". . . እንዲህ ያለ ሰው አይተን አናውቅም የሚለው ንግግር አንዱን ከሌላው ጋራ በተመሳሳይ መስፈርት አነጻጽሮ ልቆ የተገኘውን ከፍ አርጎ ለማቅረብ ነው። ይህን ቃል ካፋቸው አውጥተው የተናገሩት አባ ማትያስ ናቸው። የተናገሩትም ለብጹዕ አባታችን ፓትርያርክ ተክለ ሃይማኖት ነው። ምን ጊዜና እንዴት ተናገሩት? አቅራቢውስ ይህን ምስክረነት ለመግለጽ ያስቻለው በዚህ ወቅት የት ነበር? የሚሉ ጥያቄዎች ባንባቢ ህሊና ላይ መፈጠራቸው አይቀርም። "ለምስክርነት ያበቃኝን ዝርዝር በዚህች ጦማር ለማቅረብ ሰአት ወስኖኛል። አስፈላጊ ከሆነ ዝርዝር ሀተታውን ከዚህች ጦማር ቀጥየ ማቅረብ እችላለሁ። . . ." (ሙሉውን ጥናታዊ ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about አባ ማትያስ “እንዲህ ያለ ፓትርያርክ አይተን አናውቅም”
Right Column - Primary Sidebar
የዶ/ር መሠረት ቸኮል አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
በቅርቡ ያረፉት ዶ/ር መሠረት ቸኮል ላለፉት 8 ዓመታት ሲለፉባት የነበረውና የኢትዮጵያን የ100 የፕሬስ ታሪክ የሚያሳይ መጽሐፍ ለገበያ መቅረቡን ቤተሰቦቹ ገለጹ። ጥልቀት ባላቸው ትንታኔዎቹና ቀላል አቀራረቡ የሚታቀው ጋዜጠኛና መምህር ዶ/ር መሠረት ቸኮል የጻፈው ታሪካዊው መጽሐፍ “The Quest for Press Freedom: One Hundred Years of History of the Media in Ethiopia” የሚሰኝ ሲሆን በamazon.com እንዲሁም በባርነስ ኤንድ ኖብል የመጽሐፍት መሸጫ መደብሮች እንደሚገኙ ቤተሰቦቹ ገልጸዋል። ይህ መጽሐፍ ለማስተማሪያነት ሁሉ ታስቦ እንደተጻፈ የገለጹት የዶ/ር መሠረት ባለቤት ወ/ሮ በልዩ ወደፊት መጽሐፉን በአማርኛ ለማሳተም እንደተዘጋጁም ገልጸዋል። “ዶ/ር መሠረት ይህን መጽሐፍ በአማርኛም ጀምሮት ነበር። ሆኖም ግን በድንገት ሳጨርሰው በማረፉ … [Read more...] about የዶ/ር መሠረት ቸኮል አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ
አስቸጋሪው ነገር አገርን መገንባት ነው!!
ወያኔን ማስወገድ አይደለም የሚያስቸግረው፤ አስቸጋሪው ነገር አገርን መገንባት ነው !! "We are just leaving barbarism and are still entirely at the beginning. The French, however have already gone a piece of the way and have a century`s lead in every respect.” Friedrich the Great II to Wilhelm of Prussia መግቢያ የወያኔን አገዛዝ ነፍስ ለመዝራት፣ ወይንም የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም የሚደረገውን በአንዳንድ ምሁሮች የሚነዛውን የማያስፈልግ አጻጻፍ ትተን፣ እስከዛሬ ድረስ በተለይም ብዙዎቻችንን ያሰጨነቀንና የሚያስጨንቀን፣ የቀድሞዎቹ አገዛዝም ሆነ ወያኔ ያተራመሰውን አገር እንዴት መገንባት አለብን ? የሚለው ሳይሆን፣ እሱን አስወግዶ እንዴት ስልጣን መያዝ … [Read more...] about አስቸጋሪው ነገር አገርን መገንባት ነው!!
ትውልድ ያናወጠ ጦርነት
የመጽሐፉ ርእስ.................. ትውልድ ያናወጠ ጦርነት ደራሲ.................................. ንጋቱ ቦጋለ (ሻለቃ) አሳታሚ............................... በግል አታሚ.................................. ኢንተርናሽናል ሊደርሺፕ የሕትመት ሥራ የገጽ ብዛት............................ 341 ዋጋ........................................ 55 ብር ቅኝት..................................... በአበራ ለማ ". . . የሽሬ ውጊያ ብሎም በትግራይ ውስጥ የነበረው የመንግሥት ጦር አመራር በነመጋቢ ሃምሳ አለቃ ለገሠ አስፋው ችሎታ ማነስ ምክንያት፣ ምን ያህል ተፍገምግሞ እንደወደቀ ደህና አድርገህ ገልጸህዋል፡፡ መጋቢ ሃምሳ አለቃ ለገሠ አስፋው ጀምለው በያዙት … [Read more...] about ትውልድ ያናወጠ ጦርነት
አባይ የኢህአዴግ ኤአርቲ!
Nile River, Arabic Baḥr Al-Nīl or Nahr Al-Nīl river, the father of African rivers and the longest river in the world. It rises south of the Equator and flows northward through northeastern Africa to drain into the Mediterranean Sea. Encyclopedia Britannica. በዓለማችን በግዙፍነታቸው ከሚወደሱትና አንቱ ከተባለላቸው ወንዞች መሃል የአባይ ወንዝ /Blue Nile/ግንባር ቀደሙ ነው።ከ6ሺ ኪሎሜትር በላይ ርዝማኔ ያለው የኣለማችን ግዙፉ ወንዝ በርካታ አገሮችን እያቋረጠ የሜዲትሪያንያን ባህርን ይቀላቀላል። አባይ የሚያቋርጥባቸው አገሮች ደም ስር ሆኖ በማገልገልም ላይ ይገኛል።ምንም እንኳን የአባይ ወንዝ ምንጭና የ80 በመቶ ባለድርሻ … [Read more...] about አባይ የኢህአዴግ ኤአርቲ!
ታላቅ ሕዝባዊ የስብሰባ ጥሪ
ኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል በአገራችን ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ለመምከር ቅዳሜ ጁን 22 ቀን 2013 ሕዝባዊ ስብሰባ አዘጋጅቷል። በዕለቱም የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በክብር እንግድነት ይገኛሉ። ስለሆነም በተጠቀሰው ቀን ከምሽቱ 8:00 ጀምሮ በኢየሩሳሌም ከተማ በያፎ 97 ብንያን ክላል ሕንጻ እንዲገኙና የበኩልዎን ተሳትፎ እንዲያደርጉ አስተባባሪ ኮሚቴው ጥሪውን ያቀርባል። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 054-2950990 ወይም 052-4062853 ይደውሉልን አስፈላጊውን መረጃ ልንሰጥዎ ዝግጁ ነን። አስተባባሪ ኮሚቴው … [Read more...] about ታላቅ ሕዝባዊ የስብሰባ ጥሪ
አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት!
ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡- 1ኛ - ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣ 2ኛ - መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን … [Read more...] about አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት!
ግንቦት 25 /2005/
የ ኢትዮጵያ 21ኛው ክፍለ፥ዘመን የተጀመረበት ቀን ሊሆን ይችላል! ትግሉ እንዲቀጥል፣ አንዳንድ ቁም ነገሮች… አንደኛ - በተለይም የግብጽ ወጣቶች በምን ዘይቤና ብልሃት ወደ ህዝቡ ልቦናና መንፈስ ወስጥ ሰርጸው በመግባት፣ በሰላማዊ አመጽ፣ በአልገዛም ባይነት፣ ያን እስተአፍጢሙ ድረስ የታጠቀን የሙባረክ መንግሥትን እንዴት እንዳምበረከኩ፤ (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ግንቦት 25 /2005/
በሰላማዊ ሠልፉ ሰማያዊ ፓርቲና መንግሥት እየተወዛገቡ ነው
ሰማያዊ ፓርቲ ከአንድ ወር በፊት በጠራውና ባለፈው እሑድ የተደረገውን ሰላማዊ ሠልፍ መንግሥት ሲያወግዝ፣ ሰላማዊ ፓርቲ ደግሞ የመንግሥት ውግዘት በተቃውሞ የተነሳውን ሕዝብ ከማሸማቀቅ ባለፈ የሕግ ድጋፍ እንደሌለው እየገለጸ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዝያ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. ባስተላለፈው የሰላማዊ ሠልፍ ጥሪ፣ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጐች ወጥተው ተሰተውለዋል፡፡ አራት ኪሎ ቀበና አካባቢ ከሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ ጽሕፈት ቤት መነሻውን ያደረገው ሰላማዊ ሠልፉ በአራት ኪሎ፣ በፒያሳና በቸርችል ጐዳና አድርጐ ኢትዮ ኩባ የወዳጅነት መናፈሻ ደርሶ፣ እስከ ቀኑ ስምንት ሰዓት ድረስ የተለያዩ መፈክሮችንና ተቃውሞዎችን በመንግሥት፣ በመንግሥት መገናኛ ብዙኅንና በአንዳንድ የግል መገናኛ ብዙኅን ላይ አሰምተዋል፡፡ ሠልፈኞቹ ለመንግሥት ካቀረቧቸው ጥያቄዎችና መፈክሮች … [Read more...] about በሰላማዊ ሠልፉ ሰማያዊ ፓርቲና መንግሥት እየተወዛገቡ ነው
ዶ/ር አበራ ጀምበሬ ትዝታዬና መጽሐፉ
ዛሬ ብቻ ኖረው - በዛሬ ያልቀሩ ነገንም አስበው - ለነገ የሠሩ ለራሳቸው ሳይሆን - ለህዝብ የኖሩ ግዴታ ሆነና ሞት - ቢሆን ዕጣቸው ሲበራ ይኖራል - አይጠፋም ሐቃቸው ግጥም - አስራት ዳምጠው በስድስተኛ ዓመቴ መጨረሻ ግድም አንድ ቀይ እንግዳ እቤታችን መጣ። ከናትና አባቴ ጋር ሆኜ ከሰውየው ጋር የመቀመጥ እድል አገኘሁ። ቀዩ ሰውዬ ሳቂታ ፊት፣ የሚቁለጨለጩ አይኖች፣ ሰልካካ አፍንጫና፣ የሞሉ ጉንጮች አሉት።ያም ሆኖ ሙሉ ፊቱ ስትታይ አነስተኛ ነች። ይህን ሰው ከዛን ቀን በፊት ስለማወቄ እርግጠኛ አይደለሁም። እንኳን እሱን ሌሎች አብረውኝ ያሉትንም ዝምድናቸውን ለይቼ ለመናገር እቸገራለሁ። ያን ቀን ያንን ሰው አይነ ህሊናዬን ምን እንዳበራው አላውቅም ቀረብኩት። አንድ አይነት የሚያስተሳስረን ነገር እንዳለን ገባኝ። ነፍስ ማወቅ ይሄ ይሆን? ይሄ ካልሆነ ሌላ ምንም … [Read more...] about ዶ/ር አበራ ጀምበሬ ትዝታዬና መጽሐፉ










