ከእስረኞች ጠበቆች ጋር የተደረገው ውይይት ታፈነ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ከአሜሪካ የህግ ባለሙያዎች ማህበር ጋር በመሆን በኢትዮጵያ እስር ቤት ለሚገኙ የህሊናና የፖለቲካ አስረኞች ጥብቅና ከቆሙ የህግ ባለሙያዎች ጋር ለመነጋገር ያደረገው ሙከራ ታፈነ። የጋራ ንቅናቄው ለጎልጉል እንዳስታወቀው ዓርብ ሰባት ከሚሆኑ ጠበቆች ጋር ለመያየትና መረጃ ለመለዋወጥ መስመር ተዘርግቶ ነበር። አቶ ኦባንግ ሜቶና የጋራ ንቅናቄው የሚዲያ ዴስክ፣ ከአሜሪካ የጠበቆች ማህበር አራት፣ ከአዲስ አበባ ሰባት ጠበቆች በመሆን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 11 ሰዓት ላይ የስካይፕ ውይይት ለመጀመር ተዘጋጅተው ነበር። የጋራ ንቅናቄው እንዳስታወቀው ውይይቱ ሲጀመር ድምጽ መስማት አልተቻለም። በዚሁ ሳቢያ ውይይቱ መቋረጡን ያስታወቀው አኢጋን ከአሜሪካ የጠበቆች ማህበር ጋር በመነጋገር ሰኞ ቀን … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
Right Column - Primary Sidebar
የፖለቲካ ኃይል ሽግሽግ ትግል – ቁጥር 01
ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ እሁድ ግንቦት 25 ቀን 2005 ካለምንም እንከን ተጠናቀቀ። አምባገነን መለስ ዜናዊ ከግንቦት 8 ቀን 1997 ዓመተ ምህረት ጀምሮ በሽብርተኛ ህጎቹ እና ተግባሮቹ የገነባው የፍርሃት ፖለቲካ ህንጻ ፈረሰ። በዚኹ እለት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ኃይሎች ማዕከል በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ እና በማህበራዊ መስኮች መፈጸም አለባቸው የሚላቸውን እርማቶች በንግግሮች እና በመፈክሮች በአደባባይ አስታወቀ። እነሱም ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ሊቀርቡ ይችላሉ፥ “መብት መጠየቅ ወንጀል አይደለም፣ ነፃነት እንሻለን፤ ፍትህ እንሻለን፤ አንለያይም፤ የህሊና፣ የሃይማኖት እና ሌሎች ፖለቲከኛ እስረኞች ይፈቱ፤ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄዎች ይመለሱ፤ በአገራችን ሰላም አጣን፤ ልማት እያሉ ሙስና ሰሩ፤ በኑሮ ውድነት የጎበጠው ትከሻችን እረፍት ይሻል፤ ህዝብ ማፈናቀል የዘር ማጥራት ወንጀል … [Read more...] about የፖለቲካ ኃይል ሽግሽግ ትግል – ቁጥር 01
ኃያሉ አሜሪካ፤ የሞትህ ትዝታ በኢማኑዔል ቶድ
በፈረንሣዩ የታሪክና የህዝብ ቁጥር ዕድገት (Demography) ተመራማሪ በኢማኑዔል ቶድ (Emmanuele Todd) የተደረሰው መጽሀፍ ከሶቪየት ህብረት አገዛዝ መገርሰስ ወዲህ የቀረውና ብቸኛው ኃያል መንግሥት የሚባለውን የአሜሪካንን የበላይነት መቦርቦርና ውድቀት የሚያሳይ የ252 ገጽ መጽሀፍ ነው፡፡ (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ኃያሉ አሜሪካ፤ የሞትህ ትዝታ በኢማኑዔል ቶድ
እኛ ያልነው ለፉገራ…
በሰሞኑ ቀልድ ልጀምር። የአፈሪካ ህብረት ድርጅት 50ኛ አመቱን በያዝነው ሳምንት በአዲስ አበባ ሲያከብር በነበረው የሻምፓኝ ስነ-ስርዓት ላይ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ብቻ ከመሪዎቹ ተነጥለው ያለ ብርጭቆ ቆመዋል። ለፕሮቶኮል እንዲመሳሰሉ ቢጠየቁ አሻፈረኝ አሉ። የህብረቱ የወቅቱ ሊቀመንበር ስለነበሩ ለይሰሙላ እንኳን ብርጭቆዋን ጨብጡ ቢባሉ አይሆንም፣ ሃይማኖቴ አይፈቅድም አሉ። በመጨረሻ ግን በረከት ስምዖን በጆሯቸው አንዳች ነገር ነገራቸውና የያዘውን ብርጭቆ ሲሰጣቸው ተቀብለው በደስታ ጨለጡት። በረከት ለጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ በጆሯቸው እንዲህ ነበር ያላቸው። "ብርጭቆ ውስጥ ያለው መለስ የጀመረው ወይን ነው።" አሁን አሁን መቀለጃ እየሆኑ የመጡት ሃይለማርያም ደሳለኝ፤ መለስ የጀመረውን ሁሉ፤ ፉገራም ቢሆን - ያንን ለመጨረስ ነው የተቀመጥኩት ይሉናል። እየደጋገሙ! ብርኖ … [Read more...] about እኛ ያልነው ለፉገራ…
የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎች 60 የክስ መዝገቦች መቋረጣቸውን አስታወቀ
- የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት - ሁለት ተጠርጣሪዎች በምርመራ ወቅት መደብደባቸውን ተናገሩ ‹‹ተያዘ የተባለው ሰነድ ሁሉ በሀብት ምዝገባ ያስመዘገብኩት ነው›› አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ቡድን፣ በተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዲቋረጡ ከተደረጉት 60 የክስ መዝገቦች ውስጥ 28 ያህሉን መሰብሰቡን ግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡ መርማሪ ቡድኑ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ እንዳስረዳው፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ባለፉት 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ላይ የሠራውን የምርመራ ሥራ እንዳብራራው፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሥራዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን … [Read more...] about የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎች 60 የክስ መዝገቦች መቋረጣቸውን አስታወቀ
Egypt reacts to Ethiopia dam announcement
Ethiopia’s sudden announcement on Tuesday that it would begin diverting the Blue Nile ahead of the planned construction of the Grand Renaissance Dam has drawn reaction from several figures in Egypt, most notably Prime Minister Hisham Qandil and members of the Shura Council. Sudan’s Minister of Water Resources and Electricity, Osama Abdullah Mohamed Hassan, arrived in Cairo on Wednesday for a one-day visit to discuss the repercussions of Ethiopia’s announcement, state-owned news agency MENA … [Read more...] about Egypt reacts to Ethiopia dam announcement
Meles Zenawi and our money
The last seven years or so I have been writing opinion pieces on the political situation in our homeland. Naturally I have discussed the late Prime Minter Meles Zenawi and his central role in charting the direction our country should follow on the road he envisioned to improve the life of our people. Prime Minter Zenawi ruled over our country for twenty one years. One can say from 1991 when the TPLF took over to 2001 when the split within the party took place in the aftermath of the Eritrean … [Read more...] about Meles Zenawi and our money
ለደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መዕመናን የቀረበ ጥሪ
የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛለች ይኸውም ለሥልጣን ያቆበቆቡ እሾም ባዮች ፣ ለጥቅማቸው የቆሙ ግለሰቦች እና ሆድ አደሮች የሀገራችው ፣ የሕዝባቸው፣ የቤተ ክርስቲያኗ ገዳማውያን እና መናንያን ሐዘንና ሰቆቃ ሳይገዳቸው እኔ ከሞትኩኝ ስርዶ አይብቀል እንዳለችው አህያ የግል ቀቢጸ ተስፋቸውን (ego) ላማሟላት ብቻ ቤተ ክርስቲያኗን ለወያኔ አሳልፈው ለመስጠት መሰናዶአችውን ጨርሰውና ወገባቸውን ጠበቅ እድርገው ተነስተውልህ June 2, 2013ን በትልቅ ጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ (በነገጋችን ላይ ስለ June 2, 2013 ለማታውቁ ወይንም ላልሰማችሁ ለማሰማት ይረዳ ዘንድ….. June 2, 2013 የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ወደ ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ትቀላቀል ወይንስ አትቀላቀል የሚለው ውሳኔ ይሰጥ ዘንድ የቤተ ክርስቲያኗ የአስተዳደር ቦርድ … [Read more...] about ለደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን መዕመናን የቀረበ ጥሪ
ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ አባላትና ወዳጆች እንዲሁም በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን።
በስመ አብ፤ ወወልድ፤ ወመንፈስ ቅዱስ፤ አሐዱ አምላክ አሜን። በአንዲት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን የአስተዳደር ጉዳይ ወሳኞቹ የቤተ ክርስቲያኗ ዋልታና ምሰሶ የሆኑት አባላቷ ካህናት ምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች መሆናቸው በቃለ ዓዋዲውና በማንኛቸውም ሕገ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተደንግጎ የሚገኝ ሆኖ ሳለ፤ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው ግን ይህንን ሃቅ በመካድ አዛዡም ሆነ ወሳኙ እኛ ብቻ ነን በማለት ሕዝብን ማማከርም ሆነ በሕዝብ ማስወሰን ሳያስፈልጋቸው በገዛ ፈቃዳቸው ቤተ ክርስቲያንን በመዝጋት በዓብይ ጾምና በሱባዔ ወቅት ሕዝበ ክርስቲያንን በመበተን ለከፍተኛ መከራና ችግር ዳረጉት። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ አባላትና ወዳጆች እንዲሁም በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን።
አስቸኳይ ጥሪ በሆላንድ ለምትገኙ ኢትዮጵያን በሙሉ
አንደተለመደው መራሹ ወያኔ ኢ ህ አ ዴ ግ በመላው ዓለም አባይን ለመገደብ በሚል ምክኒያት የዋህ ደጋፊዎቹን አና በጥቂት ጥቅሞች የተደለሉ ሆዳሞችን በማስተባበር በሮተርዳም ከተማ ቅዳሜ 1 ጁን 2013 ልክ 13፡00 ሰዓት የቦንድ ዘረፋ ለማካሄድ ማቀዱን ከወያኔ ቀኝ እጅ ከሚባሉት ሾልኮ የወጣ ሚስጢር ደርሶናል ስለዚህ ቦታውና ሰዓቱን አሁንም በሌሎች አህጉሮች የደረሰበትን ሽንፈት በሆላንድም እንደሚገጥመው ሂሳቤ እንደሚያደርግ አንጠራጠርም ይህንን ፍራቻ ቦታውን እና ስዓቱን ከቀየረ በትክክል አውቀው የሚነግሩን ታማኞች አሰማርተናል ስለዚህ በዚህ ቀን ለአፈናና ህዝባችንን ለማሸበር የሚስበስቡትን ገንዘብ ተባብረን በማክሸፍ ወገናዊነታችን አናረጋግጥ እባኮዎን ከታቀደው ሰዓት ቢያንስ 2 ሰዓት ቀደም ብለን እንድንገጝ አደራችን ነው ቦታው :- DELFTSEPLEIN 37 3013 AA … [Read more...] about አስቸኳይ ጥሪ በሆላንድ ለምትገኙ ኢትዮጵያን በሙሉ










