• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገዛዙ ለሰላማዊ ሰልፉ ዕውቅና የሰጠው ፈጽሞ አማራጭ ስላልነበረው ነው – በእኔ አመለካከት!

June 8, 2013 01:21 am by Editor Leave a Comment

ሕወሓት/ኢህአዴግ በሰማያዊ ፓርቲ አዘጋጅነት የተካሄደውን ሰላማዊ ዕውቅና የሰጠው ወድዶና ፈቅዶ ወይም ሕገ-መንግሥቱ አጣብቂኝ ውስጥ ከትቶት አልነበረም። ይልቅስ አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱት ሁለት ነገሮች ናቸው ፡-

1ኛ – ወቅታዊነት! በወቅቱ የሚካሄደውን ርዕሰ-ሃገራትና ከፍተኛ የዓለም ባለሥልጣናት (እንደ ጆን ኬሪ እና ባንኪ ሙን) በተገኙበት እንዲሁም በዓለም መገናኛ ብዙሃን እየተዘገበ በሚካሄደው የአፍሪካ ሕብረት 50ኛ ዓመት ጉባዔ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ዕውቅና መጠየቁ፣

2ኛ – መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት!!! የሰማያዊ ፓርቲና አመራሩ መደራጀት፣ ብስለት እና ቁርጠኝነት፤ ሕወሓት/ኢህአዴግ ከለመዳቸው የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች መግደርደሮች (ከይቅርታ ጋር በርካታ የከሸፉ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና አመራሮች እንዳሉም ጭምር እምነት አለኝ) የተለየ መሆኑን መገንዘቡና ፓርቲውም የተጠየቀውን ዋጋ ከፍሎ ሕገ-መንግሥቱ የሚፈቅድለት መብቱን ከደጋፊዎቹ ጋር ከማራመድ ወደኋላ እንደማይል (that those guys were not bluffing) እየመረረው መረዳቱ።

“መንግሥት” አማራጭ እንዳልነበረው ሌላው ተጨባጭ ማስረጃ ደግሞ በሚያስደንቅ ቅንጅት፣ ኅብር፣ ምጥነት፣ ጨዋነት እና ሰላም የተካሄደውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በተመለከተ የመንግሥት ግንኙነት ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚ/ር ዲኤታ አቶ ሽመልስ ከማል እና የሕወሓት/ኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ሁሴን የሰጡት ከድንጋጤ የመነጨ የተፋለሰ መግለጫ ነው። በነገራችን ላይ እንደተለመደው “የኢትዮጵያ” ቴሌቪዥን አንድም የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባል ወይንም የሰልፉ ተሳታፊ ዜጋ አላነጋገረም፣ ወይንም አላቀረበም – በወፍ-በረር ቅኝት በመበተን ላይ ያለና ዘርዘር ያለ የሕዝብ ስብስብ ጠብቆ በካሜራው ከመቅረፅና ማቅረብ በስተቀር።

የ”መንግሥት” ወገኖችን አተያይ ስንቃኝ፤

በመጀመሪያ ከ”ኢትዮጵያ” ቴሌቪዥን ብንጀምር ከክስ አዘል ዘገባዎቹ መካከል፡- “የሰልፈኞቹ ጥያቄ በፍርድ ቤት በተያዘው የሙስሊሙ መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የሸባሪነት ክስ ላያ አተኩሯል፣ በኢቲቪ እና በመንግሥት ላይ ያላቸውን ቅሬታ ገልፀዋል፣ አትነሳም ወይ ይሄ ባንዲራ ያንተ አይደለም ወይ ሲሉ ነበር፣ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት ዕውቅና የተሰጠው የሀገሪቱ ሰንደቅ ዓላማ እንዳይታይ ሲከለክሉም ተስተውለዋል፣ በተቃውሞ ሰልፉ ማጠናቀቂያ የእስልምና ተከታዮች የስግደት ሥነ-ስርዓት ፈጽመዋል።”

በመቀጠል አቶ ሽመልስ ከማል ከሰነዘሩዋቸው ውስጥ ደግሞ፡- “….መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አለመግባት የሚለውን ሕገ-መንግሥት አጥብቆ ያከብረዋል……..በተደረገው ሰልፍ በፖለቲካና በሃይማኖት መካከል ሕገ-መንግሥቱ ያሰመረው መስመር ሲደረመስ የሚታይበት ሁኔታ አለ፣ በሃይማኖት ሽፋን ሽብርተኝነት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ ያለውን ግለሰቦች የተከሳሾቹ ጠበቃዎች ከፍርድ ቤት ውጪ በሆነ ሂደት የፍርድ ሂደቱን ለማጨናገፍ መሞከር ሕግ አይፈቅድላቸውም፣ ከቤኒንሻንጉል ገምዝ የተፈናቀሉትን ሰዎች አስመልክቶ የዛሬዎቹ ሰዎች ኡኡታ ከማሰማታቸው አስቀድሞ መንግሥት ሁኔታውን አይቶ ፈጣን እርምጃና እርምት የወሰደበት ጉዳይ ነው ፣ ከዚህ ባለፈ እንዲህ ዓይነቶቹን ጉዳዮች….exceptions ወይም እንደ በስተቀር የሚወሰደውን ነገር (እጅግ በጣም አልፎ አልፎ የሚከሰት ነገር ማለታቸው ነው) ዋና መደበኛ አሠራር አስመስሎ ያንን አጉልቶ ከዚያ ፖለቲካዊ ትርፍ አስልቶ ለማግኘት የሚኬድ ነገር ውጤታማ ሊሆን እንደማይችል መታወቅ ይኖርበታል።”

በሌላ ወሬ የሕወሓት/ኢህአዴግ ቃል አቀባይ አቶ ሬድዋን ሁሴን “ሰማያዊ ፓርቲ ከአሸባሪዎች ጋር ፖለቲካዊ ጋብቻ መፈፀሙን እሁድ ለት በጠራው ሰልፍ በግልፅ አሳይቷል…” ብለዋል፡፡

ይህ ምን ይነግረናል? ምስክር በሦስት ይፀናል እንዲሉ አበው፤ ሦስት የመንግሥት ከፍተኛ አካላት (ኢቲቪ፣ አቶ ሽመልስ እና አቶ ሬድዋን) ከላይ የተጠቀሱትን መሠረተ-ቢስ ውንጀላዎች አካሂደዋል። በእነሱ ስሌት የበለጠ ጉዳትን ለማስቀረት በአጣብቂኝ ዕውቅና የሰጡት ሰላማዊ ሰልፍ ስኬታማነት ያስደነገጣቸውና ያበሳጫቸው የአገዛዙ ባለሥልጣናት የሰጡት  ይፋዊ መግለጫ የሚያሳየው፤ ቀድሞውኑ አማራጭ አጥተው የተስማሙበት ጉዳይ መሆኑን ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊትም ተመሳሳይ ጥያቄ ላለማስተናገድ ሰማያዊ ፓርቲን፣ አመራሩንና፣ ተቃዋሚ ሕዝቡን እንደተለመደው “በሽብርና ሕገ-መንግሥት ለመናድ መሞከር” በመወንጀል (framing the opposition forces by criminalizing peaceful dissent) የመፃዒ የቤት ሥራቸውን መሠረት ጥለዋል።

ስለዚህ ቀድሞውኑም “መንግሥት” የምርጫ ‘97 ዓይነቱን የፖለቲካ ክፍተት ፈቀደ፣ ዲሞክራሲያዊ ብልጭታ አሳየ ወዘተርፈ በማለት ለሺህኛ ጊዜ በየዋህነት ለተታለሉ የዋህ ዜጎች እላለሁ – በእኔ አመለካከት ሕወሓት/ኢህአዴግ መፈናፈኛ አጥቶ ነው ይህቺ የፖለቲካ ክፍተት የተፈጠረችበት እንጂ ሃገሪቱን ወደየት እየመራት እንደሆነ ለማንኛውም የሚያመዛዝን አዕምሮ ግልጽ ነው።

“መንግሥት” አሁን በያዘው አካሄድ አገዛዙ እንዲህ ያለ የፖለቲካ አዎንታዊነት መፍጠር ማለት ወደ ጠፈር በመተኮስ ላይ ያለን ሮኬት ጠምዝዞ ወደምድር የመመለስ ያህል ይመስለኛል። በዚህም ምክንያት እላለሁ – ትግሉ መራራ ነው። የተኛ መንቃት፣ የተናጠለ መደራጀት፣ የበቃው ቁርጠኝነት ይሻዋል።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule