“Individuals can be penalised made suffer …even killed but democracy is a destiny of humanity which cannot be averted, it can be delayed but not defeated. (Prominent Ethiopian Journalist Eskinder Nega sent letter from Kality) Source: Pen America. We have been witnessing for the last 25 years, Tigray People’s Liberation's Front (TPLF) domination of the political, economic and social sphere in the country. Power is in the hands of the few and dominated by the secretive police force, and … [Read more...] about Ethiopia on the transition from total dictatorship: the role of individuals and organisations
Opinions
የኔ ሃሳብ
INTERNATIONAL ALERT REGARDING ETHIOPIA TO WESTERN POLICY MAKERS, DONORS AND STAKEHOLDERS
Open letter to the Western Governments and Donor Countries concerning the deteriorating situation of human rights and political instability in Ethiopia that is shifting from bad to worse day after day. Your Excellency, The State of Emergency declared by the ruling ethnic apartheid regime of the TPLF/EPRDF, which is an attempt to enforce draconian measures to repress the emerging vocalization of discontent by the people of Ethiopia, will undoubtedly fail, with unknown results. Some of these … [Read more...] about INTERNATIONAL ALERT REGARDING ETHIOPIA TO WESTERN POLICY MAKERS, DONORS AND STAKEHOLDERS
“ባንዶች ሀገራችሁን እንደጎዳችሁ ዛሬ ደግሞ የምትክሱበት ጊዜ ነው” ጄኔራል ለማ ገ/ማርያም
ጄኔራል ለማ ገብረማርያም የኢጣልያ ፋሺሽቶች ኢትዮጵያን በወረሩበት ዘመን በጽንዓት ተዋግተው ከነበሩት የኢትዮጵያ አርበኞች አንደኛው ነበሩ። በፈጸሙት አኩሪ ትግል ኢጣልያዊ ስለ መማረካቸውና አሁን ደግሞ ሕይወተ ሕልፈት ያጋጠማቸው መሆኑን፤ Ethiopian Media Forum የዘገበውን ከዚህ በታች መመልከት ይቻላል። ጄኔራል ለማ ለሐገር ነጻነትና ክብር ካከናወኑት እጅግ የሚያኮራ ተግባር ውስጥ አብሮ ሊደነቅ የሚገባው አንዱ አስተዋጽኦዋቸው ቫቲካን በፋሺሽቱ ወረራ ዘመን ለፋሺሽት ኢጣልያ ላከናወነችው ያልተቆጠበ ድጋፍ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ በማመልከት ከዚህ ጋር የተያያዘውን ግልጽ ደብዳቤ ማስተላለፋቸው ነው። (ደብዳቤውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) በልጅነታቸው ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሽምግልናቸው፤ በ97 እድሜያቸው ጭምር ጀኔራል ለማ ለሐገራቸው ያልተቆጠበ ጥረት ያበረክቱ … [Read more...] about “ባንዶች ሀገራችሁን እንደጎዳችሁ ዛሬ ደግሞ የምትክሱበት ጊዜ ነው” ጄኔራል ለማ ገ/ማርያም
ግልፅ ደብዳቤ ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ
ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ዋይት ሐውስ 1600 ፔንሲልቫንያ አቬኑ ሰሜን ምዕራብ ዋሽንግቶን ዲሲ 20500 የተከበሩ ፕሬዚደንት ኦባማ፤ ይህንን ደብዳቤ የምጽፍሎት በኢትዮጵያ ውስጥያለውን የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ ላሳውቆት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ተጎዳን፣በደል ተፈጸመብን በማለት የሚያሰማውን አቤቱታ፣ ህጋዊ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሰልፎችን ሁሉ መንግሥት ከማዳመጥ ይልቅ ጉልበትንና ኃይሉን ሁሉ እንደሚጠቀም ያውቃሉ ብዬ አምናለሁ። ይህ ሁኔታ ባግባቡ ካልተያዘ በሀገሪቷና በአካባቢው ሁሉ ያልተጠበቀና አስከፊ ሁኔታ ሊከሠት ይችላል።የኢትዮጵያና የዩናትድ እስቴት አሜሪካ ግንኙነት ከ1903 ጀምሮ እንደሆነ ይታወቃል። ስለዚህ የንግድና የወዳጅነት ውል ተፈራርመው ኢትዮጵያም ጥብቅ ወዳጅ ተብላ ትታወቅ ነበር። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አብላጫውን የአሜሪካን ረድኤት እንድታገኝምሆኗል። በአጸፋው … [Read more...] about ግልፅ ደብዳቤ ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ
My two cents to break the deadlock between the Oromos and Unity Camps
Researches recognized that many change agendas fail not because of resistance to change. It is due to wrong responses to resistances. Many people tend to think that all resistances are one and the same. And hence, they use the same response to all resistances. To give you a quick background, experts in the field agree that there are three major levels of resistances to change. People resist at Level 1 since they don’t understand the change at all. Those who resist at Level 2, they capture the … [Read more...] about My two cents to break the deadlock between the Oromos and Unity Camps
መንፈሳዊ ወኔና ሥልጣን
ባለሥልጣኖቻችን ሚስቶቻቸውንና ልጆቻቸውን በጣም የናቋቸው ይመስላል፤ ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቀውን ሁሉ ያውቃሉ፤ የኢትዮጵያን ቴሌቪዥን ያያሉ፤ የኢትዮጵያን ራድዮ ይሰማሉ፤ ባሎቻቸውና አባቶቻቸው የዛሬ ሳምንት የተናገሩትን ረስተው፣ ወይም ክደው፣ ወይም ዋሽተው ተቃራኒውን ሲናገሩ መሸማቀቃቸው አይቀርም፤ እንዲህ ያለው የንግግር መገለባበጥ የእምነት መገለባበጥን፣ የማሰብ ችግርን፣ የመንፈስ ልልነትን ያሳያል፤ ታዲያ ሚስቶችና ልጆች እየተሸማቀቁ አካላቸውም ነፍሳቸውም ሲያልቅ ለባለሥልጣኖቹ አይታወቃቸውም? ወይስ የቤተሰብ አባሎች ጠባይ እየሆነ ሽታዬ ሽታዬ እየተባባሉ ነው? አንዳንዶች ባለሥልጣኖች ወንበሩ ላይ የወጡት እግዚአብሔርን ሳይይዙ ነው፤ አንዳንዶቹ ደግሞ እግዚአብሔርን ይዘው ወንበሩ ላይ ይወጡና እግዚአብሔርን ከተቆናጠጡ በኋላ እግዚአብሔርን ከውስጣቸው የሚያስወጡት … [Read more...] about መንፈሳዊ ወኔና ሥልጣን
ኢትዮጵያ ትጠየቅ!
ነገር ቢበዛ በአህያ አይጫንም። ስለዚህ ነገሬን አጠር አድርጌ ላቅርብ። እነሆ! የኢትዮጵያ ማንነት መገለጫው በዋነኛነት ምንድነው? ሕዝቡ ነው። ታዲያ በሕዝቡ ስም (ኢትዮጵያ) ጥላ ስር መሪዎቻችን ሁሉ የማይሰባሰቡት ለምንድነው? የታሪክ እስረኛ ሆነን በር በሌለው ጨለማ እስር ቤት ውስጥ በመታለል ቁጭ ስላልን። ኢትዮጵያን መነሻ ሳናደርግ ኢትዮጵያ መድረሻ እንድትሆንልን ተመኝተን ጉም ስንጨብጥ። ክልላችንን (አጥሩን) አፍርሰን እንዳንያያዝ አጥሩ ጎልያድ ሆኖብን ፍርሀት ስለሞላብን። ሁሉም የሚስማማበት ጉዳይ ምንድነው? የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉም ብሔረሰብ የጭቆና ሰለባ ሆኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉም ብሔረሰብ ደግና ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሁሉም ብሔረሰብ የተደባለቀና አብሮ ለዘመናት የኖረ ነው። … [Read more...] about ኢትዮጵያ ትጠየቅ!
የኢሬቻው ጭፍጨፋና ቀጣዩ ትግል
እስካሁን አልበገር ባለውና ከሁሉም በላይ ደግሞ ለህልውናው የተማመነበት የከፋፍለህ ግዛ ፖለቲካው በህዝቦች ወንድማማችነት መንፈስ ከሽፎበት ብርክ በብርክ የሆነው የወያኔ አገዛዝ ከአንድ አመት በላይ በሰላማዊ ህዝብ ላይ ሲያወርድ የቆየውን አመጽ ቀጥሏል፡፡ በያዝነው ሳምንት በሰላም የኢሬቻ ባህላዊ በአላቸውን በሚያከብሩ ኦሮሞዎችና ሌሎች በአሉን ለማክበር በስፍራው በተገኙ ሌሎች ዜጎች ላይ እስካሁን ከታዩት ግፎች ይበልጥ ዘግናኝ የሆነ ጭፍጨፋ አካሂዷል፡፡ በዚህ አሰቃቂ ግፍ በመቶ የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወት አልፏል፡፡ በሽ የሚቆጠሩ እናት አባቶች ልጆቻቸውን፣ ጨቅላ ህጻናትና ታዳጊዎች እናት አባቶቻቸውን፣ ወንድም እህቱን እህት ወንድሟን አጥተው ለአስከፊ ሰቆቃ ተዳርገዋል፡፡ ድርጅታችን ይህንን አሰቃቂ ድርጊት በጥብቅ እያወገዘ ለተሰውት ወገኖች ዘመዶችና ወዳጆች መጽናናትን ይመኛል፡፡ ይህ ስርአት … [Read more...] about የኢሬቻው ጭፍጨፋና ቀጣዩ ትግል
እውነትም መክለፍለፍ
ጎልጉል "የዖሮምያ ሰነድ አዲሱ ቃልኪዳን" በሚል ርእስ ባወጣው ፅሁፍ የመክለፍለፍ ፖለቲካ ጎጂ አዝማሚያ በግልፅ መጠቆሙን ሳነብ እኔም "እውነትም መክለፍለፍ" ልል አማረኝ፤ እውነትም መክለፍለፍ። መቼም በኢትዮጵያ የለውጥ ታሪክ ውስጥ ልሂቃን ፖለቲከኞችና ህዝብ ሆድና ጀርባ ከሆኑ ከ40 አመት በላይ ሆኗል። ህዝብ ለሃቀኛ ለውጥ ደሙን ያፈሳል፤ ብልጡ ልሂቅ ስልጣን ይወርሳል። ህዝብ ለጋራ አላማ ይደማል፤ ልሂቅ ለግል ጥቅሙ ይሿሿማል። ህዝብ ለለውጥ ይደማል፤ ብልጣብልጥ ፖለቲከኛ ስልጣን ይቀማል። ህዝብ ላንድነት ይጮሃል፤ ህዝብ እወክላለሁ ባይ ፖለቲከኛ ለልዩነት ይሰራል። ህዝብ ደማችን አንድ ነው በሚል ሰልፉን ሲያደምቅ ለዝቅም የሚማስነው ፖለቲከኛ ለጠብ ይሮጣል። በሰሞኑም የሚታየው ይህንኑ የሚመስል ነው። ሞት አይፈሬዎቹ የህዝብ ልጆች ከጨካኝ ባለክላሾች ጋር በባዶ እጃቸው … [Read more...] about እውነትም መክለፍለፍ
“ህወሃት በእስረኞች ላይ አጥንት የሚያመነምን መርዝ ይጠቀማል” እማኝ
በኢትዮጵያ እስረኞች አጥንትን ቀስ በቀስ በሚያፈርስ መርዝ እየተጠቁ መሆኑን ታውቁ ኖሮዋል? ከጥቂት ዓመታት በፊት የግንቦት ሰባት መሪዎች እና አባላት መታሰራቸው ይታወሳል። ብዙዎቹ ቃሊቲ የሚገኘው እስር ቤት ነበሩ። በእስር ቤት እያሉ በደረሰባቸው ያልታወቀ ሕመም ምክኒያት ሕይወታቸውን ያጡ መሪዎችም ነበሩ።ታዲያ አንዴ ከሜክሲኮ ወደ ሃያሁለት በታክሲ ተሳፍሬ ስሔድ በግምት የሃያ ዓመት ዕድሜ ያለው ልጅ ታክሲው ውስጥ ገብቶ አጠገቤ ተቀመጠ። ታክሲው ሞልቶ መሔድ ሲጀምርም ወንድሜ ይቅርታህን የታክሲ ትከፍልልኛለህ ብሎ ጠየቀኝ። ዞር ብዬ ያየሁት ይህን ሲል ነበር። ድንጋጤ እና መሸማቀቅ ይነበብበት ነበር።ልቤ በጣም አዘነለት። ምን ሆነህ ነው? ከዬት ነው የምትሔደው፤ወዴት ነው የምትሔደው ብዬ ጠየኩት። እርሱም ከቃሊቲ እስርቤት ዛሬ መለቀቄ ነው አለ። ለምን ታሰርክ እንዴትስ ተለቀቅህ ስለው … [Read more...] about “ህወሃት በእስረኞች ላይ አጥንት የሚያመነምን መርዝ ይጠቀማል” እማኝ










