደሱን በማፍረስ ከተማዋን በሮም ቁጥጥር ሥር ካዋለ በኋላ የአይሁድ ሕዝብ “የእግዚአብሔር ምርጥነት” በይፋ አክትሞ ክርስትና ቦታውን ወስዷል በማለት አንዳንድ የሥነመለኮት ምሁራን ይከራከራሉ፡፡ በአይሁድ እምነት መሠረት መሲሕ ገና ይገለጣል ተብሎ ስለሚጠበቅ በምሁራኑ የሚቀርበው አስተያየት ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም፡፡

የዛሬ ሃያ ዓመት አካባቢ አስቀድመው ወደ እስራኤል የሄዱት ኢትዮጵያውያን እንደ ዜጋ የለገሱት ደም ኤችአይቪ/ኤይድስ ይኖርበታል በሚል ስጋት ለበርካታ ዓመታት ሲለግሱ የነበረው ደም ሲደፋ የቆየ መሆኑ ይፋ በተደረገበት ጊዜ ከፍተኛ ቁጣን በቤተ እስኤላውያኑ ዘንድ አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከዚያ በኋላ ሁኔታዎች ይስተካከላሉ የሚል ተስፋ የተሰጠ ቢሆንም ኢትዮጵያውያኑ ከሌሎች በተለየ በድሃ የአገሪቱ ከተሞች እንደሚሰፍሩ፤ አሰቃቂ የፖሊስ ግፍ እንደሚፈጸምባቸው፤ በዘር መድልዖ በደል እንደሚደርስባቸው በቅርብ ጊዜያት የተከሰቱት ዕውነታዎች ያስረዳሉ፡፡ ሆኖም የጠ/ሚ/ር ኔታኒያሁ መንግሥት ችግሮችን እንቀርፋለን፤ ሁኔታዎችን እናሻሽላለን በማለት በተደጋጋሚ ቃል ገብቷል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule